• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልደቱ የ98 ምርጫ ወቅት ከህወሓት ደኅንነት ሽጉጥ መቀበሉን ለፍርድ ቤት አመነ

August 10, 2020 06:23 pm by Editor Leave a Comment

ፍርድ ቤቱ አቶ ልደቱ አያሌው በህክምና ምክንያት ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ፥ መርማሪ ፖሊስ ለመጨረሻ ጊዜ ምርመራውን አጠናቆ እንዲቀርብ የሰባት ቀን ጊዜ ፈቅዷል።

በምስራቅ ሸዋ ዞን የቢሾፍቱ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ለሁለተኛ ጊዜ በቀረቡት አቶ ለደቱ አያሌው ላይ መርማሪ ፖሊስ በተሰጠው ተጨማሪ 14 ቀናት ጊዜ ውስጥ ያከናወናቸውን የምርመራ ስራዎች ገልጿል።

አቶ ልደቱ እጅ ላይ የተገኙ ሁለት ሽጉጦች እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እንዲሁም የተላላኳቸውን የስልክ መልዕክቶች በፎረንሲክ እያስመረመረ መሆኑን ተናግሯል።

በእጃቸው ላይ የኢትዮጵያ ህዳሴ እርቅና አንድነት የሽግግር መንግስት ማቋቋም የሚልና ሌሎች የፖለቲካ ሰነዶችን ማግኘቱን የገለፀው መርማሪ ፖሊስ በሰኔ 23 ቀን 2012 ዓመተ ምህረት የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ መንግስት ለመገልበጥ እቅድ ይዘው ከሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ጋር በቢሾፍቱ ሁከትና አመፅ እንዲፈጠር ሲቀሰቅሱ ነበሩ ብሎ እንደጠረጠራቸውና ለዚህም የምስክሮችን ቃል መቀበሉን ገልጿል።

ለጀመርኩት ምርመራ የፎረንሲክ ምርመራ ውጤት ለማምጣትና ተጨማሪ ሰነዶቸን ለማሰባሰብ 14 ቀን ይሰጠኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

አቶ ልደቱ ዛሬም በጠበቃ ያልተወከሉ ሲሆን፥ ፍርድ ቤቱ ለምን በጠበቃ እንዳልተወከሉ ለጠየቃቸው ጥያቄ ሁለት ጠበቆች ፍቃደኛ አለመሆናቸውን፤ አንድ ፍቃደኛ ቢያገኙም በዚሁ ሰዓት በሰበር ችሎት ቀጠሮ ስላለው እኔው ለዛሬ ልከራከር ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀው ፍርድ ቤቱም ፈቅዶላቸዋል።

በዚሁ መሰረት ፖሊስ ባቀረበው ምርመራ ላይ መቃወሚያ አሰምተዋል።

ሽጉጡን በተመለከተ 1998 ዓመተ ምህረት ላይ መንግስት ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት እንደሰጣቸው አንደኛው ሽጉጥ ደግሞ ከአባታቸው በውርስ ያገኙት እና ፍቃድ ያለው መሆኑን አስረድተዋል።

በ1998 ዓመተ ምህረት ማስፈራሪያዎች ይደርስባቸው ስለነበር በወቅቱ የነበረው መንግስት ችግሩ ሲያልፍ ትመልሳለህ ብሎ እንደሰጣቸው ነው ያስታወቁት።

ሰነዶቹንም በተመለከተ የፖለቲካ ጉዳዮች ሆነው በመገናኛ ብዙሃን እና በአደባባይ ሲገልጿቸው የነበሩ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልፀዋል።

ከዚህ በፊት ከነበረኝ ቀጠሮ ጋር ተመሳሳይ የሆነ መርመራ ነው የቀረበው፤ አዲስ አልቀረበም በማለት ተጨማሪ ጊዜ ለመርማሪ ፖሊስ ሊሰጥ አይገባም ሲሉ ተቃውመዋል።

በፈረንጆቹ ነሃሴ 6 የልብ ቀዶ ጥገና ምርመራ ለማድረግ እሁድ ወደ አሜሪካ ለመብረር ትኬት ቆርጠው አርብ እለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀው፥ አሁንም የልብ ህክምና ያሰጋኛል የፖሊስ ጣቢያው ውስጥም ማስክ ሳያደርጉ ከመንገድ ላይ የሚያዙ ሰዎች ሳይመረመሩ እየገቡ ናቸው፤ ለኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተጋላጭ እንዳልሆን ስጋት አለኝ ሲሉ አቤቱታ አስመዝግበዋል።

ከዚህ በፊት የነበረው መንግስት አምስት ጊዜ አስሯቸው ነገር ግን ማስረጃ ስላልተገኘ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ የተናገሩት አቶ ልደቱ፥ አሁንም ማስረጃ ከተገኘብኝ ይጣራ በውጭ ሆኜ ህክምናዬን እንድከታተል ፍርድ ቤቱ የጤናዬን ሁኔታ ከግምት አስገብቶ በዋስ ይልቀቀኝ ሲሉ ጠይቀዋል።

ፖሊስ በበኩሉ ፖለቲካ ሳይሆን የወንጀል ጉዳይ ነው፤ እንደ ሀገር መንግስት ለመገልበጥ በተደረገ ሙከራ በቢሾፍቱ ወጣቶችን አደራጅተው አመፅና ሁከት በመቀስቀስ ነው የተጠረጠሩት፤ በመሆኑም ዋስትና ሊፈቀድ አይገባም ሲል ተቃውሟል።

ጉዳዩን የተከታተለው ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ከዛሬ ጀምሮ አቶ ልደቱ በሀገር ውስጥ የልብ ህክምና ማእከል ህክምና እንዲያገኙ እንዲያደርግ አዟል።

የወረርሽኙን ሁኔታ በተቻለ መጠን ጥንቃቄ እንዲደረግላቸው ያዘዘው ፍርድ ቤቱ፥ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ እንዲቀርብ የመጨረሻ ሰባት ቀን ጊዜ ፈቅዶለታል። (ምንጭ፤ ፋና)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: chilot, jawar massacre, lidetu ayalew, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule