• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ መልቀቂያ አላቀረቡም!!

December 6, 2019 03:34 pm by Editor 4 Comments

ዜናው የውሸት ነው

ለሥራ ወደ አሜሪካ ያቀኑት የመከላከያ ሚኒስትር ለማ መገርሳ የሥልጣን መልቀቂያ ማስገባታቸውን ጠቅሶ ፋኑኤል ክንፉ ፈንታሌ በሚባለው የግል የዩቲዩብ ገጹ በድምጽ ያሰራጨው ዜና ከእውነት የራቀ መሆኑ ተጠቆመ። 

“የፈንታሌ ሚዲያ ምንጮች” እንደነገሩት ያስታወቀው ፋኑኤል ክንፉ ዜናው እውነት እንደሆነ አድርጎ ለማሳየት የተጠቀመው አቶ ለማ ለቪኦኤ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ነው። 

ለአቶ ለማም ሆነ በኦሮሚያ ጉዳይ እጅግ ቅርብ የሆኑ የሚዲያ ውጤቶች ለጊዜው ምንም ያላሉበትን ጉዳይ ፋኑኤል ምንጮቹን ጠቅሶ ይህንን አነጋጋሪ ዜና ትናትን ሌሊት (በአዲስ አበባ አቆጣጠር) ላይ መለጠፉ አነጋጋሪ ሆኗል። 

ዛሬ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የመከላከያ ሚኒስትርን ጠቅሶ እንዳለው ከሆነ የአቶ ለማ የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ የሚታወቅ አይደለም። የኤፒው ኤሊያስ መሠረትም የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ አነጋግሮ በተመሳሳይ አቶ ለማ መልቀቂያ ስለማቅረባቸው የሚታወቅ ነገር እንደሌለ አረጋግጦ ዜናውን “ፌክ” በማለት በፌስቡክ ገጹ አሰራጭቷል። ዜናው ሃሰተኛ ቢሆንም ይህ እስከታተመበት ድረስ ፋኑኤል ማስተባበያ አላቀረበም።

በሻኪሶ የወርቅ ማዕድን ማውጪያ አካባቢ ሚድሮክ ላደረሰው የጤና ችግር ተቃውሞ በገጠመው ወቅት በአንድ አፍታ ሚዲያ ላይ “ጃዋር እንዴት ሼኽ መሀመድ ሁሴን አላሙዲ ይታሰራሉ ይላል” በሚል በኦሮሞ አክቲቪስቶችና ልሂቃን ክፉኛ የተተቸው ፋኑኤል ዜናውን ከኦሮሚያ ጉዳይ ውስጥ አዋቂ ሊያገኘው እንደማይችል፣ ይልቁኑም አካሄዱ የዲጂታል ወያኔ ስራ አስፈጻሚ ዓይነት መሆኑንን የሚያመላክት እንደሆነ ነው አቶ ሙክታር ሰይድ ለጎልጉል የገለጹት።  

በኦሮሚያ ጉዳይ የቅርብ መረጃ ያላቸው አቶ ሙክታር ከዚህ ያለፈ ማንነታቸው እንዳይጠቀስ ጠይቀው ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንዳሉት “ፋኑኤል ዜናውን በፍጹም ከኦሮሚያ ምንጮች ሊያገኝ አይችልም፣ ከሆነም በጣም ከራቀና ተባራሪ ወሬ ብቻ ሊሆን ነው የሚችለው፤ የዲጂታል ወያኔ ሥራ መሆኑን የሚያመላክቱ ብዙ ቅመሞች አሉበት፤ የሚገርመው ግን ህወሓቶች የብሔርብሔረሰቦች ጉዳይ ይመለከተናል እያሉ ለኦሮሞ ሕዝብ አዛኝ መስለው ሰሞኑን በመቀሌ እንደታየው ስንት እያወሩ ከአንዳንድ የኦሮሞ ኃይሎች ጋር እንሠራለን እያሉ በሌላ ወገን ደግሞ እንዲህ ዓይነቱን የመብት ረገጣ ይክዳሉ” ብለዋል።  

በመደመር ሃሳብ እንደማይስማሙ ያስታወቁት አቶ ለማ “ተሰሚነት ካጣሁ ቆይቻለሁ” ሲሉ በቪኦኤ በኩል ምሬት ማሰማታቸው ይታወሳል። የኦዲፒ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈቃዱ በበኩላቸው አማራጭ ሃሳብ ካላቸው ሁሌም በሩ ክፍት መሆኑንን አመልክተው “ሃሳባቸውን በነጻነት መግለጻቸው የአዲሱ አስተሳሰብ ውጤት በመሆኑ ደስ ሊለን ይገባል” ማለታቸው የሚታወስ ነው።

አቶ ለማ ይህ ዜና እስከታተመበት ድረስ መልቀቂያ ያላስገቡ ሲሆን እሳቸው የሚመሩት ጥላ የተሰኘው የኦሮሞ ድርጅቶች ጥምረት ከሌሎች የብሄረሰብ ነጻ አውጪ ግንባሮች ጋር በዛሬው ዕለት ግንባር ለመመሥረት መስማማቱ የአቶ ለማ መጨረሻ ምን ሊሆን ይችላል? የሚለውን ሃሳብ አጠንክሮታል።

ፋኑኤል ክንፉ ከዚህ በፊት በረከት ስምዖን በመሰረተውና በሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲን በጀት ይተዳደር በነበረው ሰንደቅ ጋዜጣ ምክትል አዘጋጅ በመሆን ጋዜጣው በበጀት ችግር እስከተዘጋበት ቀን ድረስ ሲሠራ እንደነበር ይታወቃል።

በሌላ ዜና ኢሌሌ ሆቴል በተደረገ ስብሰባ አስር ፓርቲዎች መቀላቀላቸውን ፋና ዘግቧል። ከኦሮሚያ አቶ ዳውድ የሚመሩት ኦነግ ሸኔ ብቻ ነው ያለበት። ከአስሩ ፓርቲዎች ውስጥ አራቱ ቀደም ሲል አጋር ክልል ውስጥ የሚገኙ የ“ነጻነት ታጋዮች” ሲሆኑ ሲዳማ ነጻነት ንቅናቄን ጨምሮ ሶስቱ ከደቡብ ክልል ናቸው። ከአማራ ክልል ቅማንትና አገው በሸንጎና በፓርቲ ስም የተደራጁ ይገኙበታል። አቶ ዳውድ ውህደቱን አስመልክቶ ንግግር ሲያደርጉ በፈቃደኛነት የተከናወነ ሲሉ አሞግሰዋል።

ድርጅቶቹም

1) የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)

2) የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ)

3) የአፋር ህዝቦች ነፃነት ፓርቲ ፣

4) የሲዳማ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ፣

5) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ

6) የጋምቤላ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ

7) የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

8) የአገው ሀገር አቀፍ ሸንጎ

9) የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና

10) የካፋ አረንጓዴ ፓርቲ ናቸው።

አቶ ለማ የሚመሩት ጥላ የተሰኘው የኦሮሞ ድርጅቶች ኅብረት አሁን በተፈጸመው ግንባር ዙሪያ ያለው አቋም አልታወቀም። የግንባሩ የመጨረሻ ራእይም ይፋ አልሆነም። አዲስ ተመሠረተ በተባለው ግንባሩ ውስጥ አቶ ዳውድ የሚመሩት ኦነግ መገኘቱ ቀጣዩ ጨዋታ ምን ይሆን የሚል ጥያቄ አስነስቷል።

ከዐሥሩ ድርጅቶች በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው በጣም ጥቂቶቹ ሲሆኑ በአዲሱ የምርጫ ቦርድ የፓርቲዎች ምዝገባ ሥነሥርዓት መሠረት ተገቢውን የአባላት ፊርማ አሰባስበው ዕውቅና ለማግኘት የሚበቁት ምን ያህሉ እንደሆነ ሌላው አጠያያቂ ጉዳይ ሆኗል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: digital woyane, Full Width Top, lemma megerssa, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    December 7, 2019 08:15 pm at 8:15 pm

    We know know TPLF is the source behind the fabrication that Obo Lema ,submitted a letter of resignation.The main strategy for TPLf for disseminating this rubish, according Ethio-codes and Tolosa Ibsa is that. After the official statment of Obo Lema,TPLF sensed there is a frictaion between Lema and Abiy,and is in the process of planning a serious of sabotages aimed at assassinating Ethiopian officials,including Obo Lema.

    TPLF ,in collaboration with Ezekiel Gebisa,Daud Ibsa,Jwar Mohamed,Tesgaye Ararasa, has reached a deal in Mekele conference.One of the agreement of that conference is that plan an assassination aginst Obo Lema. Then,blame this on the regime and use it as a means to agitate the Oromo people for uprising against P.M Abiy.

    In other words, precipitate such a crisis within the reform team,mobilize the Oromos for anti Abiay protest,and use this occasion to usurp illegitimate power in collaboration with its junior partner the OLF. OLF is apolitical jackass that will not hesitate to bargain on the life of one of the beloved citizen. This dreamers will never leave the Ethiopian people alone so long they are given ample room to continue their dirty politics of stabilizing he nation.

    Reply
    • Aman Kidane says

      December 8, 2019 10:36 pm at 10:36 pm

      Brother,
      How old are you? Why you write such trush comment.

      Reply
  2. Baba says

    December 10, 2019 07:56 am at 7:56 am

    Tesfa!
    Your analysis or opinion is illogical, incoherent and out of this world. To hate TPLF is one thing but to conclude to ridiculous conclusion entirely different. Lemma and abiy are two sides of the same coin, they may disagree on somethings and that is natural. Also the other personalities you mentioned are within their rights to associate with whomever they wish and prefer. This is what is called personal freedom. The fear and doubts we endured under TPLF rule is gone. One thing you should understand is OLF is an organization and an idea as well . Oromos love the idea of freedom that OLF the organization enunciated many years ago.

    Reply
    • Tesfa says

      December 13, 2019 02:38 am at 2:38 am

      Actually my opinion far from being illogical ,i sense, it generates surprise response from you. Lema’s interview with VOA,while he was conducting an official business was out of protocol than your assertion, “the differences between the two is minor”. Beside, the Mekele gathering which reportedly spent $14 million in expense for the entertainment of TPLF’s friends,mainly for drink, hotel and other luxury items while the people of Tegrie are in dire straight.

      And you said those who traveled to Mekele were ,”Exercising their personal freedom”.The Mekele conference is a discussion on how to conduct political subversion , with the participants involved against the reform team.As far as I know the decadent OLF was out of fortune since iat has nothing going for her after it spent decades immured in Asmara.Until the day team Lema traveled to Asmara and offered them a face saving means to enter Ethiopia.Ever since it entered through Bole Airport,it has been desperate for power. And this desperation, has led it to employ multiple means.

      One of it is to launch OLF Shane to be armed and financed through bank robbery,forced tax levy from merchants who work in Oromo and material support gained from TPLF. while the notorious Abatorbe is terrorizing the Oromos in to submission,by eliminating ODP members and police officers within Oromo.

      Two,use the OMN propagandists J.M,Ezekiel Gebisa,,Tesgaye Ararasa in cooperation with TPLF to spin revisionist ideas, to promote a forum favorable for TPLF come back.I am just calling the OLF a spade. And there is no such a thing of freedom of assembly,when OLF sympathizers assemble with TPLF to devise a means, how to remove a legitimate government.

      Not to mention the fact there is no such a thing as two centers of power in Ethiopia. TPLF can not continue to play two cards.She has to make up her mind between cessation or to stick around.That means,before any thing else, she has to settle this issue for once and for all with the people of Tegria. And the Ezkiel group if they have issue against the governme,nt they must address it in Ethiopia, thn to go to Tegrie to join a subversive movement.I can only say this the time has come any one that travels to Mekele be it the OMN propagandists or any paid cadre to choose either Mekele as his /her center or Addis. They can not have it both ways.If they insist both means we want them to be locked up.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule