• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም”አቶ ክርስቲያን

November 9, 2021 10:29 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ከውስጥም ሆነ ከውጭ የተቃጣባትን የህልውና አደጋ ለመመከትና ሀገርን ለማስቀጠል እያንዳንዱ ዜጋ የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ገለጹ።

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እንደተናገሩት፤ አሸባሪው ሕወሓት ከምስረታው ጀምሮ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተፈጠረ ቡድን በመሆኑ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል የሚፈልግ ዜጋ ሁሉ ይህንን አሸባሪ ቡድን ግንባር ድረስ ሄዶ ሊፋለመው ይገባል።

አቶ ክርስቲያን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ከአሸባሪው ሕወሓት ውጪ በዓለም ታሪክ የመራትን ሀገር ለማጥፋት አልሞ የተነሳ የፖለቲካ ፓርቲ የለም። አሸባሪው የሕወሓት ቡድን በገሀድ ሀገርን የማፍረስ አላማን አንግቦ ኢትዮጵያን በማፈራረስ ወደ ትናንሽ መንደርነት የመቀየር ፍላጎት አለው።

አቶ ክርስቲያን አሸባሪ ቡድኑ ለህፃናት አረጋውያንና ለደከሙት እንዲሁም ለእንስሳትም ጭምር የማይራራ መሆኑን ገልፀው፤ ቡድኑን ማስወገድ ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑንም ጠቁመዋል።

አቶ ክርስቲያን ማንኛውም ህብረተሰብ አካባቢውን የመጠበቅ ሞራልያዊ መብት እንዳለው እንደሚያምኑ የጠቆሙ ሲሆን፤ ፓርቲያቸውም በዚህ ሀገርን የማዳን እንቅስቃሴ ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ፓርቲያቸው የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ለህልውና ዘመቻው መንግሥት ጥሪ ከማቅረቡ በፊት ጀምሮ በራሱ ተነሳሽነት እንደተሳተፈ የጠቆሙት አቶ ክርስቲያን፤ የዞን ከፍተኛ አመራሮቹንም በዘመቻው ከአካል ጉዳት እስከ ህይወት መስዋዕትነት ድረስ ከፍለዋል ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን “ኢትዮጵያ ከትናንት የወሰድናት ብቻ ሳትሆን ለነገው ትውልድ ልንሰጥ በአደራ መልክ የተረከብናት ናትና ትናንት በተረከብንበት መንገድ ሳትጎዳ በተሻለ ቁመና ልናስረክብ ይገባናል፤ ለዚያም አሸባሪውን መዋጋት አለብን” ሲሉም ሀገር የማዳን ተግባሩ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መንግሥትን መቃወም ማለት ሀገርን እንዲፈርስ መተው አይደለም ሲሉም መንግሥትን የሚቃወሙና ሕወሓትን ለሚደግፉ ሌሎች አካላት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ሀገርን ማዳን ማለትም መንግሥትን መደገፍ ማለት አይደለም፤ መንግሥትን እኛም እንቃወመዋለን፤ ሀገራችንን ግን አናስነካም ሲሉም ገልፀዋል።

አቶ ክርስቲያን መላው ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ የሃይማኖትና የተለያዩ ልዩነቶቻቸውን በመተው ልዩነትን ማስተናገድ የሚቻልባትን ሀገር ለማትረፍ ሁሉም ሀገሩን ለማስቀጠል የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉም ገልፀዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: Christian Tadele, nama, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule