• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”

November 27, 2019 12:32 pm by Editor Leave a Comment

የህወሓት ዘመን ማብቂያው አካባቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ካለ በኋላ ለጠ/ሚ/ር ቦታ በተደረገው ሽኩቻ ዶ/ር ዐቢይ (የለማ ቡድን) አሸንፎ በወጣ ጊዜ የህወሓት ቡድን ወደ መቀሌ ሄዶ ሲመሽግ ስብሃት ነጋ በተፈጠረው ተናድዶ የሚከተለውን መናገሩ ታማጭ የመረጃ ምንጫችን አስታውቆናል። ስብሃት ነጋ በትግሪኛ የተናገረውና በአማርኛ ተተርጎመው የስብሃት ንግግር እንዲህ ይነበባል፤

“(ደመቀ) ለትህነግ ታማኝና ታዛዥ ነበር። ፈፅም! የተባለውን ነገር ለመፈፀም ‘ለምን?’ ብሎ እንኳን አያውቅም። አንድ ቀን ግን የሱዳን ግዛት የሆነውን አዋሳኝ መሬት ለመስጠት ‘ፈርም’ ሲባል ‘አይሆንም አልፈርምም!’ ብሎ አሻፈረኝ ሲል ያኔ ይህ ሰው አንድ ቀን እንደሚሸውደን እርግጠኛ ሁኜ ለጓዶቼ ነግሬያቸው ነበር። ሁሉም የእኔን እይታ ሳያቅማሙ ሲቀበሉኝ ጌታቸው (አሰፋ)ግን ‘አታስብ እሱ መዳፋችን ውስጥ ነው፤ የትም አይደርስም!’ ብሎ በንቀት ሲመልስልኝ ሲሰሙ ሌሎቹ ጓዶች በጌታቸው ላይ ከፍተኛ እምነት ስለነበራቸው እነሱም የኔን ንግግር ወደጎን ተውት።

“እኔ ግን ‘ጀግናን የሚገድለው ተራ ወይም የተናቀ ሰው ነው’ ብየ ጌታቸውን አስጠንቅቄው ነበር። የመጨረሻው የጠ/ሚ/ር የውድድር ዕለት ዋዜማ ማታ ላይ በነበረን ስብሰባም ይህ ሰው አንድ ነገር እንዳያደርግ በሚል ጥሩ ስሜት እንደማይሰማኝ ስናገር በተለይ ጌታቸው አሰፋ፣ ጌታቸው ረዳ እና አቦይ ፀሀየ ‘አትጨነቅ ደመቀ በሚገባ አምኖበታል፤ የተባለውን ባያደርግ የሚደርስበትንም ያውቃል፤ በተጨማሪ ደግሞ ሁሉንም የብአዴን፣ የኦህዴድ እና የደኢህዴን አባላት ቀጣይ የከፍተኛ ሚኒስትርነት ስልጣንና ዳጎስ ያለ ገንዘብ እንደሚሰጣቸው በራሳቸው ሰዎች ስለተነገራቸው በደስታ ተቀብለውታል’ ብለው ሊያሳምኑኝ ሞከሩ። በእርግጥም በተለይ የደኢህዴንና የብአዴን አመራሮች ለሥልጣንና ለጥቅም የማይከፍሉት ዋጋ እንደሌለ በማስረጃ ሲያስቀምጡልኝ ባላምንበትም ይሁን ብየ ተውኩት።

“በትጥቅ ትግል ወቅትም ሆነ በሥልጣን ላይ ከሆንን በኋላ ድርጅቴ ሊደርስበት ከተጋረጠ እስከ መፍረስ የሚያደርስ ከፍተኛ አደጋዎች በአለቀ ሰዓት እንኳን እንደታደግሁ ስለሚያውቁኝ ይቀበሉኛል ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር። አሁን ግን ከእኔ ውጪ የእኔን ሀሳብ የሚያስብና የሚደግፈኝ ሰው ሳጣ ዝም ብየ ቁጭ አልኩና የሚሆነውን ለማየት ወሰንኩ። በመጨረሻ ግን ለረጅም አመታት በነበረን የትጥቅ ትግል መሰሪው ጀበሃ (ሻዕቢያ) እንኳን ሸውዶን የማያውቀውን ሽወዳ ደመቀ ሸወደን! አዋረደን! ለዚህ ውድቀታችን ተጠያቂዎች ሁለቱ ጌታቸው የተባሉትና ፀሀየ ናቸው”።

ስብሃት ነጋ እንደ አንጋፋ የህወሓት ኃላፊ ይህንን ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም ሳይሰማ በመቅረቱ የለውጡ ባቡር እየተጓዘ ያለበትን ፍጥነት ህወሓቶች ሊደርሱበት የማይችሉ እንዲሆን አድርጎታል። አሁንም በስተመጨረሻው የኢህአዴግ ፓርቲዎች ተሰባስበው (ህወሓትንም ጨምሮ) የወሰኑትን የውህደት ሃሳብ ህወሓቶች ለመቀበል አቅቷቸው እዚህ ግባ የማይባል ምክንያቶች እየደረደሩ ይገኛሉ።

ሦስቱ እህት ፓርቲዎች ከአምስቱ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ኢህአዴግን ወደ መቃብር ልከው በአዲስ ፓርቲና መርሃ ግብር ወደ ምርጫው ይገባሉ። ህወሓት “ኢህአዴግ አይፈርሰም” ብትልም በፖለቲካዊ አካሄድም ሆነ በሕግ ማስቆም ግን በፍጹም የማትችልበት ሁኔታ ላይ ትገኛለች።

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና እስካሁን በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኘው ትህነግ/ህወሓት በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የተገንጣዮች ጥርቅም እንደሆነ ይታወቃል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: abiy ahmed, demeke, Full Width Top, Middle Column, sibhat, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule