• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም

June 17, 2020 06:57 am by Editor Leave a Comment

ለዚህ ሃሳብ ማብራሪያ የሰጡት የህወሓት ሊቀ መንበርና የትግራይ ክልል መንግሥት ምክትል ርዕስ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ውይይቱ የተናጠል ሳይሆን ሁሉንም አካላት ማካተት እንዳለበት መናገራቸውን ጠቅሷል።

“የውውይት መድረክ መፈጠር ካለበት፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ድርጅቶች፣ ብሔር ብሔረሰቦችን የሚወክሉ ፌደራሊስት ኃይሎች የሚሳተፉበት አገራዊ መድረክ መዘጋጀት አለበት እንጂ ከህወሓት/ትግራይ መንግሥት ጋር በድብቅ የሚደረግ ውይይት አንቀበልም፤ ትርጉምም አያመጣም” ማለታቸውን ቢሮው ገልጿል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ “ውይይቱ በመጨረሻ ሰዓት የተጀመረ ቢሆንም መሞከሩ ግን ጥሩ ነው” ያሉ ሲሆን ጨምረውም “የአገሪቱን ችግር ለመፍታት የሚንቀሳቀስ አካል ችግሩ የተፈጠረው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ በአገሪቱ አምባገናናዊ ሥርዓት ለመገንባት እየተሯሯጠ በሚገኘው ብልፅግና የተሰኘው ቡድንና የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እንጂ በፌደራል መንግሥትና በትግራይ ክልል መካከል ብቻ የተፈጠረ አለመግባባት አድርጎ መመልከት አይገባም” ብለዋል።

የሐይማኖት አባቶቹና የአገር ሽማግሌዎች ስለጦርነት አላስፈላጊነት መስበካቸውና ስለሰላምና ውይይት መናገራቸው ልክ መሆኑን ያመለከቱት ደብረፅዮን (ዶ/ር)፣ ነገር ግን “ይህ መባል ያለበት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማክበር ምርጫ አድርጋለሁ ባለው ክልል ላይ የጦር አዋጅ ለሚያውጀው የፌደራል መንግስት ነው” ሲሉ ከሰዋል።

በዛሬው የሽምግልና ውይይት ላይ ስለተነሱ ጉዳዮች በተለይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ባነሷቸው ጉዳዮች ላይ አተኩሮ መግለጫ ያወጣው የትግራይ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ እንዳለው፤ መፍትሔ ለማምጣት ተፈልጎ ከሆነ ቢያንስ በክልሉ የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ሌሎችም መሳተፍ እንደነበረባቸው መናገራቸውን ገልጿል።

ከዚሁ በተጨማሪም የመገናኛ ብዙሃን እንዳይገባ የተፈለገበት ምክንያትም ልክ እንዳልሆነ ተናግረዋል የተባሉት ደብረፅዮን (ዶ/ር) “ወደፊትም ቢሆን መደባበቁ ችግሩ ሊያባብሰው ካልሆነ መፍትሄ አይሆንም” ብለዋል።

በውይይቱ ወቅት በርካታ ጥያቄዎችና ሃሳቦች ከተሳታፊዎቹ ለሽምግልና ቡድኑ መቅረቡ የተነገረ ሲሆን፤ እነሱም የተነሱ ጉዳዮችን ይዘው ወደ ፌደራሉ መንግሥት እንደሚቀርቡ ተናግረዋል ሲል የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ መግለጫ ጠቅሷል።

BBC

Filed Under: Left Column, News, Slider, Uncategorized

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule