• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች

February 13, 2023 03:28 am by Editor Leave a Comment

እሁድ የካቲት 5 ቀን 2015ዓም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን የስንዴ ምርት ወደ ውጭ የመላክ መርሃግብር በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን አስጀመሩ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ትኩረቱን በሰላም፣ ልማትና ብልፅግና ላይ በማድረግ የበለፀገችና ለሌሎች የምትተርፍ ሀገር ለማየት እንዲተጋም ጥሪ አቅርበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመርሃግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ባሌ ላይ ያየነው ስንዴን ኤክስፖርት የማድረግ ሂደት ለኢትዮጵያ ማድረግ ከሚገባን ትንሹ ስኬት ነው ብለዋል።

የምናደርገውንና የምናቅደውን በተግባር በአረንጓዴ አሻራና በህዳሴ ግድብ እያሳየን መጥተናል፤ አሁን ደግሞ ስንዴን ከውጭ ከማስገባት ከማቆም ባለፈ ወደ ውጭ በመላክ ያሰብነውን በተግባር ፈፅመን ለኢትዮጵያዊያንና ለዓለም አሳይተናል ነው ያሉት።

በዚህም ኢትዮጵያ ከስንዴ እርዳታ መላቀቅና ወደ ውጭ መላክ አትችሉም ያሉንን ችለን በማሳየታችን ኩራት ተሰምቶናል ብለዋል።

ለዚህ ስኬት የኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ ሌሎች ክልሎችም በክረምት፣ በበልግና የበጋ መስኖ ልማት ጉልህ አበርክቶ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።

በተለይም የኦሮሚያ፣ የሶማሌ እና የአማራ ክልሎች ሰፊ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ላይ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ250 ሚሊዮን በላይ እርዳታ ፈላጊዎች መኖራቸውን በመጥቀስ “ኢትዮጵያን ኤይድ” በሚል ስንዴ ለመለገስ ተግተን እንሰራለን ነው ያሉት።

በዓለም ላይ የተፈጠረውን የስንዴ ገበያ ችግር ለማቃለልም ኢትዮጵያ የበኩሏን እንደምትወጣ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ትኩረቱን በሰላም፣ ልማትና ብልፅግና ላይ በማድረግ የበለፀገችና ለሌሎች የምትተርፍ ሀገርን ለማየት እንዲተጋም ጥሪ አቅርበዋል።

የሚያጋጥሙ ችግሮችን በስሜት ሳይሆን በምክክርና በማስተዋል እየፈታን ለሀገር መስራት አለብን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግስት ህዝቡን ከድህነት ለማላቀቅ ከሚሰራው ስራ ባሻገር ለዘመናት ተከማችቶ የቆየውን የእዳ ጫና የማቃለል ትልቅ ህልም ይዞ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በመሆኑም የኢትዮጵያን የስንዴና ሌሎች የኤክስፖርት ምርቶች በማሳለጥ ልማቷን በማፋጠን ጠንካራና የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን ብለዋል።

“ኢትዮጵያ ያሰበችውን ከማሳካት ሊያቆማት የሚችል እንደሌለ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በወንድማማችነት፣ እየተመካከርን፣ እየተደማመጥን በጋራ የሀገራችንን ህልም ማሳካት አለብን ነው ያሉት።

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሺመልስ አብዲሳ፤ ባለፉት አራት ዓመታት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሰነቁት ሀሳብ መሠረት በስንዴ ምርት እራስን ከመቻል እስከ ኤክስፖርት ማድረግ ታቅዶ በመሰራቱ ሰፊ ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል።

በኦሮሚያ ክልል በዘንድሮው ዓመት 10 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ለውጭ ገበያ ዝግጁ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በክረምት ይለማ ከነበረው 800 ሺህ ሄክታር መሬት በአሁኑ ወቅት 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ሄክታር መድረሱን በመጥቀስ በ7 ሺህ ሄክታር መሬት የተጀመረው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዘንድሮው በጀት ዓመት 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር ለማልማት ወደ ሥራ መገባቱን ገልፀዋል።

የክልሉ ህዝብ ስንዴን ኤክስፖርት በማድረግ ታሪክ መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ፤ የኢትዮጵያ ስንዴ ኤክስፖርት የማድረግ ህልም በህይወት እያሉ በመሳካቱ ኩራት እንደተሰማቸው ገልጸዋል።

ሀገራዊ ለወጡን ተከትሎ መንግስት ስንዴን በስፋት በማምረት በአጭር ጊዜ ከውጭ የሚገባ ስንዴን በሀገር ውስጥ ምርት መተካቱን ጥቀሰዋል።

የስንዴ ምርት እና የምግብ ፍጆታ ሚዛን ታይቶ ከሀገሪቱ ፍጆታ የሚተርፍ 32 ሚሊዮን ኩንታል ትርፍ እንደሚኖር በመረጋገጡ በዚህ ዓመት ስንዴን ወደ ውጭ የመላክ ስራ በይፋ ተጀምሯል ብለዋል።

ለዚህም ዘንድሮ ሱዳንና ኬንያን ጨምሮ ስንዴ የመግዛት ፍላጎት ያላቸው ስድስት አገራት ጋር የ3 ሚሊዮን ኩንታል የውል ስምምነት ተፈርሟል ነው ያሉት። (ኢዜአ)

በኦክስፎርድ የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት “ችጋር” ለሚለው ቃል ኢትዮጵያን እንደ ምሳሌ መጥቀሱ በርካታዎችን ያሳዘነና አንገት ያስደፋ ነበር። ታሪክ ተቀይሮ ከችጋር መጠሪያነት ወደ ስንዴ ላኪነት የተቀየረችው ኢትዮጵያ በጸረ ኮሎኒያሊዝም ትግል ፋና ወጊ እንደነበረችው በዚህም መስክ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት ምሳሌ እንደምትሆን ይጠበቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Ethiopian Wheat Export, famine, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule