• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው”

September 20, 2021 10:43 am by Editor Leave a Comment

በጋሸና ግንባር የሚገኙ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት በጠላት ላይ የላቀ የበላይነት እያገኙ እንደሆነ አባላቱና መሪዎቹ ተናግረዋል።

ሳጅን ካሳዬ ወርቁ በጋይንት ግንባር ያለው የአማራ ልዩ ኃይል ተጋድሎ አኩሪ እንደነበረ ተናግሯል። ልዩ ኃይሉ ከጋሳይ ጀምሮ እስከ ደብረ ዘቢጥ ጀብድ ፈጽሟል ብሏል። የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ልዩ ኃይሉ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድንን በተቀናጀ መልኩ እንደደመሰሱት ገልጿል።

ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ለማስረከብ እንደተገደደም አስረድቷል። ኮንስታብል አሳልፍ ተመሰለው ልዩ ኃይሉ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እንደደመሰሱት ተናግሯል። የአማራ ብሎም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ከአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ነፃ እስኪሆኑ ድረስ ተጋድሏቸውን እንደሚቀጥሉ ነው የተናገረው።

ኮንስታብል እህቱ ጌታ በጠላት ላይ የተቀዳጁት ድል ወርቃማ እንደነበር ገልጻል “እኛ መቼም ቢሆን ወደ ኋላ አንመለስም፤ ጠላትን ከወንዶች እኩል እየታገልኩና እያሸነፍኩ ነው፤ ጠላት ቀድሞ ቢመሽግም ምሽጉን መስበር ችለናል፤ ከፍተኛ ውድመት የደረሰበት ጠላት ሬሳውን እንኳን ማንሳት አልቻለም” ብላለች። ለሕዝቡ ነፃነት ሲባል ዝናብ፣ ብርድና ፀሐይን ችለው እንደሚታገሉም አስረድታለች።

ረዳት ኢንስፔክተር አስፋው አረጋ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ብዙ ጀግኖችን ያፈራ ለቀናት መዋጋት የሚችል ትኩስ ኃይል ነው ብለዋል። አባላቱ የጠላትን ምሽግ በማፍረስም ይታወቃሉ ነው ያሉት። “የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ልክ እንደ አባቶቹ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው ጠላትን የሚቀጣው” ብለዋል።

የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድንን ከአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን ከየትም ቦታ ሙሉ በሙሉ ለማጽዳት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ወንድሞቹ ጋር በመናበብ፣ እጅና ጓንት ሆነው ጠላትን በመደምሰስ ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል። ለትግላቸው ስኬት የአማራም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ደጀንነት ወሳኝ መሆኑንም ረዳት ኢንስፔክተሩ አስረድተዋል።

የአማራ ክልል ልዩ ኃይል የመቅደላ ብርጌድ አዛዥ ኮሎኔል አዱኛ አለማየሁ በመቄት ወረዳ ፍላቂት አካባቢ ጠላት የመጨረሻውን እድል የወሰነበት ነው ብለዋል። ጠላት የተጠቀመበት አካባቢ ለውጊያ አስቸጋሪ ቢሆንም የተለያየ የውትድርና ስልቶችን በመጠቀም ሳይመለስ እንዲቀበር አድርገነዋል ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ልዩ ኃይልና የሀገር መከላከያ ሠራዊት ለአንድ ዓላማ ነው የሚታገሉት ያሉት አዛዡ በቅርቡ ጠላትን ቀብረን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ድልን እናበስራለን ብለዋል።

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን ከደቡብ ጎንደር ዞን ጋሳይ ከተማ ጀምሮ እስከ ሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ድረስ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ሊማር በሚችልበት ሁኔታ እንደተቀጣ ተመልክቷል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule