• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው”

September 20, 2021 10:43 am by Editor Leave a Comment

በጋሸና ግንባር የሚገኙ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት በጠላት ላይ የላቀ የበላይነት እያገኙ እንደሆነ አባላቱና መሪዎቹ ተናግረዋል።

ሳጅን ካሳዬ ወርቁ በጋይንት ግንባር ያለው የአማራ ልዩ ኃይል ተጋድሎ አኩሪ እንደነበረ ተናግሯል። ልዩ ኃይሉ ከጋሳይ ጀምሮ እስከ ደብረ ዘቢጥ ጀብድ ፈጽሟል ብሏል። የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ልዩ ኃይሉ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድንን በተቀናጀ መልኩ እንደደመሰሱት ገልጿል።

ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ለማስረከብ እንደተገደደም አስረድቷል። ኮንስታብል አሳልፍ ተመሰለው ልዩ ኃይሉ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድንን እንደደመሰሱት ተናግሯል። የአማራ ብሎም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ከአሸባሪው ትህነግ ወራሪ ቡድን ነፃ እስኪሆኑ ድረስ ተጋድሏቸውን እንደሚቀጥሉ ነው የተናገረው።

ኮንስታብል እህቱ ጌታ በጠላት ላይ የተቀዳጁት ድል ወርቃማ እንደነበር ገልጻል “እኛ መቼም ቢሆን ወደ ኋላ አንመለስም፤ ጠላትን ከወንዶች እኩል እየታገልኩና እያሸነፍኩ ነው፤ ጠላት ቀድሞ ቢመሽግም ምሽጉን መስበር ችለናል፤ ከፍተኛ ውድመት የደረሰበት ጠላት ሬሳውን እንኳን ማንሳት አልቻለም” ብላለች። ለሕዝቡ ነፃነት ሲባል ዝናብ፣ ብርድና ፀሐይን ችለው እንደሚታገሉም አስረድታለች።

ረዳት ኢንስፔክተር አስፋው አረጋ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ብዙ ጀግኖችን ያፈራ ለቀናት መዋጋት የሚችል ትኩስ ኃይል ነው ብለዋል። አባላቱ የጠላትን ምሽግ በማፍረስም ይታወቃሉ ነው ያሉት። “የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ሲተኩስ ልክ እንደ አባቶቹ ከአንገት በላይ መምታት እንዳለበት አምኖ ነው ጠላትን የሚቀጣው” ብለዋል።

የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድንን ከአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን ከየትም ቦታ ሙሉ በሙሉ ለማጽዳት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ወንድሞቹ ጋር በመናበብ፣ እጅና ጓንት ሆነው ጠላትን በመደምሰስ ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል። ለትግላቸው ስኬት የአማራም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ደጀንነት ወሳኝ መሆኑንም ረዳት ኢንስፔክተሩ አስረድተዋል።

የአማራ ክልል ልዩ ኃይል የመቅደላ ብርጌድ አዛዥ ኮሎኔል አዱኛ አለማየሁ በመቄት ወረዳ ፍላቂት አካባቢ ጠላት የመጨረሻውን እድል የወሰነበት ነው ብለዋል። ጠላት የተጠቀመበት አካባቢ ለውጊያ አስቸጋሪ ቢሆንም የተለያየ የውትድርና ስልቶችን በመጠቀም ሳይመለስ እንዲቀበር አድርገነዋል ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ልዩ ኃይልና የሀገር መከላከያ ሠራዊት ለአንድ ዓላማ ነው የሚታገሉት ያሉት አዛዡ በቅርቡ ጠላትን ቀብረን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ድልን እናበስራለን ብለዋል።

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን ከደቡብ ጎንደር ዞን ጋሳይ ከተማ ጀምሮ እስከ ሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ድረስ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን ሊማር በሚችልበት ሁኔታ እንደተቀጣ ተመልክቷል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule