• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ

August 11, 2022 03:04 pm by Editor 1 Comment

ነገሩ እንዲህ ነው። በኦሮሚያ ክልል በሆሩ ጉድሩ ወለጋ ዞን ጮማን ጉዱሩ ወረዳ ውስጥ ካሉት ቀበሌዎች መካከል በአንዲት ቀበሌ ውስጥ ታላቅ ጀብዱ ተፈፅሟል። ቀበሌዋ ጉደኔ ጫላ ሲበሬ ትባላለች። እንደወትሮው ሁሉ ህዝቡ ውስጥ ለመደበቅ የአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ወደዚህች ቀበሌ ዘልቀው ይገባሉ።

ነገር ግን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ አሁን በቃችሁን በማለት 07 ወጣቶች ከታጠቁት ሸኔ ታጣቂዎች ጋር በጦርና በገጀራ ጦርነት ገጠሙ። ከ7ቱ ሶስቱ የዩኒቨሪሲቲ ተማሪዎች ሲሆኑ አራቱ ደግሞ አርሶ ከደር ናቸው። ጩሃቱን የሰማው የቀበሌው ህዝብ በሙሉ በነቂስ ወጥቶ ከታጠቁት ሸኔዎች ጋር በባህላዊ ጦርና ገጀራ ገጠሙ።

ይህንኑ ያላሰቡትን የህዝብ ማዕበልና ቁጣ አይተው የተደናበሩት አሸባሪዎች እግር አውጪኝ ብለው እግራቸው ወደመራቸው አቅጣጫ መሸሽን መረጡ። ነገር ግን የህዝብ ማዕበሉ አንዱን በጦር በመግደል ሶስቱን ደግሞ ከእነትጥቃቸው ማርኮ ለወረዳው አስተዳደርና በአከባቢው ለተሰማራው ለመከላከያ ሰራዊታችን አስረክበዋል።

ይህንን ጀብዱ የሰሙ አጎራባች የወረዳው ቀበሌዎች በሙሉ በጋራ አደባባይ ወጥተው ለጀግናዋ ቀበሌ ህዝብ የጀግኖች አቀባበል አደረጉ።

በተዘጋጀው መርሐ ግብር ላይ ጀብዱ ለፈፀሙት አባላትና ለቀበሌዋ ህዝብ ዕውቅና ተሠጠ። የዞን አመራሮችንና በአከባቢው የተሰማራውን የመከላከያ ሰራዊት አመራሮችም ተጋበዙ። ከታጠቁት ታጣቂዎች ጋር ገጥመው ሞትና ሞርኮ ላደረጉ የቀበሌው አባላት ሠንጋዎች ቀረላቸው።

በዝግጅቱ ላይ በመገኘት ለጀግኖቹ የዕውቅና ሽልማት በመስጠት ንግግር ያደረጉት የሆሩ ጉድሩ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ምሬሳ ፊጣ የሸኔ የሚደበቅበትን የማሳጣት ዘመቻ ማብቃቱን አብስረዋል። ከእንግዲህ ሆሩ ጉድሩ ዞን የሰላምና የልማት ዘመቻ እንጂ በቀመኞቹና ዘራፊዎች የመበደል ጊዜ አብቅተዋል። ማብቃቱን ደግሞ የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ህዝቦች በህዝባዊ ማዕበል ጀብዱ በመፈፀም በተግባር አሳይተችሁናልና የጀግንነታችሁ ችቦ ደግሞ በመላው ዞናችን ይቀጣጠላል ብለዋል።

ጀብዱ ለፈፀሙት ለዩኒቨርስቲው 3 ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው ሶስት ሶስት ሺህ የተበረከተላቸው ሲሆን ለቀሩት ለአራት አርሶ አደሮች ደግሞ ለእያንዳንዳቸው ጠመንጃና ሰርትፍኬት ተሸልመዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት በአከባቢው የተሰማራው ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ደግሞ ከህዝባችን ጋር የጀመርነውን የአሸባሪው ሸኔን የማፅዳት ዘመቻ አጠናክረን በመቀጠል ዞኑንና መላውን ኦሮሚያን የሰላምና የልማት ቀጠና እናደርጋለን አትጠራጠሩ ብለዋል።

በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን በአሁኑ ወቅት የክልሉ ልዩ ሃይል ፤ ህዝባዊ ፖሊስና ሚልሻ ፤ የፌደራል ፖሊስ አባለት በሙሉ በመከላከያ ኮማድ ፖስት ስር ሆኖ ዞኑን ከአሻባሪው ሸኔ በማፅዳት ላይ ይገኛሉ።

(ታሪኩ ሻሜቦ ከመከላከያ ሠራዊት፤ ፎቶግራፍ የሆሩ ጉድሩ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, shemelis abdissa, SHINE, wollega

Reader Interactions

Comments

  1. Tediros Tsaew says

    August 17, 2022 07:46 pm at 7:46 pm

    ስ ጃካማ ያነበብኩት ጣጣም ነዉ የወደድኩት

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule