• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ታሪካዊውን የተሃድሶ ጥረት” እናደንቃለን – ማይክ ፔንስ

July 27, 2018 09:30 pm by Editor 2 Comments

በአሜሪካ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካው ምክትል ፕሬዚዳንት ጋር መገናኘታቸውን ማምሻው ላይ የኋይት ሃውስ ጽህፈት ቤታቸው ባወጣው አጭር መግለጫ አስታውቋል። በአሁኑ ጊዜ እየተካሄደ ያለውን የተሃድሶ ጥረት እንደሚያደንቁ ሚስተር ፔንስ ተናግረዋል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ በትላንትናው ዕትም ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ከምክትል ፕሬዚዳንት ፔንስ ጋር እንደሚገናኙ በዘገበ ወቅት ግንኙነቱ ወሳኝና ጠቃሚ እንደሆነ መጥቀሱ ይታወሳል። ምክትል ፕሬዚዳንቱ ዶ/ር ዐቢይ “ሰብዓዊ መብቶችን በማክበር፣ የንግዱን ማኅበረሰብ ሁኔታ በማሻሻል እና ከኤርትራ ጋር ሰላም በመፍጠር ረገድ” እያካሄዱ ያሉትን ለውጥ በማድነቅ አገራቸው የተሃድሶ ለውጡን እንደምትደግፍ አረጋግጠዋል።

ከዚህ ሌላ ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ከዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክርስቲን ላጋርድ ጋር ተገናኝተዋል። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ አይ ኤም ኤፍ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ለመሥራት ያለውን ቁርጠኝነት በመግለጽ ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ከኤርትራ ጋር የደረሱት ስምምነት ለቀጣናው መረጋጋት በማምጣት አዎንታዊ ተጽዕኖ እንደሚያደርግ ያለውን ዕምነት ገልጾዋል።

አይ ኤም ኤፍ በነጻ “የሚሰጠው ምሳ” እንደሌለ የሚታወቅ ሲሆን የምዕራባውያን ድርጅቶች አገልጋይ ሎሌ የነበረው ሟቹ መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያን በነጻ ለዕርድ እንዳቀረበ ይታወሳል። በአስተሳሰብ፣ በዕውቀት፣ በጥበብ፣ በራዕይ፣ በአመለካከት፣ በባህርይና በኢትዮጵያዊነት ፍጹም ልዩ የሆኑትና ለውድድር በማይቀርብበት መልኩ እጅግ የላቁት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ከሚከተሉት አገራዊ መርህ አኳያ ተመሳሳይ ተግባር እንደማይፈጽሙ ይታመናሉ።  (ፎቶዎቹ የተወሰዱት ከዕልፍኝ አስከልካዩ አቶ ፍጹም አረጋ የትዊተር ገጽ ነው)

ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ከአይ ኤም ኤፍ ዋና ዳይሬክተር ክርስቲን ላጋርድ ጋር


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: abiy ahmed, Full Width Top, laggard, Middle Column, mike pence

Reader Interactions

Comments

  1. Lusif says

    July 28, 2018 08:10 pm at 8:10 pm

    One of my friend who had been angry, upset and frustrated for several years about Ethiopian politics after looking to the pictures above said: he completely is seeing a transformed ( of the previous officials ) human face. Dr. Abiy and his team of change must be miraculous plastic surgeons. This much people are exited. Really funny.

    Reply
  2. Tesfa says

    August 1, 2018 05:38 pm at 5:38 pm

    አማርኛ ቋንቋ ማለፊያ ቋንቋ ነው። እንዳበጁት ይበጃልና። በቅኔም/በግጥም/በወርቅና ሰም/በተረትና ምሳሌ እንዲሁም በሌሎቹ የንግግርና የጽሁፍ ዘይቤዎች ልብን ለማስተንፈስ ይመቻል። ትዝ ከሚለኝ አንድ ልጥቀስ።

    ቋት ላይሞላ ነገር ከላይ ታች ይሮጣል
    የአንዳንድ ሰው ቆዳ እየለፋ ያልፋል።
    (ከፈቃድ ተ/ማሪያም ስራዎች የተወሰደ)

    በኑሮ መባከንን በምዕራቡ ዓለም ለምትኖሩ አልነግራችሁም። ያው በሽታ ወደ ሃገር ቤት መጋባቱ ግን ያሳስባል። ጠ/ሚ አብይና አብረዋቸው ወደ አሜሪካ ያቀኑት ልኡካን በሰላም ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸው እፎይታ ነው። ይሁን እንጂ በዲሲ/በሎስ አንጀለስ ያዩትን ሚኒሶታ ከገጠማቸው የጠባብ ብሄተኞች የስብስብ ፓለቲካን ሲመለከቱ አብይም ሆነ ለማ ልባቸው ሳይዝን አይቀርም። በመሰረቱ ለአንዲት ሃገር የቆመ ህዝብ ለመሪው የሚያደርገው አቀባበል ሳይሆን “የኦሮሞ ፊስቲቫል” ነበር የሚመስለው። ተልካሾች ዛሬም የሚያስቡት በዚያው በቋንቋቸውና በዘራቸው ዙሪያ ብቻ ነው። እንደመር ያሉ ተገፍተው የኢትዮጵያ ባንዲራ ወደ ዳር ተጥሎ እኛን ብቻ ስሙ የተባለበት መድረክ ነበር። እኔ ይህን ትኢይንት በቴሌቪዝን እየተከታተልኩ አቶ ለማ በአማርኛ ሲናገር በኦሮምኛ እንዲሆን ሲጮሁ መስማት የመደመር ሃሳብ እንደሌላቸው ያመላክታል። በመሰረቱ ዶ/ር አቢይና ለማ ኦሮሞዎች ባይሆኑ ኑሮ ማለትም የሃገሪቱ መሪ ከትግራይ/ከአማራ ክልል/ከአፋር/ከሱማሌ ቢሆን ምን ያደርጉ ነበር ብሎ ማሰብንም ከግምት ማስገባት መልካም ነው። ገና ይቀረናል!
    ጠ/ሚ አብይ ሰውን ሁሉ ሃገር ግቡ ማለታቸው ማለፊያ ሆኖ እያለ ለእኔ ግን የሚያሳስቡኝ አያሌ ነገሮች አሉ። በቅርቡ የሃገሪቱን አንጡራ ሃብት የሚፈስበት የዓባይ ግድም ሥራ አስፈጻሚ በጠራራ ጸሃይ በሃገሪቱ መዲና ተገለው ሲገኙ ምን ያህል ሃገሪቱ የወሮበሎች እንደሆነች ያሳያል። እንዴት ይህን ያህል ሃላፊነት የተጣለበት ሰው ያለ ጠባቂ ይንቀሳቀሳል? የሃገር ውስጥ ገዳዮች እንኳን ባይሆኑ የውጭ ጠላቶች ፕሮጀክቱን ለማዳከም የሚፈጽሙት ደባ ሊኖር ይችላል ብሎ ማሰብ ለምን አልተቻለም። በመሰረቱ ግድያው ሃገር በቀል ነው። ከዳንጎቴ የሲሚንቶ ፋብሪካ ሰራተኛ ሞት ጋር ተመሳሳይነትም አለው። ከየአቅጣጫው ወደ ሃገሪቱ ጥሪውን ሰምተው የሚገቡ የተቃዋሚም ሆነ የድሮ ባለስልጣኖች የደህንነት ዋስትና ያሰጋኛል። ከዚህም በዘለለ ጠበንጃ አንግተው ወያኔና ሥራውን ሲጋፈጡ የነበሩ የተናጠልም ሆነ የቡድን ሃይሎች ወያኔ ጥቃት እንዳያደርስባቸው ምን ጥንቃቄ ተደርጓል። ዝም ብሎ እንደመር እያሉ ሰውን አሰባስቦ ለሞት መዳረግም ተገቢ አይደለም። ዛሬ አፍቃሪ ወያኔ በሆኑ ድህረ ገጾች የምናነበው ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ነው። መሰረታዊ ጥንቃቄ ካልተደረገ የማይጠፋ እሳት ሊቀሰቅስ የሚችል ችግር ሊፈጠር ይችላል።
    ብሩህ በሆነ መልኩ ጠ/ሚ ሃገርና አንድነትን አስቀድመው በሃገርና በውጭ የሚያደርጉትን ጥረት አደንቃለሁ። በሃገሪቱ የረጅም ጊዜ ታሪክ በባህር ማዶ መሪዎቿ የሃገሬን ሰዎች ከእሥር ፍቱ በማለት ጠበቃ የቆምበት ጊዜ አልነበረም። ጠ/ሚ አብይና ለማ በእውን ለኢትዮጵያ አንድነትና ህብረት እንደቆሙ ምስክር አንሻም። ተግባራቸውና ቃላቸው በቂ ነውና! እኔም ከጎልጉል ድህረ ገጽ ተበድሬ ““ታሪካዊውን የተሃድሶ ጥረት” አደንቃለሁ። በየጊዜው የሚገደሉት ወገኖቻችን ደም ለፍትህ ይጮሃል። ገዳዮች ለፍርድ ይቅረቡ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule