• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢዜማ በአዲስ አበባ አስተዳደር ላይ ክስ መሠረተ

October 12, 2020 11:38 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሰሰ። ፓርቲው ክሱን የመሰረተው የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት በሰጠው ትዕዛዝ፤ የፓናል ውይይት እንዳያደርግ መከልከሉን በመቃወም ነው።    

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ፍትሐ ብሔር ችሎት ባለፈው አርብ መስከረም 30፤ 2013 የተከፈተው የክስ መዝገብ፤ በፓርቲው ላይ የደረሰው “የሁከት ተግባር እንዲታገድ” የሚጠይቅ ነው። ኢዜማ ይህን ክስ ለማቅረብ የተገደደው ሕገ መንግስታዊ የሆነው “የመሰብሰብ መብት” በተከሳሽ መስሪያ ቤት በተሰጠ ትዕዛዝ በመገደቡ መሆኑን ገልጿል። 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ለክስ ያበቃውን ትዕዛዝ ለፓርቲው የጻፈው ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 25፤ 2013 ነበር። በከተማይቱ ከንቲባ ጽህፈት ቤትና ካቤኔ ጉዳዮች ኃላፊ በሆኑት አቶ ኤፍሬም ግዛው ፊርማ የተላከው ደብዳቤ፤ ፓርቲው ለመስከረም 28 የጠራውን የፓናል ውይይት እንዲሰረዝ ያሳስባል። 

ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የኢዜማ የፓናል ውይይት ትኩረቱን ያደረገው፤ በአዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ሁኔታ ተንሰራፍቷል በተባለው ሕገወጥ የመሬት ወረራ እና ፍትሃዊ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ዕደላ ጉዳይ ላይ ነበር። ፓርቲው የፓናል ውይይት ለማድረግ የተነሳው በጉዳዩ ላይ ያደረገውን ዝርዝር ጥናት ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ለህዝብ ይፋ ካደረገ በኋላ ነው። 

በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኖ የሰነበተውን ይህን ጥናት እንዲካሄድ የወሰነው፤ የኢዜማ ብሔራዊ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንደነበር ፓርቲው በክሱ ማብራሪያ ላይ ጠቅሷል። የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በጉዳዩ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እንዲደረግ ተጨማሪ ውሳኔ ማስተላለፉን ተከትሎ ፓርቲው ለመስከረም 15 በፓርቲው ጽህፈት ቤት ውይይት ጠርቶ እንደነበር አስታውሷል።  

ሆኖም ከከተማ አስተዳደሩ እና ከጸጥታ አካላት ጋር በተደረገ ውይይት፤ ዕለቱ የመስቀል በዓል ደመራ መሆኑንና በሳምንቱም የኢሬቻ በዓል የሚከበር ስለሆነ “በቂ የጸጥታ ጥበቃ እንደማይኖር” እንደተገለጸለት ፓርቲው በክሱ ዝርዝር ላይ አስረድቷል። በዚህም ምክንያት የፓናል ውይይቱን የሚካሄድበትን ቀን ለመስከረም 28 ማስተላለፉን እና ይህንኑም ለከተማው አስተዳደር፣ ለጸጥታ አካላት እና ለተሳታፊዎች ማሳወቁን አብራርቷል። 

ኢዜማ ውይይቱን ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቅቆ በሚጠባበቅበት ወቅት፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ውይይቱን ማድረግ እንደማይችሉ በደብዳቤ ማሳወቁን አመልክቷል። ፓርቲው ጽህፈት ቤቱ የሰጠውን ይህን ማሳሰቢያ “ህገ ወጥ ትዕዛዝ” ሲል በክሱ ላይ ጠርቶታል። 

“በሕገ መንግስቱ መብት የማክበርና የማስከበር ግዴታና ኃላፊነት የተሰጠው ተከሳሽ መስሪያ ቤት፤ ግዴታውን ካለመወጣት አልፎ የመብት አደናቃፊ መሆኑ በጣም አሳሳቢ እና እንደ ፓርቲም ሆነ እንደ ሀገር ልንገነባው የምናስበውን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት እንቅፋት የሚሆን የመብት ረገጣ ተግባር በከሳሽ ፓርቲ ላይ ፈጽሟል” ሲል ኢዜማ በክሱ ላይ አትቷል። 

ሕገመንግስታዊ የመሰብሰብ መብቱን “በፍርድ ኃይል እንዲከበር” በማሰብ ክሱን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ለማቅረብ መገደዱን የገለጸው ፓርቲው፤ ክሱ ከቀረበለት ፍርድ ቤት በሁለት ጉዳዩች ላይ ዳኝነት ለማግኘት ጥያቄ አቅርቧል። የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት በሕግ ከተሰጠው ስልጣን ውጪ ፓርቲው ሊያደርግ የነበረውን ውይይት መከልከሉ “ሕገ ወጥ ድርጊት ነው” በማለት ውሳኔ እንዲሰጥ ያመለከተበት ነው።

ሁለተኛው ደግሞ ፓርቲው ስብሰባ እና ውይይት እንዳያደርግ፤ ተከሳሽ መስሪያ ቤት የሰጠውን ትዕዛዝ እንዲያነሳ እና ወደፊትም ተመሳሳይ የመብት ጥሰቶችን ከማድረግ እንዲቆጠብ፤ ፍርድ ቤቱ ግልጽ ትዕዛዝ እና ውሳኔ እንዲሰጥ የጠየቀበት ነው። ፓርቲው ጉዳዩን የሚያስረዱለት ሁለት የሰው ማስረጃዎችን በክስ መዝገቡ ላይ የጠቀሰ ሲሆን ሶስት የሰነድ ማስረጃዎችንም አያይዞ አቅርቧል። 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ለፓርቲው የጻፈው ደብዳቤ በሰነድ ማስረጃነት ከቀረቡት ውስጥ አንዱ ነው። ጽህፈት ቤቱ በዚሁ ደብዳቤው፤ ኢዜማ ከመሬት ወረራና ከጋራ መኖሪያ ቤቶች አንጻር ያነሳቸውን ጉዳዮች የከተማው አስተዳደር “በጥሞና” መመልከቱን ገልጿል። አስተዳደሩ “የመረጃውን ወይም ጥቆማውን ተገቢነት በመመርመር ተገቢውን አስተዳደራዊና ህጋዊ ውሳኔዎችን ለመስጠት በተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መሆኑን”፤ የፓርቲው የበላይ አመራሮች ከምክትል ከንቲባ አዳነች አበቤ ጋር በተገናኙበት ወቅት መግለጹንም አስታውሷል። 

በፓርቲው አመራሮች እና በከተማው የስራ ኃላፊዎች ዘንድ “መግባባት” እንደነበር የሚጠቅሰው ጽህፈት ቤቱ፤ መረጃው እየተጣራ በሚገኝበት ወቅት ኢዜማ የፓናል ውይይት ማዘጋጀቱን የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሰው አመልክቷል። አስተዳደሩ ቀደም ሲል ደርሰንበታል ባለው መግባባት እና በሶስት ምክንያቶች መሰረት የፓናል ውይይቱ መሰረዝ እንዳለበት በደብዳቤው አሳስቧል። 

የመጀመሪያው ምክንያት “አስተዳደሩ የጀመራቸውን ስራዎች መጨረስ ስለሚገባው” የሚል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ “እንደዚህ አይነት የማጥራት ተግባራት የመንግስት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ በሌላ መንገድ መሄዱ ተገቢነት ስለሌለው” መሆኑ በደብዳቤው ተጠቅሷል። ለፓናል ውይይቱ መሰረዝ የከተማይቱ አስተዳደር በመጨረሻነት የጠቀሰው “የማጥራት ስራውን አስተዳደሩ ባለጠናቀቀበትና በትጋት እየሰራ ባለበት ወቅት ውይይት መጥራት ወደ ሌላ አተካራና ምናልባትም ወደ ግጭት የሚወስድ ነው” የሚል ነው። 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ባሰረዘው የፓናል ውይይት ምክንያት የቀረበበትን ክስ ለመመልከት ገና ቀጠሮ እንዳልተሰጠ የኢዜማ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ በቀጣዩቹ ቀናት ቀጥሮ ሊሰጥ ይችላል ተብሎ እንደሚጠበቅም አስረድተዋል። (በተስፋለም ወልደየስ፤ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: addis ababa land grab, addis condo, ezema

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule