• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፍትኅ ለአዲስ አበባ” በሚል መሪ ቃል የማኅበራዊ መገናኛዎች ዘመቻ ተጀመረ

September 3, 2020 08:57 am by Editor Leave a Comment

ስለ አዲስ አበባ ፍትኅ የሚጠይቅ የማኅበራዊ መገኛ ዘዴዎች ዘመቻ ዛሬ በዋናነት በትዊተር ላይ ተጀመረ።

ዘመቻው ዛሬም እንደሚቀጥል አዘጋጆቹ የገለጡ ሲኾን፦ “በአዲስ አበባ የታየውን የመሬትና የኮንዶምንየም ምዝበራ በመቃወም” ፍትኅ ለመጠየቅ የተጀመረ መኾኑንም አክለዋል።

በዘመቻዉ ላይ “#ፍትህለአዲስአበባ”፤ “#አዲስአበባ” እንዲሁም “#ኢትዮጵያ” የሚሉ አሰባሳቢ ቃላት (ሐሽታጎች) ጥቅም ላይ ውለዋል።

የዘመቻው ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ “ተፈጸመ” ያሉትን አድሏዊ አሠራር እና በደል በመዘርዘር ተቃውሟቸውን እና ቅሬታቸውን ሲያስተጋቡ ተስተውለዋል።

የዘመቻው አስተባባሪዎች ባሰራጩት ጽሑፍ፦ “በኢ/ር ታከለ ኡማ አስተዳደር ዘመን በአዲስ አበባ የታለያዩ አድሎአዊ አሠራሮች፤ ጥቅመኝነት፤ የህዝብን ሃብት ማባከን የመሳሰሰሉ ጥፋቶች ተስተውለዋል” ብለዋል።

ግድፈቶች ብለው ከዘረዘሯቸው ነጥቦች መካከል፦ “በዋነኛነት የሚጠቀሰው የመሬት ወረራና ፍትሃዊ ያልሆነ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እደላ” መኾናቸውን አስምረውበታል። “እነዚህን ግድፈቶች አውጥተው ሲቃወሙ የነበሩ የሰብአዊ መብት አራማጆች የተለያዩ ማስፈራሪያዎች እና እስር ሲደርስባቸው” ማየታቸውንም አክለዋል። አዘጋጆቹ፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በቅርቡ ይፋ ያደረገው ጥናትን ዋቢ በማድረግም “ይህንን የሚያረጋግጥ ሆኗል” ብለዋል።

ኢዜማ ከሰሞኑ ጋዜጣዊ መግለጫ ከተከለከለ በኋላ “በአዲስ አበባ ከተማ የሚፈፀም የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ ጋር በተያያዘ” ጥናት ማድረጉን ገልጦ የጥናት ውጤቱን ይፋ አድርጎ ነበር።

ኢዜማ በጥናቱ ከ250ሺ ካሬ በላይ መሬት በሕገወጥ መንገድ ወረራ የተያዘ መኾኑን፤ ከብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ባለተገባ መንገድ ለግለሰቦች መተላለፋቸውን እንደሚያሳይም የማኅበራዊ መገናኛ ዘመቻው አዘጋጆች በጽሑፋቸው አክለዋል። የቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ዑማ በማኅበራዊ መገናኛ አውታራቸው ባሰራጩት መልዕክት በአስተዳደራቸዉ ዘመን ተከሰተ የተባለውን ምዝበራ እና አድሏዊ አሠራር አስተባብለዋል።

“ለ20ሺህ አርሶ አደሮች የተሰጡ የኮንዶሚኒየም ቤቶችን በተመለከተም ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት በካቢኔ የተወሰነና የተተገበረ ነው” ብለዋል። አስተዳደራቸው በወቅቱ የወሰደውን ርምጃም፦ “ከመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻዋ እለት ድረስ ጠንካራ የሆነ ርምጃ ስንወስድበት የቆየንበት ጉዳይ ነው”ም ብለዋል። “ከመሬታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ ከወደቁ በራሳቸው መሬት ላይ በተሠራ ህንጻ ዘበኛ እና ተሸካሚ ሆነው ከቀሩ 67ሺህ አባወራዎች መሃል የከፋ ችግር ላይ ለወደቁት 20ሺህ ኮንዶሚንየም ቢያንስ እንጂ የሚበዛ አይደለም። ስህተትም ከሆነ ለ67,000ውም አለመስጠታችን ነው። ከዚህ ውጭ በሕገወጥ መንገድ የተሰጠ ምንም አይነት ቤት የለም” ብለዋል።

የማኅበራዊ መገናኛ አውታሮች ዘመቻው አስተባባሪዎች፦ እንደ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፤ እንባ ጠባዊ ተቋም እና ሌሎች የሰብአዊ ድርጅቶች ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው በዋናነት “አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ ጫና እንዲያደርጉ መጠየቅ” ግባቸውን መኾኑን ጠቅሰዋል። በአዲስ አበባ አስተዳደር ላይ ከዚሕ ቀደምም ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በተለይ አኹን እስር ላይ በሚገኙት አቶ እስክንድር ነጋ በኩል ተደጋጋሚ መግለጫዎች ሲሰጥ እና ተቃውሞው ሲስተጋባ መቆየቱ የሚታወስ ነው። የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ጉዳዩ ያገባናል የሚሉ ወገኖችም ቅሬታቸዉን ሲያሰሙ ነበር።©ጀርመን ድምፅ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News, Politics, Social

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule