• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ መልቀቂያ አላቀረቡም!!

December 6, 2019 03:34 pm by Editor 4 Comments

ዜናው የውሸት ነው

ለሥራ ወደ አሜሪካ ያቀኑት የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ የሥልጣን መልቀቂያ ማስገባታቸውን ጠቅሶ ፋኑኤል ክንፉ ፈንታሌ በሚባለው የግል የዩቲዩብ ገጹ በድምጽ ያሰራጨው ዜና ከእውነት የራቀ መሆኑ ተጠቆመ። 

“የፈንታሌ ሚዲያ ምንጮች” እንደነገሩት ያስታወቀው ፋኑኤል ክንፉ ዜናው እውነት እንደሆነ አድርጎ ለማሳየት የተጠቀመው አቶ ለማ ለቪኦኤ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ነው። 

ለአቶ ለማም ሆነ በኦሮሚያ ጉዳይ እጅግ ቅርብ የሆኑ የሚዲያ ውጤቶች ለጊዜው ምንም ያላሉበትን ጉዳይ ፋኑኤል ምንጮቹን ጠቅሶ ይህንን አነጋጋሪ ዜና ትናትን ሌሊት (በአዲስ አበባ አቆጣጠር) ላይ መለጠፉ አነጋጋሪ ሆኗል። 

ዛሬ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የመከላከያ ሚኒስትርን ጠቅሶ እንዳለው ከሆነ የአቶ ለማ የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ የሚታወቅ አይደለም። የኤፒው ኤሊያስ መሠረትም የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ አነጋግሮ በተመሳሳይ አቶ ለማ መልቀቂያ ስለማቅረባቸው የሚታወቅ ነገር እንደሌለ አረጋግጦ ዜናውን “ፌክ” በማለት በፌስቡክ ገጹ አሰራጭቷል። ዜናው ሃሰተኛ ቢሆንም ይህ እስከታተመበት ድረስ ፋኑኤል ማስተባበያ አላቀረበም።

በሻኪሶ የወርቅ ማዕድን ማውጪያ አካባቢ ሚድሮክ ላደረሰው የጤና ችግር ተቃውሞ በገጠመው ወቅት በአንድ አፍታ ሚዲያ ላይ “ጃዋር እንዴት ሼኽ መሀመድ ሁሴን አላሙዲ ይታሰራሉ ይላል” በሚል በኦሮሞ አክቲቪስቶችና ልሂቃን ክፉኛ የተተቸው ፋኑኤል ዜናውን ከኦሮሚያ ጉዳይ ውስጥ አዋቂ ሊያገኘው እንደማይችል፣ ይልቁኑም አካሄዱ የዲጂታል ወያኔ ስራ አስፈጻሚ ዓይነት መሆኑንን የሚያመላክት እንደሆነ ነው አቶ ሙክታር ሰይድ ለጎልጉል የገለጹት።  

በኦሮሚያ ጉዳይ የቅርብ መረጃ ያላቸው አቶ ሙክታር ከዚህ ያለፈ ማንነታቸው እንዳይጠቀስ ጠይቀው ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንዳሉት “ፋኑኤል ዜናውን በፍጹም ከኦሮሚያ ምንጮች ሊያገኝ አይችልም፣ ከሆነም በጣም ከራቀና ተባራሪ ወሬ ብቻ ሊሆን ነው የሚችለው፤ የዲጂታል ወያኔ ሥራ መሆኑን የሚያመላክቱ ብዙ ቅመሞች አሉበት፤ የሚገርመው ግን ህወሓቶች የብሔርብሔረሰቦች ጉዳይ ይመለከተናል እያሉ ለኦሮሞ ሕዝብ አዛኝ መስለው ሰሞኑን በመቀሌ እንደታየው ስንት እያወሩ ከአንዳንድ የኦሮሞ ኃይሎች ጋር እንሠራለን እያሉ በሌላ ወገን ደግሞ እንዲህ ዓይነቱን የመብት ረገጣ ይክዳሉ” ብለዋል።  

በመደመር ሃሳብ እንደማይስማሙ ያስታወቁት አቶ ለማ “ተሰሚነት ካጣሁ ቆይቻለሁ” ሲሉ በቪኦኤ በኩል ምሬት ማሰማታቸው ይታወሳል። የኦዲፒ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈቃዱ በበኩላቸው አማራጭ ሃሳብ ካላቸው ሁሌም በሩ ክፍት መሆኑንን አመልክተው “ሃሳባቸውን በነጻነት መግለጻቸው የአዲሱ አስተሳሰብ ውጤት በመሆኑ ደስ ሊለን ይገባል” ማለታቸው የሚታወስ ነው።

አቶ ለማ ይህ ዜና እስከታተመበት ድረስ መልቀቂያ ያላስገቡ ሲሆን እሳቸው የሚመሩት ጥላ የተሰኘው የኦሮሞ ድርጅቶች ጥምረት ከሌሎች የብሄረሰብ ነጻ አውጪ ግንባሮች ጋር በዛሬው ዕለት ግንባር ለመመሥረት መስማማቱ የአቶ ለማ መጨረሻ ምን ሊሆን ይችላል? የሚለውን ሃሳብ አጠንክሮታል።

ፋኑኤል ክንፉ ከዚህ በፊት በረከት ስምዖን በመሰረተውና በሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲን በጀት ይተዳደር በነበረው ሰንደቅ ጋዜጣ ምክትል አዘጋጅ በመሆን ጋዜጣው በበጀት ችግር እስከተዘጋበት ቀን ድረስ ሲሠራ እንደነበር ይታወቃል።

በሌላ ዜና ኢሌሌ ሆቴል በተደረገ ስብሰባ አስር ፓርቲዎች መቀላቀላቸውን ፋና ዘግቧል። ከኦሮሚያ አቶ ዳውድ የሚመሩት ኦነግ ሸኔ ብቻ ነው ያለበት። ከአስሩ ፓርቲዎች ውስጥ አራቱ ቀደም ሲል አጋር ክልል ውስጥ የሚገኙ የ“ነጻነት ታጋዮች” ሲሆኑ ሲዳማ ነጻነት ንቅናቄን ጨምሮ ሶስቱ ከደቡብ ክልል ናቸው። ከአማራ ክልል ቅማንትና አገው በሸንጎና በፓርቲ ስም የተደራጁ ይገኙበታል። አቶ ዳውድ ውህደቱን አስመልክቶ ንግግር ሲያደርጉ በፈቃደኛነት የተከናወነ ሲሉ አሞግሰዋል።

ድርጅቶቹም

1) የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)

2) የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ)

3) የአፋር ህዝቦች ነፃነት ፓርቲ ፣

4) የሲዳማ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ፣

5) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ

6) የጋምቤላ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ

7) የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

8) የአገው ሀገር አቀፍ ሸንጎ

9) የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና

10) የካፋ አረንጓዴ ፓርቲ ናቸው።

አቶ ለማ የሚመሩት ጥላ የተሰኘው የኦሮሞ ድርጅቶች ኅብረት አሁን በተፈጸመው ግንባር ዙሪያ ያለው አቋም አልታወቀም። የግንባሩ የመጨረሻ ራእይም ይፋ አልሆነም። አዲስ ተመሠረተ በተባለው ግንባሩ ውስጥ አቶ ዳውድ የሚመሩት ኦነግ መገኘቱ ቀጣዩ ጨዋታ ምን ይሆን የሚል ጥያቄ አስነስቷል።

ከዐሥሩ ድርጅቶች በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው በጣም ጥቂቶቹ ሲሆኑ በአዲሱ የምርጫ ቦርድ የፓርቲዎች ምዝገባ ሥነሥርዓት መሠረት ተገቢውን የአባላት ፊርማ አሰባስበው ዕውቅና ለማግኘት የሚበቁት ምን ያህሉ እንደሆነ ሌላው አጠያያቂ ጉዳይ ሆኗል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: digital woyane, Full Width Top, lemma megerssa, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    December 7, 2019 08:15 pm at 8:15 pm

    We know know TPLF is the source behind the fabrication that Obo Lema ,submitted a letter of resignation.The main strategy for TPLf for disseminating this rubish, according Ethio-codes and Tolosa Ibsa is that. After the official statment of Obo Lema,TPLF sensed there is a frictaion between Lema and Abiy,and is in the process of planning a serious of sabotages aimed at assassinating Ethiopian officials,including Obo Lema.

    TPLF ,in collaboration with Ezekiel Gebisa,Daud Ibsa,Jwar Mohamed,Tesgaye Ararasa, has reached a deal in Mekele conference.One of the agreement of that conference is that plan an assassination aginst Obo Lema. Then,blame this on the regime and use it as a means to agitate the Oromo people for uprising against P.M Abiy.

    In other words, precipitate such a crisis within the reform team,mobilize the Oromos for anti Abiay protest,and use this occasion to usurp illegitimate power in collaboration with its junior partner the OLF. OLF is apolitical jackass that will not hesitate to bargain on the life of one of the beloved citizen. This dreamers will never leave the Ethiopian people alone so long they are given ample room to continue their dirty politics of stabilizing he nation.

    Reply
    • Aman Kidane says

      December 8, 2019 10:36 pm at 10:36 pm

      Brother,
      How old are you? Why you write such trush comment.

      Reply
  2. Baba says

    December 10, 2019 07:56 am at 7:56 am

    Tesfa!
    Your analysis or opinion is illogical, incoherent and out of this world. To hate TPLF is one thing but to conclude to ridiculous conclusion entirely different. Lemma and abiy are two sides of the same coin, they may disagree on somethings and that is natural. Also the other personalities you mentioned are within their rights to associate with whomever they wish and prefer. This is what is called personal freedom. The fear and doubts we endured under TPLF rule is gone. One thing you should understand is OLF is an organization and an idea as well . Oromos love the idea of freedom that OLF the organization enunciated many years ago.

    Reply
    • Tesfa says

      December 13, 2019 02:38 am at 2:38 am

      Actually my opinion far from being illogical ,i sense, it generates surprise response from you. Lema’s interview with VOA,while he was conducting an official business was out of protocol than your assertion, “the differences between the two is minor”. Beside, the Mekele gathering which reportedly spent $14 million in expense for the entertainment of TPLF’s friends,mainly for drink, hotel and other luxury items while the people of Tegrie are in dire straight.

      And you said those who traveled to Mekele were ,”Exercising their personal freedom”.The Mekele conference is a discussion on how to conduct political subversion , with the participants involved against the reform team.As far as I know the decadent OLF was out of fortune since iat has nothing going for her after it spent decades immured in Asmara.Until the day team Lema traveled to Asmara and offered them a face saving means to enter Ethiopia.Ever since it entered through Bole Airport,it has been desperate for power. And this desperation, has led it to employ multiple means.

      One of it is to launch OLF Shane to be armed and financed through bank robbery,forced tax levy from merchants who work in Oromo and material support gained from TPLF. while the notorious Abatorbe is terrorizing the Oromos in to submission,by eliminating ODP members and police officers within Oromo.

      Two,use the OMN propagandists J.M,Ezekiel Gebisa,,Tesgaye Ararasa in cooperation with TPLF to spin revisionist ideas, to promote a forum favorable for TPLF come back.I am just calling the OLF a spade. And there is no such a thing of freedom of assembly,when OLF sympathizers assemble with TPLF to devise a means, how to remove a legitimate government.

      Not to mention the fact there is no such a thing as two centers of power in Ethiopia. TPLF can not continue to play two cards.She has to make up her mind between cessation or to stick around.That means,before any thing else, she has to settle this issue for once and for all with the people of Tegria. And the Ezkiel group if they have issue against the governme,nt they must address it in Ethiopia, thn to go to Tegrie to join a subversive movement.I can only say this the time has come any one that travels to Mekele be it the OMN propagandists or any paid cadre to choose either Mekele as his /her center or Addis. They can not have it both ways.If they insist both means we want them to be locked up.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule