• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም”አቶ ክርስቲያን

November 9, 2021 10:29 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የተቃጣባትን የህልውና አደጋ ለመመከትና ሀገርን ለማስቀጠል እያንዳንዱ ዜጋ የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ገለጹ።

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እንደተናገሩት፤ አሸባሪው ሕወሓት ከምስረታው ጀምሮ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተፈጠረ ቡድን በመሆኑ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል የሚፈልግ ዜጋ ሁሉ ይህንን አሸባሪ ቡድን ግንባር ድረስ ሄዶ ሊፋለመው ይገባል።

አቶ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ከአሸባሪው ሕወሓት ውጪ በዓለም ታሪክ የመራትን ሀገር ለማጥፋት አልሞ የተነሳ የፖለቲካ ፓርቲ የለም። አሸባሪው የሕወሓት ቡድን በገሀድ ሀገርን የማፍረስ አላማን አንግቦ ኢትዮጵያን በማፈራረስ ወደ ትናንሽ መንደርነት የመቀየር ፍላጎት አለው።

አቶ ክርስቲያን አሸባሪ ቡድኑ ለህፃናት አረጋውያንና ለደከሙት እንዲሁም ለእንስሳትም ጭምር የማይራራ መሆኑን ገልፀው፤ ቡድኑን ማስወገድ ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑንም ጠቁመዋል።

አቶ ክርስቲያን ማንኛውም ህብረተሰብ አካባቢውን የመጠበቅ ሞራልያዊ መብት እንዳለው እንደሚያምኑ የጠቆሙ ሲሆን፤ ፓርቲያቸውም በዚህ ሀገርን የማዳን እንቅስቃሴ ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ፓርቲያቸው የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ለህልውና ዘመቻው መንግሥት ጥሪ ከማቅረቡ በፊት ጀምሮ በራሱ ተነሳሽነት እንደተሳተፈ የጠቆሙት አቶ ክርስቲያን፤ የዞን ከፍተኛ አመራሮቹንም በዘመቻው ከአካል ጉዳት እስከ ህይወት መስዋዕትነት ድረስ ከፍለዋል ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን “ኢትዮጵያ ከትናንት የወሰድናት ብቻ ሳትሆን ለነገው ትውልድ ልንሰጥ በአደራ መልክ የተረከብናት ናትና ትናንት በተረከብንበት መንገድ ሳትጎዳ በተሻለ ቁመና ልናስረክብ ይገባናል፤ ለዚያም አሸባሪውን መዋጋት አለብን” ሲሉም ሀገር የማዳን ተግባሩ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መንግሥትን መቃወም ማለት ሀገርን እንዲፈርስ መተው አይደለም ሲሉም መንግሥትን የሚቃወሙና ሕወሓትን ለሚደግፉ ሌሎች አካላት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም፤ መንግሥትን እኛም እንቃወመዋለን፤ ሀገራችንን ግን አናስነካም ሲሉም ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መላው ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ የሃይማኖትና የተለያዩ ልዩነቶቻቸውን በመተው ልዩነትን ማስተናገድ የሚቻልባትን ሀገር ለማትረፍ ሁሉም ሀገሩን ለማስቀጠል የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉም ገልፀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: Christian Tadele, nama, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule