• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም”አቶ ክርስቲያን

November 9, 2021 10:29 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የተቃጣባትን የህልውና አደጋ ለመመከትና ሀገርን ለማስቀጠል እያንዳንዱ ዜጋ የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ገለጹ።

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እንደተናገሩት፤ አሸባሪው ሕወሓት ከምስረታው ጀምሮ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተፈጠረ ቡድን በመሆኑ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል የሚፈልግ ዜጋ ሁሉ ይህንን አሸባሪ ቡድን ግንባር ድረስ ሄዶ ሊፋለመው ይገባል።

አቶ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ከአሸባሪው ሕወሓት ውጪ በዓለም ታሪክ የመራትን ሀገር ለማጥፋት አልሞ የተነሳ የፖለቲካ ፓርቲ የለም። አሸባሪው የሕወሓት ቡድን በገሀድ ሀገርን የማፍረስ አላማን አንግቦ ኢትዮጵያን በማፈራረስ ወደ ትናንሽ መንደርነት የመቀየር ፍላጎት አለው።

አቶ ክርስቲያን አሸባሪ ቡድኑ ለህፃናት አረጋውያንና ለደከሙት እንዲሁም ለእንስሳትም ጭምር የማይራራ መሆኑን ገልፀው፤ ቡድኑን ማስወገድ ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑንም ጠቁመዋል።

አቶ ክርስቲያን ማንኛውም ህብረተሰብ አካባቢውን የመጠበቅ ሞራልያዊ መብት እንዳለው እንደሚያምኑ የጠቆሙ ሲሆን፤ ፓርቲያቸውም በዚህ ሀገርን የማዳን እንቅስቃሴ ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ፓርቲያቸው የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ለህልውና ዘመቻው መንግሥት ጥሪ ከማቅረቡ በፊት ጀምሮ በራሱ ተነሳሽነት እንደተሳተፈ የጠቆሙት አቶ ክርስቲያን፤ የዞን ከፍተኛ አመራሮቹንም በዘመቻው ከአካል ጉዳት እስከ ህይወት መስዋዕትነት ድረስ ከፍለዋል ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን “ኢትዮጵያ ከትናንት የወሰድናት ብቻ ሳትሆን ለነገው ትውልድ ልንሰጥ በአደራ መልክ የተረከብናት ናትና ትናንት በተረከብንበት መንገድ ሳትጎዳ በተሻለ ቁመና ልናስረክብ ይገባናል፤ ለዚያም አሸባሪውን መዋጋት አለብን” ሲሉም ሀገር የማዳን ተግባሩ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መንግሥትን መቃወም ማለት ሀገርን እንዲፈርስ መተው አይደለም ሲሉም መንግሥትን የሚቃወሙና ሕወሓትን ለሚደግፉ ሌሎች አካላት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም፤ መንግሥትን እኛም እንቃወመዋለን፤ ሀገራችንን ግን አናስነካም ሲሉም ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መላው ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ የሃይማኖትና የተለያዩ ልዩነቶቻቸውን በመተው ልዩነትን ማስተናገድ የሚቻልባትን ሀገር ለማትረፍ ሁሉም ሀገሩን ለማስቀጠል የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉም ገልፀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: Christian Tadele, nama, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule