• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦብነግ፤ ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በሕዝብ ደም መቀለድ ነው!

December 3, 2019 07:12 pm by Editor Leave a Comment

በቀን 10/03/2012 ዓ.ም ተፅፎ በቁጥር 07642/2019 ወጪ የተደረገው አስገራሚ ደብዳቤ ይድረስ “ለህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ መቀሌ” በማለት ይጀምራል። ጉዳዩ፡- “ስለተጠራንበት ስብሰባ ይመለከታል” በማለት ይቀጥላል። የዚህን ደብዳቤ ትርጉምና ፋይዳ በቅጡ ለመረዳት የተፃፈበትን አውድ በአጭሩ መዳሰስ ያስፈልጋል።

በደብዳቤው ላይ ፊርማቸውን አኑረው የላኩት የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ዋና ሊቀመንበር አቶ አብዲርሃማን መሃመድ ናቸው። ከላይ እንደተገለፀው ዋና ጉዳዩ ሰሞኑን በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበላቸው ጥሪ የተሰጠ ምላሽ ነው። ህወሓት በመቀሌው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ጥሪ ያቀረበላቸው በሥልጣን ዘመኑ በአሸባሪነት የፈረጃቸው የኦብነግ አመራሮች ናቸው።

እንግዲህ በአካባቢው ያለውን የተፈጥሮ ነዳጅ አውጥቶ ለመሸጥ ሲል የኦጋዴንን ህዝብ ከምድረገፅ ለማጥፋት ሲሰራ የነበረው፤ ለዚሁ ዓላማ አልሸባብ የተባለ ቡድንን ያደራጀው፣ በሶማሌላንድ በኩል የጦር መሣሪያ እያቀበለ በእጅ አዙር ሀገሩን ያስወረረው፣ የኢትዮጵያን ወታደሮችን ለሞት እየገበረ በፀረ-ሽብር ትግል ስም ከአሜሪካን እና እንግሊዝ ዶላር ሲቀበል፣ በሰላም አስከባሪ ስም ደግሞ ከተባበሩት መንግሥታት ይቀፍል የነበረው ህወሓት…። ከቻይና የነዳጅ አፈላላጊ ድርጅት ጋር በመሆን የተፈጥሮ ነዳጅ ለማውጣት በኦጋዴ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ የፈፀመው፣ አብዲ ኢሌ የሚባል ንክ ከኤሌክትሪክ ፖል ላይ አውርዶ የሶማሌ ክልል ፕረዜዳንት አድርጎ የሾመው፣ የሶማሌ ህዝብን ለአስራ አምስት አመታት ያህል በመከላከያ ሠራዊት እና በሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እንደ ጠላት እያደነ ሲያስገድል የነበረው፤ ንፁሃንን ማሰርና መግደል በውስጡ ያለውን ሰይጣናዊ መንፈስ ማርካት ተስኖት እስር ቤት ውስጥ ጅብና ነብር አስሮ ሲያሰቃይ የነበረው፣… ያለ ምንም ሃፍረት፣ ፀፀት፣ ይቅርታ፣ ተጠያቂነት፣… በጠራው ስብሰባ መገኘት የሶማሌን ህዝብ ማዋረድ ነው። የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር ከህወሓት ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ የሰጠው ምላሽ ይህንን መራራ ሃቅ እንዲህ ሲል ገልፆታል፡- 

ኦብነግ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ በሰጠው ምላሽ ሊሰመርባቸው የሚገቡ ሦስት መሠረታዊ ነጥቦች አሉ። የመጀመሪያው ህወሓት ላለፉት 27 ዓመታት በሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት በንፁሃን ዜጎች ላይ ለፈጸመው ግፍና በደል ተጠያቂ ሊሆን ይገባል። ሁለተኛ በማንኛውም አግባብ ቢሆን ከህወሓት ጋር ትብብርና ጥምረት መፍጠር ላለፉት 27 ዓመታት ግፍና በደል በተፈፀመባቸው ዜጎች ደምና እምባ ላይ እንደመቀለድ ይቆጠራል። ሦስተኛ ከህወሓት ጋር በመተባበር የፌደራሊስቶች ግንባር ለመመሥረት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ግለሰቦች እና ቡድኖች ህወሓቶች ቀድሞ በፈፀሙት እና ወደፊት በሚፈፀሙት የወንጀል ተግባር ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳታፊ እንደመሆናቸው መጠን ከተጠያቂነት አያመልጡም። (ኢትዮ ዊኪ ሊክስ፤ https://t.me/ethiowikileaks1)

ደብዳቤው እንዲህ ይላል፤

ተጨማሪ፤ በተያያዘ ዜና ህወሓት የፌዴራሊስት ግምባር ለመመሥረት መቀሌ ደፋ ቀና እያለ ባለበት ወቅት ከጋበዛቸው ፓርቲዎችና ቡድኖች ግማሽ ያህሉ ብቻ የተገኙ ሲሆን አንጋፋዎቹና ተስፋ የተጣለባቸው ኦፌኮ፣ ኦነግ፣ … አልተገኙም፤ ኦብነግ አለመገኘት ብቻ ሳይሆን ከዚያ ይልቅ “የምንፈልጋት ኢትዮጵያ በ2032” በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ ላይ ተገኘቷል።  

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ህወሓት በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ የፈጸመውን ግፍ አስመልክቶ ከዚህ በፊት “ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት”፤ “አንዳችሁንም አናስተርፍም፤ እንጨርሳችኋልን” የህወሃት ነፍጠኞች – በሚል ርዕስ ዘገባ አውጥቶ ነበር። ነውር ጌጡ፤ ውርደት ቀለቡ የሆነው ህወሓት ይህንን ግፍ የት አስቀምጦ ይሆን “አሸባሪ” እያለ ሲጠራው የነበረውን ኦብነግ ለስብሰባ የጠራው? ሙሉ ዘገባውን እዚህ ላይ ማንበብ ይቻላል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: federalist meeting, Left Column, onlf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule