• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ ይመረቃል

February 11, 2024 04:04 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ነጻነቷን ጠብቃ እንድትኖር ያደረጓት አባቶቻችንን የሚዘክር የዓድዋ ድል መታሰቢያ በአዲስ አበባ ፒያሳ ተገንብቶ ዛሬ ይመረቃል።

መታሰቢያው የተገነባው ጀግኖች ወደ ጦርነቱ ሲተሙ በአንድነት ተሰባስበው ጉዟቸውን የጀመሩበት ቦታ ላይ ነው።

የዓድዋ ድል መታሰቢያ ላይ የሚታየው 00 ኪሎ ሜትር መነሻ ቦታ የኮምፓስ ምልክት በአዲስ አበባ እንዲሁም በመላ ኢትዮጵያ ለሚገኙ ቦታዎች የርቀት መለኪያ መነሻ ነው።

የዓድዋ ድል መታሰቢያ በ5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን 5 ወለል እና 8 በሮች አሉት። አጠቃላይ ከታች እስከ ላይ በ5ቱ ወለል ላይ ያለዉ መሬት ስፋት 12 ሄክታር ነው።

ሙዚየሙ ከምድር በታች ያለውን ሁለት ደረጃዎችን ጨምሮ 5 ወለሎች አሉት። ከ1 ሺህ በላይ የመኪና ማቆሚያ፣ ሲሲቲቪ ካሜራ፣የራሱ መቆጣጠሪያ ያለው ስማርት ፓርኪን ሥርዓት አለው።

በአንድ ጊዜ 2 ሺህ 500 ሰዎችን መያዝ የሚችል የፓንአፍሪካኒዝም አዳራሽ፣ 2 ሺህ 300 ሰዎችን መያዝ የሚችል ዘመናዊ ሁለገብ አዳራሽ፣ 4 ሺህ ሰዎችን መያዝ የሚችል የቤት ውስጥ የስፖርት ሜዳ እና አዳራሽ ይዟል።

የህፃናት መጫወቻ፣ የንግድ ሱቆች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ፣ ካፌና ሬስቶራንት፣ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ ቢሮዎች እና የአርት ጋላሪ አለው።

ለዓድዋ ጦርነት ሰበብ የሆነው የውጫሌ ውል አንቀፅ 17ን እንዲሁም ከድሉ በኋላ የአዲስ አበባ ውል በሚል ኢትዮጵያ እና ጣሊያን ካደረጉት ስምምነት ውስጥ ሁለት አንቀፆች ይገኙበታል። እነሱም ኢትዮጵያ ሉዓላዊ አገር መሆኗን እና የውጫሌ ውል በዚህ ውል መሰረዙን፣ የውጫሌው ውል ምንም የሕግ ውጤት እንደማይኖረው የሚያረጋግጡ አንቀፆች ናቸው።

የዓድዋ ድል ታሪክን የኢትጵዮያዊነት እሴቶችን የሚገልፁ ቅርፃ ቅርፆች፣ የሥዕል ሥራዎች ለእይታ ቀርበዋል።

መታሰቢያው እያንዳንዳቸው 280 ሰዎችን መያዝ የሚችሉ 2 ሲኒማ ቤቶች አሉት። ቤተመጻሕፍት፣ የቤት ውስጥ ውድድሮች ሜዳ፣ የህፃናት መጫወቻ ስፍራ እና ጂምናዚየም ተሰርቶለታል።

የምሥራቅ ጀግኖች በር፣ የምዕራብ ጀግኖች በር፣ የሰሜን ጀግኖች በር፣ የደቡብ ጀግኖች በር፣ የፈረሰኞች በር፣ የአርበኞች በር፣ የፓንአፍሪካኒዝም በር ተብለው የተሰየሙ ስምንት በሮች አሉት።

በ4ቱም አቅጣጫዎች የተሰየሙ በሮች በዓድዋ ድል ከአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያውያን በጋራ የተሳተፉበት የጋራ ድላቸው መሆኑን ያመለክታል። የአንድነት ድልድይ ሙዚየሙን ከማዘጋጃ ቤቱ ጋር እንዲያገናኝ ታስቦ የተሰራ እና ትናንት ከዛሬ ዛሬን ከነገ ያሚያገናኝ ነው።

የኢትዮጵያ ታሪክን፣ የባህል አሻራዎችን፣ የጦር ሜዳ ስፍራዎችን የሚያሳዩ እና የዓድዋ ድል የክተት አዋጅ የታወጀበት ነጋሪት በነሐስ ተሰርቶ በሙዚየሙ ውስጥ ይገኛሉ።

የዓድዋ ድል መሃንዲሶች አፄ ምኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ ብጡል ሀውልት፣ የ12ቱን የጦር መሪዎች ሀውልት፤ በጦርነቱ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን እና የቤት እንሰሳት መታሰቢያ የቅርፃ ቅርፅ እና የአርት ሥራዎችንም ይዟል።

በጦርነት ግንባር ከዘመቱ 120 ሺህ ጀግኖች መካከል 45 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን እና በዐውደ ውጊያው ከመሳተፍ አልፈው ምግብ ዝግጅት እና ቁስለኞችን በመንከባከብ ሴቶች ለድሉ ቁልፍ ሚና መጫወታቸውን የሚዘክር ማስታወሻ ተቀምጧል።

የጀግኖች መታሰቢያ ሀውልት ማስታወሻ፣ የዓድዋ ድል ለፓንአፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያበረከተውን አስተዋጽኦ የሚዘክር የአፍሪካ ከርታ እና የኅብረቱን አርማ እንደፀሐይ ብርሃን ፈንጣቂ ማሳያ ይዟል።

ከዓድዋ ጀግኖች መታሰቢያ ሐዉልት አጠገብ ደግሞ የአሁኑ ትውልድ በገንዘቡ በጉልበቱ በእውቀቱ ያለምንም ብድር እና እርዳታ በራሱ አቅም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ እውን ማድረጉን የሚያመለክተው ፋውንቴን ተሰርቶለታል።

በነጋሪት ቅርጹ ትይዩ ያለው ስፍራ የዓድዋ ድል በዓል ማክበርያ ቦታ ነው። መታሰቢያ ዲዛይኑም ግንባታውም የግንባታ ቁጥጥሩም በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የተሰራ እና የከተማዋን ገፅታ የቀየረ ነው።

default

በኢትዮጵያ የተሰራችው እና ከ88 ዓመታት ስደት በኋላ ወደ ሀገሯ የተመለሰችው ፀሀይ አውሮፕላን በዓድዋ ድል መታሰቢያ እንድትቀመጥ ተደርጓል።

ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እና የዓድዋ ድል ትስስር የዓድዋ ዘመን ትውልድ በአንድነት እና በተባበረ ክንድ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት አስከብረው ነፃ አገር እንዳስረከቡን ሁሉ የዚህ ዘመን ትውልድ ደግሞ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን በአንድነት እና በተባበረ ክንድ በመላ ኢትዮጵያውያን ርብርብ የኢትዮጵያን ሕዳሴ ያበሰረ የዘመናችን ዓድዋን ገንብቷል። ተምሳሌቱም የአኩሪ ታሪክ ግንባታችን ይቀጥላል የሚል ነው። (በላሉ ኢታላ፤ ኢቢሲ)

  • default
  • default
  • default
  • default
  • default
  • default
  • default
  • default
  • default
  • default

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: adwa, African Victory, emperor menelik, Queen Tayitu

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule