• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦብነግ፤ ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በሕዝብ ደም መቀለድ ነው!

December 3, 2019 07:12 pm by Editor Leave a Comment

በቀን 10/03/2012 ዓ.ም ተፅፎ በቁጥር 07642/2019 ወጪ የተደረገው አስገራሚ ደብዳቤ ይድረስ “ለህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ መቀሌ” በማለት ይጀምራል። ጉዳዩ፡- “ስለተጠራንበት ስብሰባ ይመለከታል” በማለት ይቀጥላል። የዚህን ደብዳቤ ትርጉምና ፋይዳ በቅጡ ለመረዳት የተፃፈበትን አውድ በአጭሩ መዳሰስ ያስፈልጋል።

በደብዳቤው ላይ ፊርማቸውን አኑረው የላኩት የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ዋና ሊቀመንበር አቶ አብዲርሃማን መሃመድ ናቸው። ከላይ እንደተገለፀው ዋና ጉዳዩ ሰሞኑን በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበላቸው ጥሪ የተሰጠ ምላሽ ነው። ህወሓት በመቀሌው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ጥሪ ያቀረበላቸው በሥልጣን ዘመኑ በአሸባሪነት የፈረጃቸው የኦብነግ አመራሮች ናቸው።

እንግዲህ በአካባቢው ያለውን የተፈጥሮ ነዳጅ አውጥቶ ለመሸጥ ሲል የኦጋዴንን ህዝብ ከምድረገፅ ለማጥፋት ሲሰራ የነበረው፤ ለዚሁ ዓላማ አልሸባብ የተባለ ቡድንን ያደራጀው፣ በሶማሌላንድ በኩል የጦር መሣሪያ እያቀበለ በእጅ አዙር ሀገሩን ያስወረረው፣ የኢትዮጵያን ወታደሮችን ለሞት እየገበረ በፀረ-ሽብር ትግል ስም ከአሜሪካን እና እንግሊዝ ዶላር ሲቀበል፣ በሰላም አስከባሪ ስም ደግሞ ከተባበሩት መንግሥታት ይቀፍል የነበረው ህወሓት…። ከቻይና የነዳጅ አፈላላጊ ድርጅት ጋር በመሆን የተፈጥሮ ነዳጅ ለማውጣት በኦጋዴ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ የፈፀመው፣ አብዲ ኢሌ የሚባል ንክ ከኤሌክትሪክ ፖል ላይ አውርዶ የሶማሌ ክልል ፕረዜዳንት አድርጎ የሾመው፣ የሶማሌ ህዝብን ለአስራ አምስት አመታት ያህል በመከላከያ ሠራዊት እና በሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እንደ ጠላት እያደነ ሲያስገድል የነበረው፤ ንፁሃንን ማሰርና መግደል በውስጡ ያለውን ሰይጣናዊ መንፈስ ማርካት ተስኖት እስር ቤት ውስጥ ጅብና ነብር አስሮ ሲያሰቃይ የነበረው፣… ያለ ምንም ሃፍረት፣ ፀፀት፣ ይቅርታ፣ ተጠያቂነት፣… በጠራው ስብሰባ መገኘት የሶማሌን ህዝብ ማዋረድ ነው። የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር ከህወሓት ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ የሰጠው ምላሽ ይህንን መራራ ሃቅ እንዲህ ሲል ገልፆታል፡- 

ኦብነግ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ በሰጠው ምላሽ ሊሰመርባቸው የሚገቡ ሦስት መሠረታዊ ነጥቦች አሉ። የመጀመሪያው ህወሓት ላለፉት 27 ዓመታት በሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት በንፁሃን ዜጎች ላይ ለፈጸመው ግፍና በደል ተጠያቂ ሊሆን ይገባል። ሁለተኛ በማንኛውም አግባብ ቢሆን ከህወሓት ጋር ትብብርና ጥምረት መፍጠር ላለፉት 27 ዓመታት ግፍና በደል በተፈፀመባቸው ዜጎች ደምና እምባ ላይ እንደመቀለድ ይቆጠራል። ሦስተኛ ከህወሓት ጋር በመተባበር የፌደራሊስቶች ግንባር ለመመሥረት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ግለሰቦች እና ቡድኖች ህወሓቶች ቀድሞ በፈፀሙት እና ወደፊት በሚፈፀሙት የወንጀል ተግባር ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳታፊ እንደመሆናቸው መጠን ከተጠያቂነት አያመልጡም። (ኢትዮ ዊኪ ሊክስ፤ https://t.me/ethiowikileaks1)

ደብዳቤው እንዲህ ይላል፤

ተጨማሪ፤ በተያያዘ ዜና ህወሓት የፌዴራሊስት ግምባር ለመመሥረት መቀሌ ደፋ ቀና እያለ ባለበት ወቅት ከጋበዛቸው ፓርቲዎችና ቡድኖች ግማሽ ያህሉ ብቻ የተገኙ ሲሆን አንጋፋዎቹና ተስፋ የተጣለባቸው ኦፌኮ፣ ኦነግ፣ … አልተገኙም፤ ኦብነግ አለመገኘት ብቻ ሳይሆን ከዚያ ይልቅ “የምንፈልጋት ኢትዮጵያ በ2032” በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ ላይ ተገኘቷል።  

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ህወሓት በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ የፈጸመውን ግፍ አስመልክቶ ከዚህ በፊት “ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት”፤ “አንዳችሁንም አናስተርፍም፤ እንጨርሳችኋልን” የህወሃት ነፍጠኞች – በሚል ርዕስ ዘገባ አውጥቶ ነበር። ነውር ጌጡ፤ ውርደት ቀለቡ የሆነው ህወሓት ይህንን ግፍ የት አስቀምጦ ይሆን “አሸባሪ” እያለ ሲጠራው የነበረውን ኦብነግ ለስብሰባ የጠራው? ሙሉ ዘገባውን እዚህ ላይ ማንበብ ይቻላል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: federalist meeting, Left Column, onlf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule