• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢዜማ በአዲስ አበባ አስተዳደር ላይ ክስ መሠረተ

October 12, 2020 11:38 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሰሰ። ፓርቲው ክሱን የመሰረተው የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት በሰጠው ትዕዛዝ፤ የፓናል ውይይት እንዳያደርግ መከልከሉን በመቃወም ነው።    

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ፍትሐ ብሔር ችሎት ባለፈው አርብ መስከረም 30፤ 2013 የተከፈተው የክስ መዝገብ፤ በፓርቲው ላይ የደረሰው “የሁከት ተግባር እንዲታገድ” የሚጠይቅ ነው። ኢዜማ ይህን ክስ ለማቅረብ የተገደደው ሕገ መንግስታዊ የሆነው “የመሰብሰብ መብት” በተከሳሽ መስሪያ ቤት በተሰጠ ትዕዛዝ በመገደቡ መሆኑን ገልጿል። 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ለክስ ያበቃውን ትዕዛዝ ለፓርቲው የጻፈው ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 25፤ 2013 ነበር። በከተማይቱ ከንቲባ ጽህፈት ቤትና ካቤኔ ጉዳዮች ኃላፊ በሆኑት አቶ ኤፍሬም ግዛው ፊርማ የተላከው ደብዳቤ፤ ፓርቲው ለመስከረም 28 የጠራውን የፓናል ውይይት እንዲሰረዝ ያሳስባል። 

ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የኢዜማ የፓናል ውይይት ትኩረቱን ያደረገው፤ በአዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ሁኔታ ተንሰራፍቷል በተባለው ሕገወጥ የመሬት ወረራ እና ፍትሃዊ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ዕደላ ጉዳይ ላይ ነበር። ፓርቲው የፓናል ውይይት ለማድረግ የተነሳው በጉዳዩ ላይ ያደረገውን ዝርዝር ጥናት ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ለህዝብ ይፋ ካደረገ በኋላ ነው። 

በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኖ የሰነበተውን ይህን ጥናት እንዲካሄድ የወሰነው፤ የኢዜማ ብሔራዊ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንደነበር ፓርቲው በክሱ ማብራሪያ ላይ ጠቅሷል። የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በጉዳዩ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እንዲደረግ ተጨማሪ ውሳኔ ማስተላለፉን ተከትሎ ፓርቲው ለመስከረም 15 በፓርቲው ጽህፈት ቤት ውይይት ጠርቶ እንደነበር አስታውሷል።  

ሆኖም ከከተማ አስተዳደሩ እና ከጸጥታ አካላት ጋር በተደረገ ውይይት፤ ዕለቱ የመስቀል በዓል ደመራ መሆኑንና በሳምንቱም የኢሬቻ በዓል የሚከበር ስለሆነ “በቂ የጸጥታ ጥበቃ እንደማይኖር” እንደተገለጸለት ፓርቲው በክሱ ዝርዝር ላይ አስረድቷል። በዚህም ምክንያት የፓናል ውይይቱን የሚካሄድበትን ቀን ለመስከረም 28 ማስተላለፉን እና ይህንኑም ለከተማው አስተዳደር፣ ለጸጥታ አካላት እና ለተሳታፊዎች ማሳወቁን አብራርቷል። 

ኢዜማ ውይይቱን ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቅቆ በሚጠባበቅበት ወቅት፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ውይይቱን ማድረግ እንደማይችሉ በደብዳቤ ማሳወቁን አመልክቷል። ፓርቲው ጽህፈት ቤቱ የሰጠውን ይህን ማሳሰቢያ “ህገ ወጥ ትዕዛዝ” ሲል በክሱ ላይ ጠርቶታል። 

“በሕገ መንግስቱ መብት የማክበርና የማስከበር ግዴታና ኃላፊነት የተሰጠው ተከሳሽ መስሪያ ቤት፤ ግዴታውን ካለመወጣት አልፎ የመብት አደናቃፊ መሆኑ በጣም አሳሳቢ እና እንደ ፓርቲም ሆነ እንደ ሀገር ልንገነባው የምናስበውን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት እንቅፋት የሚሆን የመብት ረገጣ ተግባር በከሳሽ ፓርቲ ላይ ፈጽሟል” ሲል ኢዜማ በክሱ ላይ አትቷል። 

ሕገመንግስታዊ የመሰብሰብ መብቱን “በፍርድ ኃይል እንዲከበር” በማሰብ ክሱን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ለማቅረብ መገደዱን የገለጸው ፓርቲው፤ ክሱ ከቀረበለት ፍርድ ቤት በሁለት ጉዳዩች ላይ ዳኝነት ለማግኘት ጥያቄ አቅርቧል። የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት በሕግ ከተሰጠው ስልጣን ውጪ ፓርቲው ሊያደርግ የነበረውን ውይይት መከልከሉ “ሕገ ወጥ ድርጊት ነው” በማለት ውሳኔ እንዲሰጥ ያመለከተበት ነው።

ሁለተኛው ደግሞ ፓርቲው ስብሰባ እና ውይይት እንዳያደርግ፤ ተከሳሽ መስሪያ ቤት የሰጠውን ትዕዛዝ እንዲያነሳ እና ወደፊትም ተመሳሳይ የመብት ጥሰቶችን ከማድረግ እንዲቆጠብ፤ ፍርድ ቤቱ ግልጽ ትዕዛዝ እና ውሳኔ እንዲሰጥ የጠየቀበት ነው። ፓርቲው ጉዳዩን የሚያስረዱለት ሁለት የሰው ማስረጃዎችን በክስ መዝገቡ ላይ የጠቀሰ ሲሆን ሶስት የሰነድ ማስረጃዎችንም አያይዞ አቅርቧል። 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ለፓርቲው የጻፈው ደብዳቤ በሰነድ ማስረጃነት ከቀረቡት ውስጥ አንዱ ነው። ጽህፈት ቤቱ በዚሁ ደብዳቤው፤ ኢዜማ ከመሬት ወረራና ከጋራ መኖሪያ ቤቶች አንጻር ያነሳቸውን ጉዳዮች የከተማው አስተዳደር “በጥሞና” መመልከቱን ገልጿል። አስተዳደሩ “የመረጃውን ወይም ጥቆማውን ተገቢነት በመመርመር ተገቢውን አስተዳደራዊና ህጋዊ ውሳኔዎችን ለመስጠት በተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መሆኑን”፤ የፓርቲው የበላይ አመራሮች ከምክትል ከንቲባ አዳነች አበቤ ጋር በተገናኙበት ወቅት መግለጹንም አስታውሷል። 

በፓርቲው አመራሮች እና በከተማው የስራ ኃላፊዎች ዘንድ “መግባባት” እንደነበር የሚጠቅሰው ጽህፈት ቤቱ፤ መረጃው እየተጣራ በሚገኝበት ወቅት ኢዜማ የፓናል ውይይት ማዘጋጀቱን የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሰው አመልክቷል። አስተዳደሩ ቀደም ሲል ደርሰንበታል ባለው መግባባት እና በሶስት ምክንያቶች መሰረት የፓናል ውይይቱ መሰረዝ እንዳለበት በደብዳቤው አሳስቧል። 

የመጀመሪያው ምክንያት “አስተዳደሩ የጀመራቸውን ስራዎች መጨረስ ስለሚገባው” የሚል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ “እንደዚህ አይነት የማጥራት ተግባራት የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ በሌላ መንገድ መሄዱ ተገቢነት ስለሌለው” መሆኑ በደብዳቤው ተጠቅሷል። ለፓናል ውይይቱ መሰረዝ የከተማይቱ አስተዳደር በመጨረሻነት የጠቀሰው “የማጥራት ስራውን አስተዳደሩ ባለጠናቀቀበትና በትጋት እየሰራ ባለበት ወቅት ውይይት መጥራት ወደ ሌላ አተካራና ምናልባትም ወደ ግጭት የሚወስድ ነው” የሚል ነው። 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ባሰረዘው የፓናል ውይይት ምክንያት የቀረበበትን ክስ ለመመልከት ገና ቀጠሮ እንዳልተሰጠ የኢዜማ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ በቀጣዩቹ ቀናት ቀጥሮ ሊሰጥ ይችላል ተብሎ እንደሚጠበቅም አስረድተዋል። (በተስፋለም ወልደየስ፤ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: addis ababa land grab, addis condo, ezema

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule