• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው”

September 20, 2021 10:43 am by Editor Leave a Comment

በጋሸና ግንባር የሚገኙ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት በጠላት ላይ የላቀ የበላይነት እያገኙ እንደሆነ አባላቱና መሪዎቹ ተናግረዋል።

ሳጅን ካሳዬ ወርቁ በጋይንት ግንባር ያለው የአማራ ልዩ ኃይል ተጋድሎ አኩሪ እንደነበረ ተናግሯል። ልዩ ኃይሉ ከጋሳይ ጀምሮ እስከ ደብረ ዘቢጥ ጀብድ ፈጽሟል ብሏል። የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ልዩ ኃይሉ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድንን በተቀናጀ መልኩ እንደደመሰሱት ገልጿል።

ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ለማስረከብ እንደተገደደም አስረድቷል። ኮንስታብል አሳልፍ ተመሰለው ልዩ ኃይሉ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እንደደመሰሱት ተናግሯል። የአማራ ብሎም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ከአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ነፃ እስኪሆኑ ድረስ ተጋድሏቸውን እንደሚቀጥሉ ነው የተናገረው።

ኮንስታብል እህቱ ጌታ በጠላት ላይ የተቀዳጁት ድል ወርቃማ እንደነበር ገልጻል “እኛ መቼም ቢሆን ወደ ኋላ አንመለስም፤ ጠላትን ከወንዶች እኩል እየታገልኩና እያሸነፍኩ ነው፤ ጠላት ቀድሞ ቢመሽግም ምሽጉን መስበር ችለናል፤ ከፍተኛ ውድመት የደረሰበት ጠላት ሬሳውን እንኳን ማንሳት አልቻለም” ብላለች። ለሕዝቡ ነፃነት ሲባል ዝናብ፣ ብርድና ፀሐይን ችለው እንደሚታገሉም አስረድታለች።

ረዳት ኢንስፔክተር አስፋው አረጋ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ብዙ ጀግኖችን ያፈራ ለቀናት መዋጋት የሚችል ትኩስ ኃይል ነው ብለዋል። አባላቱ የጠላትን ምሽግ በማፍረስም ይታወቃሉ ነው ያሉት። “የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ልክ እንደ አባቶቹ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው ጠላትን የሚቀጣው” ብለዋል።

የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድንን ከአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን ከየትም ቦታ ሙሉ በሙሉ ለማጽዳት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ወንድሞቹ ጋር በመናበብ፣ እጅና ጓንት ሆነው ጠላትን በመደምሰስ ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል። ለትግላቸው ስኬት የአማራም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ደጀንነት ወሳኝ መሆኑንም ረዳት ኢንስፔክተሩ አስረድተዋል።

የአማራ ክልል ልዩ ኃይል የመቅደላ ብርጌድ አዛዥ ኮሎኔል አዱኛ አለማየሁ በመቄት ወረዳ ፍላቂት አካባቢ ጠላት የመጨረሻውን እድል የወሰነበት ነው ብለዋል። ጠላት የተጠቀመበት አካባቢ ለውጊያ አስቸጋሪ ቢሆንም የተለያየ የውትድርና ስልቶችን በመጠቀም ሳይመለስ እንዲቀበር አድርገነዋል ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ልዩ ኃይልና የሀገር መከላከያ ሠራዊት ለአንድ ዓላማ ነው የሚታገሉት ያሉት አዛዡ በቅርቡ ጠላትን ቀብረን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ድልን እናበስራለን ብለዋል።

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን ከደቡብ ጎንደር ዞን ጋሳይ ከተማ ጀምሮ እስከ ሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ድረስ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ሊማር በሚችልበት ሁኔታ እንደተቀጣ ተመልክቷል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule