• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”

November 27, 2019 12:32 pm by Editor Leave a Comment

የህወሓት ዘመን ማብቂያው አካባቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ካለ በኋላ ለጠ/ሚ/ር ቦታ በተደረገው ሽኩቻ ዶ/ር ዐቢይ (የለማ ቡድን) አሸንፎ በወጣ ጊዜ የህወሓት ቡድን ወደ መቀሌ ሄዶ ሲመሽግ ስብሃት ነጋ በተፈጠረው ተናድዶ የሚከተለውን መናገሩ ታማጭ የመረጃ ምንጫችን አስታውቆናል። ስብሃት ነጋ በትግሪኛ የተናገረውና በአማርኛ ተተርጎመው የስብሃት ንግግር እንዲህ ይነበባል፤

“(ደመቀ) ለትህነግ ታማኝና ታዛዥ ነበር። ፈፅም! የተባለውን ነገር ለመፈፀም ‘ለምን?’ ብሎ እንኳን አያውቅም። አንድ ቀን ግን የሱዳን ግዛት የሆነውን አዋሳኝ መሬት ለመስጠት ‘ፈርም’ ሲባል ‘አይሆንም አልፈርምም!’ ብሎ አሻፈረኝ ሲል ያኔ ይህ ሰው አንድ ቀን እንደሚሸውደን እርግጠኛ ሁኜ ለጓዶቼ ነግሬያቸው ነበር። ሁሉም የእኔን እይታ ሳያቅማሙ ሲቀበሉኝ ጌታቸው (አሰፋ)ግን ‘አታስብ እሱ መዳፋችን ውስጥ ነው፤ የትም አይደርስም!’ ብሎ በንቀት ሲመልስልኝ ሲሰሙ ሌሎቹ ጓዶች በጌታቸው ላይ ከፍተኛ እምነት ስለነበራቸው እነሱም የኔን ንግግር ወደጎን ተውት።

“እኔ ግን ‘ጀግናን የሚገድለው ተራ ወይም የተናቀ ሰው ነው’ ብየ ጌታቸውን አስጠንቅቄው ነበር። የመጨረሻው የጠ/ሚ/ር የውድድር ዕለት ዋዜማ ማታ ላይ በነበረን ስብሰባም ይህ ሰው አንድ ነገር እንዳያደርግ በሚል ጥሩ ስሜት እንደማይሰማኝ ስናገር በተለይ ጌታቸው አሰፋ፣ ጌታቸው ረዳ እና አቦይ ፀሀየ ‘አትጨነቅ ደመቀ በሚገባ አምኖበታል፤ የተባለውን ባያደርግ የሚደርስበትንም ያውቃል፤ በተጨማሪ ደግሞ ሁሉንም የብአዴን፣ የኦህዴድ እና የደኢህዴን አባላት ቀጣይ የከፍተኛ ሚኒስትርነት ስልጣንና ዳጎስ ያለ ገንዘብ እንደሚሰጣቸው በራሳቸው ሰዎች ስለተነገራቸው በደስታ ተቀብለውታል’ ብለው ሊያሳምኑኝ ሞከሩ። በእርግጥም በተለይ የደኢህዴንና የብአዴን አመራሮች ለሥልጣንና ለጥቅም የማይከፍሉት ዋጋ እንደሌለ በማስረጃ ሲያስቀምጡልኝ ባላምንበትም ይሁን ብየ ተውኩት።

“በትጥቅ ትግል ወቅትም ሆነ በሥልጣን ላይ ከሆንን በኋላ ድርጅቴ ሊደርስበት ከተጋረጠ እስከ መፍረስ የሚያደርስ ከፍተኛ አደጋዎች በአለቀ ሰዓት እንኳን እንደታደግሁ ስለሚያውቁኝ ይቀበሉኛል ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር። አሁን ግን ከእኔ ውጪ የእኔን ሀሳብ የሚያስብና የሚደግፈኝ ሰው ሳጣ ዝም ብየ ቁጭ አልኩና የሚሆነውን ለማየት ወሰንኩ። በመጨረሻ ግን ለረጅም አመታት በነበረን የትጥቅ ትግል መሰሪው ጀበሃ (ሻዕቢያ) እንኳን ሸውዶን የማያውቀውን ሽወዳ ደመቀ ሸወደን! አዋረደን! ለዚህ ውድቀታችን ተጠያቂዎች ሁለቱ ጌታቸው የተባሉትና ፀሀየ ናቸው”።

ስብሃት ነጋ እንደ አንጋፋ የህወሓት ኃላፊ ይህንን ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም ሳይሰማ በመቅረቱ የለውጡ ባቡር እየተጓዘ ያለበትን ፍጥነት ህወሓቶች ሊደርሱበት የማይችሉ እንዲሆን አድርጎታል። አሁንም በስተመጨረሻው የኢህአዴግ ፓርቲዎች ተሰባስበው (ህወሓትንም ጨምሮ) የወሰኑትን የውህደት ሃሳብ ህወሓቶች ለመቀበል አቅቷቸው እዚህ ግባ የማይባል ምክንያቶች እየደረደሩ ይገኛሉ።

ሦስቱ እህት ፓርቲዎች ከአምስቱ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ኢህአዴግን ወደ መቃብር ልከው በአዲስ ፓርቲና መርሃ ግብር ወደ ምርጫው ይገባሉ። ህወሓት “ኢህአዴግ አይፈርሰም” ብትልም በፖለቲካዊ አካሄድም ሆነ በሕግ ማስቆም ግን በፍጹም የማትችልበት ሁኔታ ላይ ትገኛለች።

ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና እስካሁን በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኘው ትህነግ/ህወሓት በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የተገንጣዮች ጥርቅም እንደሆነ ይታወቃል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: abiy ahmed, demeke, Full Width Top, Middle Column, sibhat, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule