• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመሬት ጋር በተያያዘ ጉቦኞች እጅ ከፍንጅ እየተያዙ ነው

September 3, 2020 01:52 pm by Editor Leave a Comment

በጉለሌ ክፍለከተማ ከመሬት ጋር በተያያዘ አገልግሎት ለማግኘት ወደ መስሪያ ቤቱ የሄዱ ተገልጋዮችን ጉዳይ እናስፈጽማለን በሚል ጉቦ ሲቀበሉ የተገኙ ግለሰቦች በትላንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በወንጀል ድርጊቱ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ከክፍለከተማ እስከ ወረዳ ከተዘረጋው ሠንሠለት በተጨማሪ ደላሎችም ይገኙበታል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ከተገልጋዮቹ ጋር በመሆን ባደረገው ተከታታይ ክትትል ለአገልግሎት እንዲከፈላቸው የጠየቁትን ገንዘብ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ኅብረተሰቡም በህጋዊ መንገድ ማግኘት የሚችለውን አገልግሎት ገንዘብ በመቀበል በህገ-ወጥ መንገድ አገልግሎት የሚሰጡ የመንግስት አካላትን በማጋለጥ ግዴታውን እንዲወጣ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

የወንጀል ድርጊቱን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎች በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ በኩል ለህዝብ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል።

በሌላ በኩል ኤፍሬም አለሙ የተባለ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 03 አስተዳደር የግንባታ ፍቃድ ጽኅፈት ቤት ሃላፊ ለተገልጋይ ህገ ወጥ የግንባታ ፍቃድ ለመስጠት በ140 ሺህ ብር ተዋውለው ተበዳዩ አልችለም በማለታቸው 60ሺ ግን ሊቀብል ሲል እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡

ባለጉዳዩ ለከንቲባ ጽ/ቤት እና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባደረሰው ጥቆማ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር በተደረገ ክትትል የጽህፈት ቤት ሃላፊውን ገንዘቡን ሲቀበል በቁጥጥር ስር መዋሉን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወንጀል ክትትል ሃላፊ ኮማደር አወሉ አህመድ ተናግረዋል፡፡

ይህ መረጃ ከተሰማ በኋላ ፖሊስ ተጨማሪ መረጃ ሰጥቷል፥….

ኤፍሬም አለሙ የተባለው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 03 አስተዳደር የግንባታ ፍቃድ ጽኅፈት ቤት ሃላፊ ለተገልጋይ ህገ ወጥ የግንባታ ፍቃድ ለመስጠት 140 ሺህ ብር ሲቀበል እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 3 አስተዳደር የግንባታ ፈቃድ ቁጥጥር ሃላፊ የሆነው ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋለው ዛሬ ነሃሴ 27 ቀን 2012 ዓም ነው፡፡

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ተወካይ ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው እንዳስረዱት ዶ/ር አድል አብደላ የተባሉት የግል ተበዳይ በረንዳ ለመስራት ፈልገው ወደ ወረዳው በመሄድ የግንባታ ፈቃድ ጠይቀው ከተፈቀደላቸው በኋላ ግንባታ ጀምረው ነበር፡፡

ይሁን እንጂ የአስተዳደሩ የቁጥጥር ሰራተኞች ወደ ግንባታው ስፍራ በመሄድ በተፈቀደው መሰረት ሳይሆን ከዚያ ውጪ እየተገባ እንደሆነ በመግለፅ እና በተጀመረው መንገድ መቀጠል ካስፈለገ የግል ተበዳይ 150 ሺህ ብር እንዲሰጡ መጠየቃቸውን ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው ተናግረዋል፡፡

የግል ተበዳይ ግን 150 ሺህ ብር የለኝም ሲሉ ወደ 80 ሺህ ብር ዝቅ እንደተደረገላቸው እና ከዚያ በኋላ ሁኔታውን ለፖሊስ ማሳወቃቸውን የጠቀሱት ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው 80ሺህ ብር እንደሌላቸውም በአካልም በስልክም ተገናኝተው ከተደራደሩ እና በ60 ሺህ ብር ከተስማሙ በኋላ ተጠርጣሪው ብሩን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡

በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን እና ማህበራዊ ትስስር ገፆች ተጠርጣሪው የተቀበለው ገንዘብ 140 ሺህ ብር እንደሆነ ተደርጎ የተገለፀው ስህተት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው ጠቅሰዋል። (የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድርና ፖሊስ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Social Tagged With: addis ababa land grab

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule