• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለሕገወጡ የትግራይ ምክር ቤትና ካቢኔ የፌዴራል በጀት ድጎማ ተከለከለ

October 7, 2020 10:18 am by Editor 4 Comments

በህገወጥ መንገድ የተቋቋመ ነው ላለው የትግራይ ክልል ምክር ቤት እና ካቢኔ የፌዴራል መንግሥት የበጀት ድጎማ እንደማያደርግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት እና ከፍተኛው የህግ አስፈፃሚ አካል (ካቢኔ) ህገመንግሥታዊ ቅቡልነት የላቸውም ያለው ምክር ቤቱ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ምንም ዓይነት ህጋዊ ግንኙነት ማድረግ እንደማይችሉ ገልጿል፡፡

ተቋማቱ የክልሉን ከፍተኛ ስራ አስፈፃሚ አካላት እንደ ህጋዊ አካል በመቁጠር ደብዳቤ መፃፃፍ፣ መረጃ መላላክ፣ ድጋፎች ማድረግ፣ በፌዴራል ደረጃ በሚካሄዱ መድረኮች ላይ ማሳተፍ እንደማይችሉም ነው የምክር ቤቱ አፈ-ጉባዔ አቶ አደም ፋራህ የተናገሩት፡፡

በአንጻሩ የክልሉ ህዝብ መሰረታዊ የልማትና የአገልግሎት ተጠቃሚነቱ እንዳይስተጓጎል እንደ ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ከተማ ካሉ ህጋዊ የክልሉ መዋቅሮች ጋር ብቻ ግንኙነት እንደሚደረግ እና ይህም በሚዋቀር ኮሚቴ ክትትል እንደሚደረግ አፈ-ጉባዔው በተለይ ለኢቲቪ አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ ውሳኔ ሊደረስ የቻለው የትግራይ ክልል መንግሥትና ገዥው ፓርቲ ህውሃት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ባከበረ መልኩ የሥራ ዘመኑ በምክር ቤቱ ውሳኔ የተራዘመውን የክልሉን ምክር ቤት የህግ አስፈፃሚ አካል ወደ ቦታው መመለስ ስላልቻሉ ነው ብለዋል አፈ ጉባኤው፡፡

ውሳኔው የትግራይ ህዝብ ኢ-ህገመንግሥታዊ አካሄድ እየተከተለ ባለ ቡድን ምክንያት ከሰላም፣ ልማትና መሰረታዊ አገልግሎት አንፃር እንዳይጎዳና የትግራይ ህዝብ እንደሌሎች የአገራችን ህዝቦች መሰረታዊ የልማትና የደህንነት አገልግሎቶች እንዲያገኙ ታስቦ መተላለፉንም አመልክተዋል፡፡

“ይሄ ሊሆን የቻለው ለትግራይ ህዝብ ካለን ክብር ነው” ያሉት አቶ አደም “ህዝብም እንደ ሌሎች የአገራችን ህዝቦች ሊያገኘው የሚገባውን ጥቅም ሊከበርለት ይገባል ከሚል ጽኑ እምነት የመነጨ ነው” ሲሉም ተናግረዋል፡፡

የውሳኔ አፈፃፀምም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥናት ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል ተብሏል፡፡

በቀጣይ በክልሉ ካሉ የከተማ አስተዳደሮች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት በተለይ ህዝቡ ማግኘት የሚገባውን መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲያገኝ በጥናት ተመስርቶ ተፈፃሚ ይደረጋልም ተብሏል፡፡

በወረርሽኙ ምክንያት የ6ኛውን ሃገራዊ ምርጫ መራዘም በመቃወም የራሱን ክልላዊ ምርጫ ያደረገው የትግራይ ክልል ህገ መንግሥቱን በብቸኝነት እንዳከበረ በመግለጽ ከመስከረም 25 በኋላ የፌዴራሉ መንግስት ህጋዊ የስልጣን ዘመን እንደሚያበቃ እና እውቅና የሚሰጠው የፌዴራል መንግሥት እንደማይኖር ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡

ይህ የድጎማ በጀቱን የተመለከተው ውሳኔ በፌዴራሉ እና በክልሉ መንግሥት መካከል ያለውን ውጥረት ይበልጥ እንደሚያከረው ይጠበቃል፡፡ (EBC)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: tigray tplf election, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. GI Haile says

    October 7, 2020 04:47 pm at 4:47 pm

    ሕወኣት የተካነው አዳዲስ ችግሮችን መፍጠር እንጂ ችግር መፍተት ችሎታቸው መለስ ዜናዊ ከሞተ በኋላ ራዕያቸውም አብሮ ተቀብሮሃል። ምሁራኖቻቸውም ፈፈሪዎች የውሳኔ ኣቋም የሌላቸው የጥቅም እንጅ ሕጋዊነትን የሚያከብሩ ለሠሆኑ ይህ ውጥረት የግትርነት በሕሪይ ውጤት ነው።

    Reply
  2. shiferaw berkineh says

    October 8, 2020 07:29 am at 7:29 am

    መንግስት ትክክለኛ ውሳኔ ወስኗል።የትግራይ ህዝብ በቀበሌ በሚገኙ ሹማምንቶቹ አማካኝነት ማንኛውንም አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ።

    Reply
  3. ዘረ-ያዕቖብ says

    October 10, 2020 07:26 am at 7:26 am

    Under Mereja:
    ” የ5,000 ሜትር ሪከርድን ስፔን፣ ቫሌንሽያ ላይ ከሰበረችው አትሌት ለተሰንበት ግደይ ጋር ያደረግኩት አጭር ቃለ-መጠይቅ! Elias Meseret
    – በመጀመርያ እንኳን ደስ አለሽ፣ ወደ ጥያቄዬ ስገባ፣ በአንቺ ስም እና ፎቶ የተከፈተ የፌስቡክ ገፅ ብዙ መረጃዎችን እያወጣ ነው። በአንድ ግዜ የተከታዮቹ ቁጥር ከ18,000 በልጧል፣ ይህ በእርግጥ የአንቺ ነው?–
    አትሌት ለተሰንበት>> እኔ ምንም አይነት የፌስቡክም ሆነ የሌላ ሶሻል ሚድያ ተጠቃሚ አይደለሁም፣ ሌላው ቀርቶ ስልክ እንኳን በአሰልጣኜ ነው የምጠቀመው፣ እንደምታውቀው አሁን እራሱ የማወራህ በሱ (ሀይሌ) ስልክ ነው። እኔ ሙሉ ትኩረቴ አትሌቲክስ ላይ ብቻ ነው። አንድ የፌስቡክ ገፅ ሰሞኑን እኔ ያላልኩትን ነገር እያወጣ እንደሆነ ሰምቻለሁ፣ አዝኛለሁም። ይህ ደስ አይልም፣ የሚፃፈው ነገር ሞራል ሊነካ ይችላል። ለህዝብ የእኔ እንዳልሆነ አሳውቅልኝ፣ ምንም የሶሻል ሚድያ አካውንት የለኝም።–
    – ቦሌ ኤርፖርት ያጋጠመሽ ነገር ምን ነበር?
    –አትሌት ለተሰንበት>> ያጋጠመኝ ነገር ያን ያህል ከባድ የሚባል ችግር አልነበረም፣ አሰልጣኜ (ሀይሌ) ነበር ሲያናግራቸው የነበረው። በሗላ አትሌት ደራርቱ መጥታ ችግሩ ተፈቷል፣ በቃ ይሄው ነው።
    –– አሁን የ5,000 ሜትር ሪከርድ ሰብረሻል፣ ቀጣይ ውጤት ምን እንጠብቅ?–
    አትሌት ለተሰንበት>> የአሁኑ ውጤት ትልቅ ብርታት ሆኖኛል ስለዚህ በቀጣይ ነገሮች ከተመቻቹ የ10,000 ሜትር ሪከርድን መስበር እፈልጋለሁ፣ እሱን ማሳካት ቀጣይ እቅዴ ነው።”

    እንዴት ነው ነገሩ ሁሉ? በሰላማውያን ተጋሩ ላይም ቦሌ ላይ ልዩነት ተጀመረ እንዴ? “ዘመንያ ግርምቢጥስ ማይ ንዓቐብ” እንዳይሆን አደራ…!

    Reply
  4. Worqu Belayeneh says

    October 10, 2020 11:44 am at 11:44 am

    This should be only the first step. Others should follow, such as: (a) cut-off of fuel supply, (b) cut-off of foreign exchange to banks serving TPLF conglomerates, (c) selectively cutting electricity and telephone/Internet services, (d) going after EFORT to pay loans that were forgiven/written off when TPLF was in control, (e) confiscating properties in Addis Abeba that do not have registered/legal owners but most probably owned by TPLF and associates.

    Reply

Leave a Reply to GI Haile Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ August 11, 2022 03:04 pm
  • በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ August 10, 2022 10:58 am
  • የስሪ ላንካው “FamilyCracy” – ከመዓቱ እስከ ተውኔቱ August 8, 2022 09:45 am
  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule