• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም”አቶ ክርስቲያን

November 9, 2021 10:29 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የተቃጣባትን የህልውና አደጋ ለመመከትና ሀገርን ለማስቀጠል እያንዳንዱ ዜጋ የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ገለጹ።

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እንደተናገሩት፤ አሸባሪው ሕወሓት ከምስረታው ጀምሮ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተፈጠረ ቡድን በመሆኑ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል የሚፈልግ ዜጋ ሁሉ ይህንን አሸባሪ ቡድን ግንባር ድረስ ሄዶ ሊፋለመው ይገባል።

አቶ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ከአሸባሪው ሕወሓት ውጪ በዓለም ታሪክ የመራትን ሀገር ለማጥፋት አልሞ የተነሳ የፖለቲካ ፓርቲ የለም። አሸባሪው የሕወሓት ቡድን በገሀድ ሀገርን የማፍረስ አላማን አንግቦ ኢትዮጵያን በማፈራረስ ወደ ትናንሽ መንደርነት የመቀየር ፍላጎት አለው።

አቶ ክርስቲያን አሸባሪ ቡድኑ ለህፃናት አረጋውያንና ለደከሙት እንዲሁም ለእንስሳትም ጭምር የማይራራ መሆኑን ገልፀው፤ ቡድኑን ማስወገድ ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑንም ጠቁመዋል።

አቶ ክርስቲያን ማንኛውም ህብረተሰብ አካባቢውን የመጠበቅ ሞራልያዊ መብት እንዳለው እንደሚያምኑ የጠቆሙ ሲሆን፤ ፓርቲያቸውም በዚህ ሀገርን የማዳን እንቅስቃሴ ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ፓርቲያቸው የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ለህልውና ዘመቻው መንግሥት ጥሪ ከማቅረቡ በፊት ጀምሮ በራሱ ተነሳሽነት እንደተሳተፈ የጠቆሙት አቶ ክርስቲያን፤ የዞን ከፍተኛ አመራሮቹንም በዘመቻው ከአካል ጉዳት እስከ ህይወት መስዋዕትነት ድረስ ከፍለዋል ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን “ኢትዮጵያ ከትናንት የወሰድናት ብቻ ሳትሆን ለነገው ትውልድ ልንሰጥ በአደራ መልክ የተረከብናት ናትና ትናንት በተረከብንበት መንገድ ሳትጎዳ በተሻለ ቁመና ልናስረክብ ይገባናል፤ ለዚያም አሸባሪውን መዋጋት አለብን” ሲሉም ሀገር የማዳን ተግባሩ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መንግሥትን መቃወም ማለት ሀገርን እንዲፈርስ መተው አይደለም ሲሉም መንግሥትን የሚቃወሙና ሕወሓትን ለሚደግፉ ሌሎች አካላት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም፤ መንግሥትን እኛም እንቃወመዋለን፤ ሀገራችንን ግን አናስነካም ሲሉም ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መላው ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ የሃይማኖትና የተለያዩ ልዩነቶቻቸውን በመተው ልዩነትን ማስተናገድ የሚቻልባትን ሀገር ለማትረፍ ሁሉም ሀገሩን ለማስቀጠል የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉም ገልፀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: Christian Tadele, nama, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule