• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፍትኅ ለአዲስ አበባ” በሚል መሪ ቃል የማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ ተጀመረ

September 3, 2020 08:57 am by Editor Leave a Comment

ስለ አዲስ አበባ ፍትኅ የሚጠይቅ የማኅበራዊ መገኛ ዘዴዎች ዘመቻ ዛሬ በዋናነት በትዊተር ላይ ተጀመረ።

ዘመቻው ዛሬም እንደሚቀጥል አዘጋጆቹ የገለጡ ሲኾን፦ “በአዲስ አበባ የታየውን የመሬትና የኮንዶምንየም ምዝበራ በመቃወም” ፍትኅ ለመጠየቅ የተጀመረ መኾኑንም አክለዋል።

በዘመቻዉ ላይ “#ፍትህለአዲስአበባ”፤ “#አዲስአበባ” እንዲሁም “#ኢትዮጵያ” የሚሉ አሰባሳቢ ቃላት (ሐሽታጎች) ጥቅም ላይ ውለዋል።

የዘመቻው ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ “ተፈጸመ” ያሉትን አድሏዊ አሠራር እና በደል በመዘርዘር ተቃውሟቸውን እና ቅሬታቸውን ሲያስተጋቡ ተስተውለዋል።

የዘመቻው አስተባባሪዎች ባሰራጩት ጽሑፍ፦ “በኢ/ር ታከለ ኡማ አስተዳደር ዘመን በአዲስ አበባ የታለያዩ አድሎአዊ አሠራሮች፤ ጥቅመኝነት፤ የህዝብን ሃብት ማባከን የመሳሰሰሉ ጥፋቶች ተስተውለዋል” ብለዋል።

ግድፈቶች ብለው ከዘረዘሯቸው ነጥቦች መካከል፦ “በዋነኛነት የሚጠቀሰው የመሬት ወረራና ፍትሃዊ ያልሆነ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እደላ” መኾናቸውን አስምረውበታል። “እነዚህን ግድፈቶች አውጥተው ሲቃወሙ የነበሩ የሰብአዊ መብት አራማጆች የተለያዩ ማስፈራሪያዎች እና እስር ሲደርስባቸው” ማየታቸውንም አክለዋል። አዘጋጆቹ፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በቅርቡ ይፋ ያደረገው ጥናትን ዋቢ በማድረግም “ይህንን የሚያረጋግጥ ሆኗል” ብለዋል።

ኢዜማ ከሰሞኑ ጋዜጣዊ መግለጫ ከተከለከለ በኋላ “በአዲስ አበባ ከተማ የሚፈፀም የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ ጋር በተያያዘ” ጥናት ማድረጉን ገልጦ የጥናት ውጤቱን ይፋ አድርጎ ነበር።

ኢዜማ በጥናቱ ከ250ሺ ካሬ በላይ መሬት በሕገወጥ መንገድ ወረራ የተያዘ መኾኑን፤ ከብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ባለተገባ መንገድ ለግለሰቦች መተላለፋቸውን እንደሚያሳይም የማኅበራዊ መገናኛ ዘመቻው አዘጋጆች በጽሑፋቸው አክለዋል። የቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ዑማ በማኅበራዊ መገናኛ አውታራቸው ባሰራጩት መልዕክት በአስተዳደራቸዉ ዘመን ተከሰተ የተባለውን ምዝበራ እና አድሏዊ አሠራር አስተባብለዋል።

“ለ20ሺህ አርሶ አደሮች የተሰጡ የኮንዶሚኒየም ቤቶችን በተመለከተም ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት በካቢኔ የተወሰነና የተተገበረ ነው” ብለዋል። አስተዳደራቸው በወቅቱ የወሰደውን ርምጃም፦ “ከመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻዋ እለት ድረስ ጠንካራ የሆነ ርምጃ ስንወስድበት የቆየንበት ጉዳይ ነው”ም ብለዋል። “ከመሬታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ ከወደቁ በራሳቸው መሬት ላይ በተሠራ ህንጻ ዘበኛ እና ተሸካሚ ሆነው ከቀሩ 67ሺህ አባወራዎች መሃል የከፋ ችግር ላይ ለወደቁት 20ሺህ ኮንዶሚንየም ቢያንስ እንጂ የሚበዛ አይደለም። ስህተትም ከሆነ ለ67,000ውም አለመስጠታችን ነው። ከዚህ ውጭ በሕገወጥ መንገድ የተሰጠ ምንም አይነት ቤት የለም” ብለዋል።

የማኅበራዊ መገናኛ አውታሮች ዘመቻው አስተባባሪዎች፦ እንደ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፤ እንባ ጠባዊ ተቋም እና ሌሎች የሰብአዊ ድርጅቶች ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው በዋናነት “አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ ጫና እንዲያደርጉ መጠየቅ” ግባቸውን መኾኑን ጠቅሰዋል። በአዲስ አበባ አስተዳደር ላይ ከዚሕ ቀደምም ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በተለይ አኹን እስር ላይ በሚገኙት አቶ እስክንድር ነጋ በኩል ተደጋጋሚ መግለጫዎች ሲሰጥ እና ተቃውሞው ሲስተጋባ መቆየቱ የሚታወስ ነው። የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ጉዳዩ ያገባናል የሚሉ ወገኖችም ቅሬታቸዉን ሲያሰሙ ነበር።©ጀርመን ድምፅ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics, Social

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule