• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከመሬት ጋር በተያያዘ ጉቦኞች እጅ ከፍንጅ እየተያዙ ነው

September 3, 2020 01:52 pm by Editor Leave a Comment

በጉለሌ ክፍለከተማ ከመሬት ጋር በተያያዘ አገልግሎት ለማግኘት ወደ መስሪያ ቤቱ የሄዱ ተገልጋዮችን ጉዳይ እናስፈጽማለን በሚል ጉቦ ሲቀበሉ የተገኙ ግለሰቦች በትላንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በወንጀል ድርጊቱ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ከክፍለከተማ እስከ ወረዳ ከተዘረጋው ሠንሠለት በተጨማሪ ደላሎችም ይገኙበታል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ከተገልጋዮቹ ጋር በመሆን ባደረገው ተከታታይ ክትትል ለአገልግሎት እንዲከፈላቸው የጠየቁትን ገንዘብ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ኅብረተሰቡም በህጋዊ መንገድ ማግኘት የሚችለውን አገልግሎት ገንዘብ በመቀበል በህገ-ወጥ መንገድ አገልግሎት የሚሰጡ የመንግስት አካላትን በማጋለጥ ግዴታውን እንዲወጣ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

የወንጀል ድርጊቱን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎች በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ በኩል ለህዝብ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል።

በሌላ በኩል ኤፍሬም አለሙ የተባለ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 03 አስተዳደር የግንባታ ፍቃድ ጽኅፈት ቤት ሃላፊ ለተገልጋይ ህገ ወጥ የግንባታ ፍቃድ ለመስጠት በ140 ሺህ ብር ተዋውለው ተበዳዩ አልችለም በማለታቸው 60ሺ ግን ሊቀብል ሲል እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡

ባለጉዳዩ ለከንቲባ ጽ/ቤት እና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባደረሰው ጥቆማ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር በተደረገ ክትትል የጽህፈት ቤት ሃላፊውን ገንዘቡን ሲቀበል በቁጥጥር ስር መዋሉን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወንጀል ክትትል ሃላፊ ኮማደር አወሉ አህመድ ተናግረዋል፡፡

ይህ መረጃ ከተሰማ በኋላ ፖሊስ ተጨማሪ መረጃ ሰጥቷል፥….

ኤፍሬም አለሙ የተባለው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 03 አስተዳደር የግንባታ ፍቃድ ጽኅፈት ቤት ሃላፊ ለተገልጋይ ህገ ወጥ የግንባታ ፍቃድ ለመስጠት 140 ሺህ ብር ሲቀበል እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 3 አስተዳደር የግንባታ ፈቃድ ቁጥጥር ሃላፊ የሆነው ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋለው ዛሬ ነሃሴ 27 ቀን 2012 ዓም ነው፡፡

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ተወካይ ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው እንዳስረዱት ዶ/ር አድል አብደላ የተባሉት የግል ተበዳይ በረንዳ ለመስራት ፈልገው ወደ ወረዳው በመሄድ የግንባታ ፈቃድ ጠይቀው ከተፈቀደላቸው በኋላ ግንባታ ጀምረው ነበር፡፡

ይሁን እንጂ የአስተዳደሩ የቁጥጥር ሰራተኞች ወደ ግንባታው ስፍራ በመሄድ በተፈቀደው መሰረት ሳይሆን ከዚያ ውጪ እየተገባ እንደሆነ በመግለፅ እና በተጀመረው መንገድ መቀጠል ካስፈለገ የግል ተበዳይ 150 ሺህ ብር እንዲሰጡ መጠየቃቸውን ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው ተናግረዋል፡፡

የግል ተበዳይ ግን 150 ሺህ ብር የለኝም ሲሉ ወደ 80 ሺህ ብር ዝቅ እንደተደረገላቸው እና ከዚያ በኋላ ሁኔታውን ለፖሊስ ማሳወቃቸውን የጠቀሱት ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው 80ሺህ ብር እንደሌላቸውም በአካልም በስልክም ተገናኝተው ከተደራደሩ እና በ60 ሺህ ብር ከተስማሙ በኋላ ተጠርጣሪው ብሩን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡

በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን እና ማህበራዊ ትስስር ገፆች ተጠርጣሪው የተቀበለው ገንዘብ 140 ሺህ ብር እንደሆነ ተደርጎ የተገለፀው ስህተት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር እሸቱ ቅጣው ጠቅሰዋል። (የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድርና ፖሊስ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Social Tagged With: addis ababa land grab

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule