• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለሕገወጡ የትግራይ ምክር ቤትና ካቢኔ የፌዴራል በጀት ድጎማ ተከለከለ

October 7, 2020 10:18 am by Editor 4 Comments

በህገወጥ መንገድ የተቋቋመ ነው ላለው የትግራይ ክልል ምክር ቤት እና ካቢኔ የፌዴራል መንግሥት የበጀት ድጎማ እንደማያደርግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት እና ከፍተኛው የህግ አስፈፃሚ አካል (ካቢኔ) ህገመንግሥታዊ ቅቡልነት የላቸውም ያለው ምክር ቤቱ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ምንም ዓይነት ህጋዊ ግንኙነት ማድረግ እንደማይችሉ ገልጿል፡፡

ተቋማቱ የክልሉን ከፍተኛ ስራ አስፈፃሚ አካላት እንደ ህጋዊ አካል በመቁጠር ደብዳቤ መፃፃፍ፣ መረጃ መላላክ፣ ድጋፎች ማድረግ፣ በፌዴራል ደረጃ በሚካሄዱ መድረኮች ላይ ማሳተፍ እንደማይችሉም ነው የምክር ቤቱ አፈ-ጉባዔ አቶ አደም ፋራህ የተናገሩት፡፡

በአንጻሩ የክልሉ ህዝብ መሰረታዊ የልማትና የአገልግሎት ተጠቃሚነቱ እንዳይስተጓጎል እንደ ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ከተማ ካሉ ህጋዊ የክልሉ መዋቅሮች ጋር ብቻ ግንኙነት እንደሚደረግ እና ይህም በሚዋቀር ኮሚቴ ክትትል እንደሚደረግ አፈ-ጉባዔው በተለይ ለኢቲቪ አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ ውሳኔ ሊደረስ የቻለው የትግራይ ክልል መንግሥትና ገዥው ፓርቲ ህውሃት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ባከበረ መልኩ የሥራ ዘመኑ በምክር ቤቱ ውሳኔ የተራዘመውን የክልሉን ምክር ቤት የህግ አስፈፃሚ አካል ወደ ቦታው መመለስ ስላልቻሉ ነው ብለዋል አፈ ጉባኤው፡፡

ውሳኔው የትግራይ ህዝብ ኢ-ህገመንግሥታዊ አካሄድ እየተከተለ ባለ ቡድን ምክንያት ከሰላም፣ ልማትና መሰረታዊ አገልግሎት አንፃር እንዳይጎዳና የትግራይ ህዝብ እንደሌሎች የአገራችን ህዝቦች መሰረታዊ የልማትና የደህንነት አገልግሎቶች እንዲያገኙ ታስቦ መተላለፉንም አመልክተዋል፡፡

“ይሄ ሊሆን የቻለው ለትግራይ ህዝብ ካለን ክብር ነው” ያሉት አቶ አደም “ህዝብም እንደ ሌሎች የአገራችን ህዝቦች ሊያገኘው የሚገባውን ጥቅም ሊከበርለት ይገባል ከሚል ጽኑ እምነት የመነጨ ነው” ሲሉም ተናግረዋል፡፡

የውሳኔ አፈፃፀምም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥናት ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል ተብሏል፡፡

በቀጣይ በክልሉ ካሉ የከተማ አስተዳደሮች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት በተለይ ህዝቡ ማግኘት የሚገባውን መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲያገኝ በጥናት ተመስርቶ ተፈፃሚ ይደረጋልም ተብሏል፡፡

በወረርሽኙ ምክንያት የ6ኛውን ሃገራዊ ምርጫ መራዘም በመቃወም የራሱን ክልላዊ ምርጫ ያደረገው የትግራይ ክልል ህገ መንግሥቱን በብቸኝነት እንዳከበረ በመግለጽ ከመስከረም 25 በኋላ የፌዴራሉ መንግስት ህጋዊ የስልጣን ዘመን እንደሚያበቃ እና እውቅና የሚሰጠው የፌዴራል መንግሥት እንደማይኖር ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡

ይህ የድጎማ በጀቱን የተመለከተው ውሳኔ በፌዴራሉ እና በክልሉ መንግሥት መካከል ያለውን ውጥረት ይበልጥ እንደሚያከረው ይጠበቃል፡፡ (EBC)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: tigray tplf election, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    October 7, 2020 04:47 pm at 4:47 pm

    ሕወኣት የተካነው አዳዲስ ችግሮችን መፍጠር እንጂ ችግር መፍተት ችሎታቸው መለስ ዜናዊ ከሞተ በኋላ ራዕያቸውም አብሮ ተቀብሮሃል። ምሁራኖቻቸውም ፈፈሪዎች የውሳኔ ኣቋም የሌላቸው የጥቅም እንጅ ሕጋዊነትን የሚያከብሩ ለሠሆኑ ይህ ውጥረት የግትርነት በሕሪይ ውጤት ነው።

    Reply
  2. shiferaw berkineh says

    October 8, 2020 07:29 am at 7:29 am

    መንግስት ትክክለኛ ውሳኔ ወስኗል።የትግራይ ህዝብ በቀበሌ በሚገኙ ሹማምንቶቹ አማካኝነት ማንኛውንም አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ።

    Reply
  3. ዘረ-ያዕቖብ says

    October 10, 2020 07:26 am at 7:26 am

    Under Mereja:
    ” የ5,000 ሜትር ሪከርድን ስፔን፣ ቫሌንሽያ ላይ ከሰበረችው አትሌት ለተሰንበት ግደይ ጋር ያደረግኩት አጭር ቃለ-መጠይቅ! Elias Meseret
    – በመጀመርያ እንኳን ደስ አለሽ፣ ወደ ጥያቄዬ ስገባ፣ በአንቺ ስም እና ፎቶ የተከፈተ የፌስቡክ ገፅ ብዙ መረጃዎችን እያወጣ ነው። በአንድ ግዜ የተከታዮቹ ቁጥር ከ18,000 በልጧል፣ ይህ በእርግጥ የአንቺ ነው?–
    አትሌት ለተሰንበት>> እኔ ምንም አይነት የፌስቡክም ሆነ የሌላ ሶሻል ሚድያ ተጠቃሚ አይደለሁም፣ ሌላው ቀርቶ ስልክ እንኳን በአሰልጣኜ ነው የምጠቀመው፣ እንደምታውቀው አሁን እራሱ የማወራህ በሱ (ሀይሌ) ስልክ ነው። እኔ ሙሉ ትኩረቴ አትሌቲክስ ላይ ብቻ ነው። አንድ የፌስቡክ ገፅ ሰሞኑን እኔ ያላልኩትን ነገር እያወጣ እንደሆነ ሰምቻለሁ፣ አዝኛለሁም። ይህ ደስ አይልም፣ የሚፃፈው ነገር ሞራል ሊነካ ይችላል። ለህዝብ የእኔ እንዳልሆነ አሳውቅልኝ፣ ምንም የሶሻል ሚድያ አካውንት የለኝም።–
    – ቦሌ ኤርፖርት ያጋጠመሽ ነገር ምን ነበር?
    –አትሌት ለተሰንበት>> ያጋጠመኝ ነገር ያን ያህል ከባድ የሚባል ችግር አልነበረም፣ አሰልጣኜ (ሀይሌ) ነበር ሲያናግራቸው የነበረው። በሗላ አትሌት ደራርቱ መጥታ ችግሩ ተፈቷል፣ በቃ ይሄው ነው።
    –– አሁን የ5,000 ሜትር ሪከርድ ሰብረሻል፣ ቀጣይ ውጤት ምን እንጠብቅ?–
    አትሌት ለተሰንበት>> የአሁኑ ውጤት ትልቅ ብርታት ሆኖኛል ስለዚህ በቀጣይ ነገሮች ከተመቻቹ የ10,000 ሜትር ሪከርድን መስበር እፈልጋለሁ፣ እሱን ማሳካት ቀጣይ እቅዴ ነው።”

    እንዴት ነው ነገሩ ሁሉ? በሰላማውያን ተጋሩ ላይም ቦሌ ላይ ልዩነት ተጀመረ እንዴ? “ዘመንያ ግርምቢጥስ ማይ ንዓቐብ” እንዳይሆን አደራ…!

    Reply
  4. Worqu Belayeneh says

    October 10, 2020 11:44 am at 11:44 am

    This should be only the first step. Others should follow, such as: (a) cut-off of fuel supply, (b) cut-off of foreign exchange to banks serving TPLF conglomerates, (c) selectively cutting electricity and telephone/Internet services, (d) going after EFORT to pay loans that were forgiven/written off when TPLF was in control, (e) confiscating properties in Addis Abeba that do not have registered/legal owners but most probably owned by TPLF and associates.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule