• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦኤምኤን ሕጋዊ ክስ ተከፈተበት፤ ለጊዜውም ሊታገድ ይችላል

July 14, 2020 09:14 am by Editor 2 Comments

በአሜሪካ አገር በትርፍ አልባ ድርጅትነት የተቋቋመውና ለበርካታዎች ሕይወት መጥፋትና ንብረት መውደም ተጠያቂ ነው የሚባለው ኦኤምኤን (የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ) ክስ ተመሥርቶበታል። ከሚዲያው ጋር ታደለ ኪታባ (የሚዲያው ሹም እንደመሆኑ)፤ እንዲሁም አያንቱ በከቾ በግል የክስ ተመሥርቶባቸዋል።

ክሱን ያቀረቡት ጥበበ ሳሙኤል ፈረንጅ እንደሚሉት ይህ ፋይል የማስከፈት ዓይነት ተግባር ነው እንጂ በትክክል በዐቃቤ ሕግ ጥፋተኛ ናቸው ተብሎ ክስ አልተመሠረተባቸውም። የጉዳዩ ባቤት የሆኑት አቶ ጥበበ ሳሙኤል እንዲህ ይላሉ፤

ከበርካታ ሰዎች እና የሚድያ አውታሮች፤ ‘OMN and its employees are Charged in District Court የሚል የዜና ዘገባ እየተራገበ መሆኑ እና እንዳብራራ ጥያቄ እየተጠየቅኩ ነው። በአጭሩ ለማብራራት “they are sued not charged”.

ይህ ዜና እየሰራጨ ያለው በስሕተት ከሆነ ይታረም፤ ግን ህን ተብሎ፤ የምናደርጋቸውን ነገሮች ተአማኒነት ለማሳጣት ከሆነ ደግሞ አይሳካም። ስለዚህ በስህተት ይህን የምታሰራጩ፤ እባካችሁ እርማት አድርጉ።

ሃቁ የሚከተለው ነው።

በኦኤምን እና በሌሎች ሁለት ሰዎች ላይ ክስ ተመስርቷል፤ የተመሰረተው ክስ ግን፤ የፍትሃ ብሄር ክስ ነው በእንግሊዘኛው አጠቃቀም መሆን ያለበት “sued” እንጂ “charged” አይደለም፤ ምክንያቱም በአማርኛው ክስ/ክስ ቢሆንም፤ በእንግሊዝኛ አጠቃቀሙ ግን ይለያያል፤ “charge” የሚለ ቃል የሚሰራው፤ አቃቤ ሕግ በወንጀል ክስ ሲመሰረት ነው። ክሱን ስመሰርት፤ ፍርድ ቤቱን ከጠየኩት ጥያቄ አንዱ፤ ለሚኒሶታ የፌደራል አቃቤ ሕግ በኦኤሜን ላይ የወንጀል ምርመራ እንዲያደርግ ትእዛዝ ይሰጥ የሚለውን ይጨምራል።

አቶ ጥበበ ይህንን ከተናገሩ በኋላ በፍርድ ቤት ስለተከፈተው ጉዳይ ሲያስረዱ በፌስቡክ ገጻቸው እንዲህ ብለዋል።

በመጀመሪያ ለትብብር እና ድጋፋችሁ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ይህ ግን ገና አንድ ስንዝር የተሄደበት መንገድ እንጂ ብዙ ይቀረናል። አሁን ካለብኝ የሥራ ውጥረት፤ ብዙ ነገር አልልም። ግን በጥቂቱ፤ ሂደቱን ልግለጽ። ይህ የተመሰረተው ክስ፤ የፍትሃ ብሔር ክስ ነው። ይህም ማለት ከግለሰብ ጉዳት ጋር በተያያዘ የቀረበ ክስ ነው። አንድ ሰው፤ በፍትሃ ብሔር፤ ለመክሰስ፤ መክሰስ የሚችልበት የግል ጉዳት ማሳየት ይኖርበታል፤ ከሳሹ legal standing ሊኖርው ይገባል፤ ይህም ክስ የተመሰረተው ይህንን legal standing በሚያሟላ መልኩ ነው።

የኮረና ቫይርሰ ጉዳይ ባይኖር ኖሮ፤ በተለይ፤ ክሱ እስኪታይ፤ አሁን ለፍርድ ቤቱ ባቀረብኩት መጠነኛ መረጃ መሰረት፤ ተከሳሾቹ፤ በምንም ሚድያ የጥላቻ፤ እና የጥፋት መልዕክታቸውን እንዳያስተላልፉ፤ ትላንትናውኑ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ሰምቶ፤ ጊዜያዊ እገዳ ትላንትናውኑ ያስተላልፍ ነበር፤ ግን በኮሮና ምክንያት፤ በስልክ ቀጠሮ ተሰጥቶ ጉዳዩ ስለሚሰማ፤ የተወሰነ ጊዜ መውሰዱ አልቀረም።

ይህ ጊዜያዊ እገዳ ከተጣለ፤ ለ20 ቀን ብቻ የሚቆይ ይሆናል ከዛ በፊት፤ ግን የፍርድ ቤት ክርክር ይደረግ እና በቂ መረጃ አቅርቤ ፍርድ ቤቱን ማሳመን ከቻልኩ፤ አጠቃላይ ክሱ እስኪታይ እና ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ፤ ተከሳሾቹ፤ ለጊዜው የጥላቻ መልዕክታቸውን እንዳያስተላልፉ ይታገዳሉ። ክሱን ካሸነፍኩ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ይታገዳሉ። ሂደቱ ይህን ይመስላል።

ክሱን በጥቅሉ ካሸነፍኩ፤ በተከሳሾቹ ላይ ፍርድ ቤቱ እንዲወስን የጠየኳቸው በጥቂቱ፤

(1) የገንዘብ ካሳ እንዲከፍሉ፤

(2) ንብረታቸው ተሽጦ እና ከህዝብ ያሰባሰቡት ገንዘብ ተነጥቆ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ጉዳት ለደረሰባቸው ካሳ እንዲከፍል፤ ለዚህም ፍርድ ቤቱ ትረስቲ እንዲመድብ፤

(3) በሚኒሶታ ለሚገኘው የፌደራል አቃቤ ህግ በተከሳሾቹ ላይ የወንጀል ምርመራ እንዲያካሂድ ትዕዛዝ እንዲሰጥ፤

(4) ተከሳሾሹ በIRS ኦዲት እንዲደረጉ፤ የሚሉ እና ሌሎችም ይገኙባቸዋል።

በኢሜልም በቴክስትም፤ በሌላም መንገድ ልታገኙኝ የሞከራችሁ አላችሁ። ቀደም ብዬ እንዳልኩት፤ በጣም የተወጣጠረ የስራ ሁኔታ ላይ ስላለሁ፤ በቶሎ መልስ ስለማልሰጣችሁ ቅር እንዳትሰኙ፤ በትህትና እጠይቃለሁ፤ መረጃ በማቀበል የተባበሩኝ 3 ሰዎች አሉ፤ ፍቃዳቸውን ጠይቄ ስማቸውን እገልፃለሁ።

ብዙዎች፤ ምን እንርዳ ብላችኋል፤ ከዚህ በፊትም የጠየኩት፤ አሁንም የምጠይቀው፤ የምታገኙትን መረጃ በኢሜሌ እንድትልኩልኝ፤ ነው፤ የኦሮሚፋ ቋንቋ መረጃ ያላችሁ፤ አስተርጉማችሁ ብትሰጡኝ፤ ይቀለኛል። ለትብብራችሁ አመሰግናለሁ። ቸሩ እግዚአብሔር ሃገራችንን እና ሕዝባችንን ይጠብቅ። ጊዜ ሲፈቅድልኝ፤ በበለጠ አብራራለሁ። tibebefsamuel@gmail.com

የእንግሊዝኛው መረጃ እንዲህ ይነበባል።

Today 07/13/2020, a civil suit against the following defendants commenced IN THE UNITED STATES DISTRICT COURT FOR THE DISTRICT OF MARYLAND

1. OromiaMedia Network (OMN)

2. PrincipalOfficer: Taddele M. Kitaba (in his OMN official capacity); AND

3. Ayantu Bekecho, in her personal capacity(individually);

The defendants, in this case, have violated 18 U.S.Code § 956, 18 U.S. Code § 878, and 26 USC Code § 501 (c). Each of these statutes provides an independent basis for entering the requested preliminary injunction. The OMN is served this lawsuit 5minutes ago through its email. This Posting is to let the defendants know that a lawsuit against them filed and to let them know to contact me to get the documents filed in court. Because EMERGENCY MOTION FOR A PRELIMINARY INJUNCTION OR Temporary Restraining Order is filed, the defendants have the legal right to present their defense. To get the document, contact me at: tibebefsamuel@gmail.com.

This posting is required by the district court as part of the legal process to get the documents to the defendants as soon as possible since the defendants are residents of the State of Minnesota.

The lawsuit in part indicates: “Pursuant to Rule 65 of the federal rules of Civil Procedure, Plaintiff Tibebe Samuel move for preliminary relief against Defendants OMN, Ayantu Bekecho, in her personal capacity, and Taddele M. Kitaba, (together, the “Defendants”), their agents, servants, employees, and attorneys, directing Defendants to stop and terminate their broadcasting services on TV, and all Social media platforms and deliveries of their message and services, mode of deliveries of their messages, fundraising activities and support services they provide to the Ethiopian community at large anywhere in the world, their direct broadcast and service to Ethiopia; and most of all to stop broadcasting any hateful messages, messages that call for the assassination of high government officials and well-known personalities in Ethiopia, the killing of any individual and any member of any ethnic group and the burning and destruction of properties in Ethiopia. In support thereof, the Plaintiff state as follows: ………”

Tibebe F. Samuel (aka Tibebe SamuelFerenji)

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: chilot, jawar, omn, ችሎት

Reader Interactions

Comments

  1. Gi Haile says

    July 16, 2020 01:48 pm at 1:48 pm

    በማንኛውም መመዘኛ ኦ .ኤም. ኤን የሚያስተላልፈው ዜናና የቃለ መጠይቆች እንግዶቻቸው ስኘ ስርዓት የጎደለው ተማሩ ከሚባሉ ሰዎች የማይጠበቅ የወደቀ፣የረከሰና የተበላሸ ኣስተያየቶች በሙሉ የጥላቻ ዘመቻ ነው። በተለይም በአገሪቱ መንግሰት መሪ በጠቅላይ ምኒስትር ዶ/ረ ኣቢይን የሚሳደብ የሚያዋርድ ግላዊ ጦርነት ነው። የአገር መሪ መስደብ እጅግ ፀያፍ ነገር ነው ለትውልድ የምናስተላልፈውን ንግግሮች ትውልዱን ጎዳቸው ወደፊትሞ ጥሩ ያልሆነ ምሳሌ ነው።

    Reply
  2. Tazabihaile says

    July 19, 2020 11:26 am at 11:26 am

    Ethiopian embassy in US should be helping him.Also we should help him financially a gofund me account need to be setip.Thank you Tibebe for taking this action
    DC resident Ethiopian wake up and help him.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule