• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ

December 13, 2022 09:42 am by Editor Leave a Comment

በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለሚከሰቱ ግጭቶችና የሰላም እጦት ችግሮች ሙስና ዋነኛው መንስኤ መሆኑን ትራንስፓረንሲ ኢትዮጵያ አስታወቀ። ባለፈው ዓመት በተካሄደው ጥናት መሰረት ኢትዮጵያ በሙስና ከዓለም 87ኛ ደረጃ ላይ እንደነበረች ተጠቁሟል።

የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ካሳሁን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ሙስና በኢትዮጵያ እየተከሰቱ ላሉ ግጭቶችና የሰላም እጦቶች ዋነኛ መንስኤ ነው።

ኢትዮጵያ የተለያዩ የጸረ ሙስና ስምምነቶችን ብታደርግም፤ የጸረ ሙስና ትግሉን የሚያጠናክሩ ተቋማት አለመኖራቸው ውጤታማ ስራ እንዳይሰራ ምክንያት ሆኗል ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ።

በኢትዮጵያ እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶችና የሰላም እጦቶች በአንድም ሆነ በሌላ ከሙስና ጋር የተያያዙ እንደሆኑ የተናገሩት አቶ ሳሙኤል፤ ሙስናና ብልሹ አሰራር እንዲስፋፋ ዋነኛ ምክንያት ማህበረሰቡ ሙስና የሀገር ገዳይ ነቀርሳ መሆኑን አለመረዳቱና እንደብልጠት መቁጠሩ ነው ብለዋል። ከዚህም ባለፈ የኑሮ ውድነት፣ ድህነትና ሀገራዊ እሴት እየተሸረሸረ መምጣት ለሙስና መስፋፋት መንስኤ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተለይ በመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ በፋይናንስ ዘርፍ፣ በፍትህና በፀጥታ ዘርፎች፣ በሽያጭና ግዢ በተለይም ከመሬት ጋር በተያያዘ እንዲሁም በብድር አሰጣጥና እጥረት ባለባቸው የፍጆታ እቃዎች አቅርቦት ዙሪያ ሰፋ ያለ ያለአግባብ የመበልጸግ እና የሌብነት ተግባራት የሚታዩ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የሙስና ተግባራቱ ኅብረተሰቡን ያማረሩ ችግሮች መሆናቸውንና በአገር እድገትና የብልፅግና ጉዞ ትልቅ እንቅፋት እየሆኑ መምጣታቸውን ገልፀው፤ መንግሥት ችግሩን ለመቅረፍና ሙሰኞችን ተጠያቂ ለማድረግ የጀመረውን እንቅስቃሴ በጥንካሬ አንስተዋል። የኅብረተሰቡ ተሳትፎ አስፈላጊ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።

እንደ አቶ ሳሙኤል ገለፃ፤ ሙስናን ለመከላከል የመንግሥት አስተዳደርና በህብረተሰቡ ውስጥ የፀረ-ሙስና ባህልን ማሳደግ አስፈላጊ ነው። በባለሥልጣናት እና በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ላይ የውጭና የውስጥ ቁጥጥር ዘዴዎችን ማጠናከርም ያስፈልጋል። ይህም የሙስና ወንጀሎችን በብቃት ከመለየት ባለፈ ሙስናን በዘላቂነት ለመከላከል ያስችላል።

ሙስናን በትክክል መዋጋት የሚቻለው በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ከሚሳተፉ ተቋማት ጋር መስራት ሲቻል ነው ያሉት አቶ ሳሙኤል፤ ስለዚህ በዚህ ዓመት በመንግሥትና በህብረተሰቡ ጥረት ለሚሰሩ ተግባራት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያደርግ ይገባል። ሙስናን መታገል በተግባር መሆን አለበት ብለዋል።

እንደ አቶ ሳሙኤል ገለጻ፤ ህብረተሰቡ ሙስናን በተግባር የሚታገልበት፣ በሥነ ምግባር እራሱን የሚያንጽበት ሁኔታን መንግሥት ማመቻቸት ይኖርበታል። ከዚህም ባለፈ ለሙስና አደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች የመንግሥት ቁጥጥርና የመከላከያ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው።

ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል በየዓመቱ የሙስና ቅኝት ጥናት በማካሄድ የሀገራትን የሙስና ሁኔታ የሚያሳይ ደረጃና ውጤት ይፋ የሚያደርግ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም ነው። ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የሙስና ቅኝት የ2021 ሪፖርት ላይ እንደተመለከተው ኢትዮጵያ ከ180 ሀገራት ውስጥ 39 ከመቶ ነጥብ በማግኘት 87ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አስፍሯል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: corruption, operation dismantle tplf, transparency international

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule