• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጃል መሮ “ሚስት” አዲስ አበባ ታየች

October 24, 2022 01:03 am by Editor Leave a Comment

ሚዲያ ኃይል ነው፤ ሚዲያ አራተኛው የመንግሥት ክንፍ ነው፤ ሚዲያ … ያነሳል ይጥላል፤ ሚዲያ መልካሙን ስም ያዋርዳል፤ ሚዲያ የተበላሸ ስም ይቀድሳል፤ ሚዲያ ነፍሰ ገዳዩን ቅዱስ ያደርጋል፤ ሚዲያ ብርቱ ነው። በተለይ በውጪ መንግሥታት እየተደገፉ ወደ አገራችን የሚተላለፉት የቋንቋ ሚዲያ አውታሮች ውስጥ የሚሠሩት ስብዕናቸውን የሸጡና በሚከፈላቸው ዳረጎት ልክ ራሳቸውን አዋርደው፤ አንገታቸውን ደፍተው የሚኖሩት ሚዲያውን የከፈቱን ታማኝ ሎሌዎች፣ የፍላጎታቸው ማስፈጸሚያዎች ናቸው። ይህንን ስል ግን ለሙያቸው ያደሩና እንከን የማይወጣላቸው ስመጥር የሚዲያ ሰዎች መኖራቸውን ሳልዘነጋ ነው።

ጃል መሮ የተባለውን ነፍሰ በላ ወንበዴ፤ መሣሪያ ታጥቆ ምስኪን ገበሬ፣ እናቶችንና ሕጻናትን የሚያርድ በላዔ ሰብ አሁን ላለበት ቁመና ያበቃው በሚዲያ ውስጥ የሚገኙ ስንኩላን ናቸው። አንዳንዶቹ ልዩ ተልዕኮ ያላቸው ሲሆኑ ሌሎቹ ግን ሳንቲም ለቃሚ የኅሊና ድህነት በእጅጉ ያጠቃቸው ናቸው።

በውጭ አገር ያሉና በሚገኙበት አገራት መንግሥት በጀት የሚተዳደሩ የሚዲያ አውታሮችና ጋዜጠኞች ለትውልድ አገራቸው ጥቅም የሚሠሩ ሳይሆን ቀጣሪዎቻቸው የሚያገለግሉ ናቸው። ለምሳሌ የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ርዕሰ አንቀጽ ባሰማ ቁጥር “ይህ የአሜሪካ መንግሥት አቋም ነው” ይላል። ይህንን የሚናገረው ግን ለኢትዮጵያውያን አድማጮቹ ነው። ዶይቸ ቨሌም (የጀርመን ድምፅ) እንዲሁም አገር ውስጥ ቁጭ ብሎ አገር አፍራሽ መረጃ የሚያትተው ቢቢሲም ከቪኦኤ ባይብሱ እንጂ በምንም ያልተለዩ ናቸው።

በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ውስጥ የሚደረገውን አሻጥርና አገር የማፍረስ ተግባር እዚህ ላይ መዘርዘር ለቀባሪው አረዱት ይሆንብኛል። የበረከት ስምዖንን ዘመድና የወያኔን አቀንቃኝ ሔኖክ ሰማእግዜርን ከመቅጠር ጀምሮ ሲፈጸም የቆየው ሤራ ብዙ የሚያስብል ነው። ቪኦኤ ደርግን ሲቃወም በነበረበት ዐቅም ወያኔን በግማሹ እንኳ ሳይቃወም መቆየቱ አሁን ከወያኔ ጋር በምናደርገው የኅልውና ጦርነት አንጻር ተመልክተን ከበቂ በላይ ምላሽ ያገኘንበት ነው። አሜሪካ ወያኔን ለማዳን ብቻ ሳይሆን መልሳ ወደ ሥልጣን ለማምጣት የሄደችበት ርቀት ቪኦኤ በርግጥም የማን ልሳን እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚነግረን ሆኗል።

ለዚህም ነው ጃል መሮ ካለበት ጎሬ ፈልጎ ቃለ መጠይቅ ለማድረግ ለቢቢሲም ሆነ ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ቀላል የሆነላቸው። በተለይ በቪኦኤ ላይ እስካሁን ጃል መሮ ያደረጋቸውን ቃለ ምልልሶች የተከታተለ ሰው “ማነው ቃለ መጠይቁን ያደርግለት የነበረው?” ብሎ ቢጠይቅ ምላሹ ጽዮን ግርማ ነች የሚል ይሆናል።

በተለይ አምና በመጋቢት ወር ጃል መሮን በቀጥታ ስልክ ጽዮን ደውላ ባነጋገረችው ጊዜ ምናልባት የሚዲያው መመሪያ ስላልፈቀደላት ይሆናል እንጂ “ጃልዬ፤ ጃሎ፤ ጃሌ ፍቅር፤ …” ብላ ብትጠራው የምትፈልግ ትመስል ነበር። ቢመልስም ባይመልስም ማንነቱን መጠየቅ ቀዳሚ ተግባሯ ነበር። ዓላማው ምን እንደሆነ እና በወለጋ ህዝብ ለምን እንደሚታረድ ለዚህም የእርሱ ቡድን ስሙ እንደሚነሳ መጠየቅ ሌላው ኃላፊነቷ ነበር። ይናገራል ብዬ ሳይሆን አለመናገሩ በራሱ የሚፈለግ ስለሆነ ነው።

የጃል መሮንና የጽዮንን ፍቅር በተመለከተ መረጃ ስፈልግ ይህንን አገኘሁ፤ …

“ቀደም ሲል በሃጫሉ ግድያ ኦነግ ሸኔ እጁ እንዳለበት በመታወቁ እጅግ የተቆጣውን ህዝብ ለማብረድ በናኮር መልካ አመቻችነት የቪኦኤ ዘጋቢ የሆነችው ጽዮን ግርማ ጃል መሮ በሬዲዮ ጣቢያው ቀርቦ ሳይፈተን እንዲፈነጭና ሃጢያቱን እንዲያራግፍ ፈቅዳለት እንደነበር ይታወሳል። ቢያንስ ማንነቱን መጠየቅ ሲገባ፣ ንጹሃንን በየቦታው እያደፈጠ ለሚጨፈጭፍ ሽፍታ፣ ሚዲያውንም ሌላ ጫካ በማድረግ የጨፍጫፊዎችን መሪ ቀረርቶ ስታሰማ “አይ ቪኦኤ ኤዲተርም፣ አለቃም፣ የሌለው ቤት ሆኗል” በሚል በርካቶች ሐዘናቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም። …

“የሆሮ ጉድሩ ሰለባዎች እና የጭፍጨፋው ምስክር የሆኑት ድንጋጤ ባዛለው ድምጽ፣ ሳግ እየተናነቃቸው “ኦነግ ሸኔ አረደን” እያሉ ነበር ለጽዮን የነገሯት። ሆኖም ጽዮን ግርማ “የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት” ዘርና ሃይማኖት ለይቶ እንደማያጠቃ ጃል መሮ ሲነገራት “ኦነግ ሸኔ” ብሎ ስሙን እንዲያስተካክል አላደረገችም። በቃለ ምልልሱ ወቅት በስህተት ቢዘነጋ እንኳ በጽሁፍ መንደርደሪያ ሲሰራለት አልተስተካከለም። ይህም ከደም ጋር ተያይዞ የቆሸሸውን ወንጀለኛውን ኦነግ ሸኔ ስሙን በመቀየር ቪኦኤ ተባባሪ እንዲሆን ያስቻለ በራሱ ወንጀል የሆነ ተግባር ነው።”

በወለጋ በቃላት ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ ለሚጨፈጨፈው ሕዝብ በቀጥታ ተጠያቂ የሆነው ሸኔ ሆኖ ሳለ ጽዮን ግን ጃል መሮ “እኔ የኦሮሞ ነጻአውጪ ሠራዊት” ነኝ ሲላት “እሺ አንበሳዬ” ማለት ሲቀራት ነው አሜን ብላ የተቀበለችው። ከላይ እንዳልኩት በወለጋ የሚታረዱት ወገኖቻችን ግን በየጊዜው የሚናገሩት “ኦነግ ሸኔ ጨፈጨፈን” በማለት ነው። በሌላ አነጋገር እስከ ቃለ መጠይቁ ድረስ በወለጋ ለተጨፈጨፉት ተጠያቂው ኦነግ ሸኔ እንጂ አሁን ጃል መሮ “የኦሮሞ ነጻ አውጪ ሠራዊት” ብሎ የዳቦ ስም የሰጠው ቡድን አይደለም።

ከላይ እንደተባለው በሃጫሉ ግድያም የሸኔ ቀጥተኛ እጅ እንዳለበት ስልክ ደውሎ ያስፈራራው የሸኔ አባል ምስክር ነው። ከዚህ ሌላ ሃጫሉ ራሱ “እየደወሉ ያስፈራሩኛል” ብሎ የተናገረ ሲሆን የቀብሩ ዕለት አምቦ ስታዲየም የኦነግ ሸኔ ባንዲራ መንጭቆ የወረወረው ዘመዱ ተግባር ብዙ የሚናገረው ነገር አለ። ይህንን ሁሉ የተከማቸ ወንጀልን ነው ጃል መሮ “እነ ሸኔ አይደለሁም” ብሎ ለጽዮን ሲነግራት “እሺ ፍቅሬ” ያለችው። ታዲያ ይህንን ለመሰለ የስም ዕድሳትና ውለታ የት ይገኛል?

መንግሥት ጃል መሮን እና ሸኔን ለማጥፋት ብዙ እየጣረ ነው። በኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳድር ውስጥ ባለ የተቀናጀ የወንበዴ ቡድንና በሌሎች እገዛ የወያኔ ፍርፋሪ ለቃሚው ጃል መሮ በሸኔ ታጣቂዎቹ አሁንም ወገኖቻችንን ማረዱን ቀጥሏል። ወያኔ ስትታነቅ ሸኔም እንደሚተን ግን ምንም ጥርጥር የለም። ቢሆንም ሸኔን ሲያነግሡ የነበሩት እነ ጽዮንን ዝም ማለት አግባብ አይመስለኝም።

በተለይ ባሁኑ ሰዓት ወያኔን አስወግዶ ሸኔን አብሮ መሸኘት አግባብ ያለው ተግባር በመሆኑ ጃል መሮን በቁጥጥር ሥር ማዋሉ በቀዳሚነት ሊሠራበት የሚገባ ጉዳይ ነው። ይህንን ደግሞ መንግሥት የሚያጣው አይመስለኝም። ስለዚህ ጃል መሮን ለማግኘት ባሁኑ ሰዓት አዲስ አበባ የምትገኘውን የጃል መሮን “ሚስት” ጽዮን ግርማን መንግሥት “እንዴት ነሽ? ሰላም ነው?” ቢላት ጥሩ ይመስለኛል። የስልክ ቁጥሩን እና በስንት ሰዓት ሲደወልለት ስልክ እንደሚያነሳ ብቻ ከተናገረች በቂ ነው። “ጽዮን የት ትገኛለች?” ብሎ ለሚጠይቅ ደግሞ መልሱ ጥሬ ሥጋ ያለበት ቦታ በሙሉ አትጠፋም ነው የጥቆማ መልሴ። እኔም ጥሬ ስትቆርጥ ባጋጣሚ አይቼ ነው ይህንን ጥቆማ የሰጠሁት። በዚህ አጋጣሚ እሷንም ሆነ አብረው ከጥሬው የሚቆርጡትን በሙሉ በወለጋ የታረዱትን ወገኖቻችንን በዓይነ ኅሊናችሁ እየተመለከታችሁና በጽዮን ያላሰለሰ ልፋትና ትጋት ለዚህ ዕድል መብቃታችሁን እያመሰገናችሁ ጥሬውን በደማቸው አወራርዱት።

ናኮር ግርማይ ነኝ         


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

    

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: jal mero, olf shanee, operation dismantle tplf, tplf terrorist, tsion girma, voa amharic

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule