• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጣመ ውይይት

January 17, 2013 09:18 am by Editor 3 Comments

ከዝግጅት ክፍሉ፤

አቶ ጋሻው ዓለሙ ጀምረውት አቶ አንዱ አለም ተፈራ የቀጠሉትና በማስከተልም አቶ ጋሻው ምላሽ የሰጡበት ውይይት እዚህ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ አቶ ጋሻው ለሰጡት ምላሽ አቶ አንዱ አለም አጸፋውን በሚከተለው መንገድ አቅርበዋል፡፡ በዚህ ጽሁፍ ላይ አቶ አንዱ አለም እንደጠቀሱት እኛም አዘጋጆቹ ይህ ውይይት አገራዊ እንደመሆኑ ሌሎቻችሁም የምትሉት ቢኖር የበለጠ ውይይቱ ያዳብረዋል፤ ያሰፋዋል እንዲሁም ፖለቲከኞቻችን ትምህርት ሊወስዱ የሚችሉበትን ሃሳብ ሊያገኙበት ይሆናል፡፡ የበርካታዎች መሳተፍ ጥቅሙ ተዘርዝሮ የሚያልቅ ባለመሆኑ ሌሎቻችሁም በዚህ ጉዳይ ላይ ያላችሁን ሃሳብ፤ አስተያየት፤ ድጋፍ እንዲሁም ተቃውሞ በሠለጠነ መልኩ በማቅረብ ውይይቱን እንድታሰፉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ለአቶ ጋሻውና ለአቶ አንዱ አለም እጅግ የከበረ ምስጋናችን ይድረሳቸው፡፡


የተቃዋሚ ፖለቲካ ኃይሎች ተቋማዊ ድክመት ወይስ የራዕይና ስትራተጂ ልዩነት?

በአቶ ጋሻው አለሙ ተጀምሮ የምናደርገው ውይይት

ዋናው ቁም ነገር ከሁለታችን ውጪ፤ ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ቢሳተፉበትና ሀገራዊ ስፋት ብንሠጠው ነውና፤ እባካችሁ ተሳተፉ። ሁለታችን ብቻ የጉዳዩ ባለቤቶች እንዳልሆንን ሁላችሁ ታውቃላችሁ። አቶ ጋሻው አለሙ የሚጥሩት፤ ጥሩ ነጥቦች በማራመድ፤ በተለይም የነገዋ ኢትዮጵያ ትክክለኛ ሥርዓት ኖሯት፤ ሰላምና ልማት እንዲከተል በማሰብ መሆኑን አጥብቄ ተረድቻለሁ። እኔም ይኼው ምኞቴ ስለሆነ፤ ባንድነት የምንሄድበትን መንገድ ለማግኘት ነው አቀራረቤ።

ሁለታችንም የተግባባንባቸውን ትቼ፤ አቶ ጋሻው አለሙና እኔ አንድ ያልተግባባንበትና አንድ የተለያየንበት ነጥብ ጎልቶ ታይቶኛል። በርግጥ ሌሎች ካሉና ከዘለልኳቸው አቶ ጋሻው እንደሚያስታውሱኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ያልተግባባንበት ያልኩትን፤ በደንብ ልትገልፀው ይገባል እንዳሉኝ አድርጌ እወስደውና አብራራለሁ። የተለያየንበትን ደግሞ ማስረገጫዬን በማቅረብ ነጥቤን አሰምራለሁ።

ያልተግባባንበት ጉዳይ፤ ሁለታችንም አንድ ነገር እያልን፤ መደማመጡ ላይ ትንሽ የተራራቅን በመሆናችን ብቻ ነው። ይኼን እንዲያስረዳልኝ፤ እስኪ ከአቶ ጋሻው አለሙ ጽሑፍ ትንሽ ጠቅሼ ላስቀምጥ፤

“እንደኔ እስካሁን ድረስ ከገመገምኳቸው 13 የፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራም አንጻር ስመለከተው መሰባሰብ ያለብን በሃሳብ ዙሪያ ነው ባይ ነኝ።”. . . . . ቀጥለውም፤ . . . . . “ስለዚህ፣ በተቃውሞ ፖለቲካ ልሂቃኖች መካከል ያለውን ግለሰባዊ ቁርሾ ወደ ጎን አድርገን፣ ትልቁን ሃገራዊውን ምስል ተመልክተን፣ አንድ በሚያደርጉን ሃሳቦች ዙሪያ ተደራጅተን በሂደት ልዩነታችንን በማጥበብ፣ የተቃውሞ ሂደቱን ተቋማዊ አድርገን፣ ጠንካራ፣ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበትን አደረጃጀትና አሰራር ዘርግተን ተቃውሞውን መምራት መቻል አለበን።”

አቶ ጋሻው አለሙ፤ አመሰግናለሁ። እኔም እኮ፤ መሰባሰቢያ የሚሆነንን ሃሳብ ነው በአምስት ነጥቦች ያሠፈርኩት። ይህ የአምስት ነጥቦች ሃሳብ እኮ ነው ትልቁ ሀገራዊ ምስል፣ አንድ የሚያደርጉን ሃሳቦች በማለት ያሠፈሩት። መለስ ብዬ ጠለቅ ያለ ትንተና ልስጥ። አምስቱን ነጥቦች አስመልክቶ፤ አቶ ጋሻው ሲጀምሩ፤

“የኢትዮጵያ እንደ ሀገር የመቆምና አንድ ሀገር ሆኖ የመቀጠል ጉዳይ መያያዝ ያለበት፤ ከግዛት አንድነት ጋር ብቻ ሳይሆን የመንፈስና የህዝቦች አንድነት ጋር ጭምር መሆን ይገባዋል::” ብለዋል።

እስኪ እኔ ያልኩትን ልድገም። በአንድ ቁጥር አንድ ሕዝብ መሆናችንን መቀበል፣ በሁለት ቁጥር አንድ ሀገር እንዳለን መቀበል አስፍሬያለሁ።

እንዲህ አድርጌ፤
፩ኛ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብን አንድነት በተመለከተ፤ አንድ ሕዝብ ነን ወይንስ አይደለንም?

፪ኛ፤ ሀገራችንን በተመለከተ፤ ኢትዮጵያ፤ የቆዳ ስፋቷና ክልሏ ተጠብቆላት፤ አንድ ሀገር ናት ወይንስ አይደለችም?

እሳቸው በሶስተኛነት ያስቀመጡት የመንፈስ አንድነት ተደጋጋሚ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። የሕዝቡን አንድነትና የሀገሪቱን አንድነት የተቀበለ፤ የመንፈስ አንድነቱ መደረት ካልሆነ የሚጨምረው አዲስ እውነታ አይታይኝም። መንፈሱ ለኔ፤ የሀገሪቱንና የሕዝቡን አንድነት መቀበል ነውና። ታዲያ ያላልኩት ምን ቀረ? ሁለታችንም አንድ ነገር ነው ያልነው ብዬ አልፈዋለሁ።

እዚህ ላይ አቶ ጋሻው አለሙ ሊያሠምሩበት የፈለጉት፤ “ስለዚህ በመሰረታዊነት በተቃውሞ ኃይሎችና ልሂቃን መታየት ያለበት ጉዳይ እኛ አንድ ህዝብ ነን ወይ የሚለው አስተሳሰብ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት በምን ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት የሚለውን ነው።”

በጣም ጥሩ ነው። ይሁን እንጂ፤ “በምን ላይ ነው የተመሠረተ” የሚለውን የአንድነት ጉዳይ ለመነጋገር፤ መጀመሪያ አንድነት የሚለውን መቀበሉ አይቀድምም ወይ? አንድነት ብለን ለመነጋገር፤ አንድነት መኖሩን መቀበል ግዴታ ነው።

ቀጥለውም፤ “የህዝቦች አንድነት መገለጽ ያለበት ትላንት በተደረጉ ድርጊቶች ብቻ ሳይሆን በነገ የጋራ ተስፋዎች ጭምር መሆን ይገባዋልና ነው።” ብለዋል። ታዲያ ይኼንን ለማድረግ፤ መጀመሪያ ባንድ ላይ መቀመጥና ለነገ የጋራ ተስፋችን ባንድ ላይ እንነጋገር፣ እንንደፍ፣ አንድ ነን መባባልን አይጠይቅም ወይ? ታዲያ ይኼ ቅድመ ሁኔታውን፤ አንድነት አለን ማስበል ግድ አይልም ወይ? ልቀጥል። በነገራችን ላይ፤ የአሜሪካ ሕዝብ አንድ ነው። የሕገ መንግሥታቸው መንደርደሪያ የሚጀምረው፤ “እኛ የአሜሪካ ሕዝብ . . . ” በማለት ነው።

እንግዲህ መሠረታዊ ለውጥ ማለት፤ ከመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ነጥቦች ቀጥለው የሠፈሩት ሶስት ነጥቦች ናቸው። አንዱ አቶ ጋሻው አለሙ እንዳሉት በስልጣን ለይ ያለውን ኃይል ከሥልጣን ማውረድ ነው። ይኼ ደግሞ በቀጥር አምስት ሠፍሯል።

፭ኛ፤ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን በተመለከተ፤ ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ጠላት ዘረኛው አምባገነን የወያኔ አስተዳደር ነው። ይህ መንግሥት ሊታረም የማይፈልግና የማይችል ነው። ይህ መንግሥት መወገድ አለበት ወይስ የለበትም? መሠረታዊና ሥር ነቀል የሥርዓት ለውጥ ያሉትን ደግሞ፤ በቁጥር ሶስትና አራት ሠፍሯል። የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብቶችና የሕግ የበላይነት ናቸው።

፫ኛ፤ የዴሞክራሲያዊ መብትን በተመለከተ፤ እያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ የግለሰብ መብቷ ተከብሮላት፣ በየትኛውም የሀገሪቱ ክልል ሠርታ የመጠቀም፣ መኖሪያ የማበጀት፣ ሀብት የማፍራት፣ በኢትዮጵያዊነቷ (ከሃይማኖትና የዘር ትውልድ ባልተዛመደና ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ በማያገልል መንገድ) ከመሰል የአስተሳሰብ አንድነት ካላቸው ኢትዮጵያዊያን ግለሰቦች ጋር የፖለቲካ ተሳትፎዋን ማድረግ የምትችልበት እንድትሆን ነው ወይ ትግሉ?

፬ኛ፤ የሕግ የበላይነትን በተመለከተ፤ ከግለሰቦችና ድርጅቶች ውጪ፤ በሕገ ደንብና አሠራር ለመገዛትና ለመተማመን ነው ወይ የምንታገለው?

ይኼንን ያልተግባባንበትን ጉዳይ፤ ይኼ ግልፅ ያደርገዋል ብዬ ልለፈው፤ ምክንያቱም ሁለታችንም የምንለው አንድ ነውና። በነዚህ አምስት ነጥቦች ላይ አንድ ነን ብለው በግልፅ፤ አቶ ጋሻው እንዳሉት፤ የሚስማሙት ድርጅቶች በሙሉ ቃላቸውን ካሠፈሩ፤ አብሯቸው ያለው ክፍል ሊጠይቃቸው መንገድ ከፈቱ ማለት ነው። ድክመት አላቸው ማለትም እንችላለን፤ መስፈሪያ አለንና! ታዲያ እኔ እኮ ያልኩት፤ እስኪ በመጀመሪያ በነዚህ አምስት ነጥቦች ላይ ስምምነት ላይ እንድረስ ነው። ተግባብተናል መስሎኛል። ወደ ልዩነታችን አመራለሁ።

አቶ ጋሻው እንዲህ ይላሉ፤

“IV. ከላይ የተጠቀሱትን አላማዎች ለማሳካት ከምንም በላይ ሰላማዊ የትግል ስልት መከተል አስፈላጊና ተገቢ ነው። . . .” ይቀጥሉና ደግሞ . . . “ሌላው ቁም ነገር እስካሁን እኔ እስካለኝ መረጃ ድረስ በትጥቅ ትግል ስልጣን የተቆናጠጡና ዴሞክራሲዊ ስርአትን ያሰፈኑ ኃይሎችን አላቅም። እንደማስበው ከሆነ ግን ይህ የሆነበት ምክንይት ጦርነት በራሱ ግቡ ሁሉንም አሸናፊ የማያረግና ከጦርነት በኃላ እነርሱ ( ጠላት ) እና እኛ የሚል አስተሳሰብ የሚያሰፍን በመሆኑ ነው። ይህም ጸረ- ዴሞክራሲያዊ ባህል እንዲያብብ እድል የሚከፍት ነው።”

ቅሬታዬን በግልፅ ላስቀምጥ። አቶ ጋሻው ከቅኝ ግዛት ነፃ ለመውጣት የተገሉትን አስመልክተው እንዲህ ባሉት ላይ፤ “ከፍተኛው የቀኝ ግዛት አስተዳደር ስልጣኖች ለቀኝ ገዢዎቻቸው የተተወ በመሆኑ የስልጣን መሰላሉ ላይ ወደ ላይኛው እርከን ማደግ ባለመቻላቸው ቅር የተሰኙ ሰዎች ናቸው።” ይህ አባባል፤ ከቅኝ ገዥዎቻቸው ነፃ ለመውጣት ያደረጉትን ትግል የሚያንኳስስ ሆኖ ስላገኘሁት ቅሬታ ተሰምቶኛል። በዕርግጥ አቶ ጋሻው በኋላ የሰዎችን ምግባር ተመልክተው የሠጡት መደምደሚያ እንደሆነ እረዳለሁ፤ ቢሆንም ግን በዚህ መልኩ ይኼ መቀንቀን የለበትም።

በሌላ በኩል የደቡብ አፍሪቃን ትግል አስመልክቶ እንዲህ ሲሉ አስቀምጠዉታል።

“በሌላ በኩል፣ ጋናን እና ደቡብ አፍሪካን እንዲሁም ዛሬ የተሻለ ዴሞክራሲ አለባቸው የሚባሉ ሃገሮችን የሚመለከት ሰው የሚገነዘበው ነገር ቢኖር ከአንባገነንና ከአፓርታይድ ስርአት ወደ ተሻለ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ያመሩበት መንገድ ስላማዊ ትግል ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው። ስለዚህም የዴሞክራሲያዊ ስርአትን ለማስፈን የሚደረግ ትግል ከጸረ-ቀኝ ግዛት ትግል ጋር ማመሳሰሉ በጣም አስቸጋሪ ነው:።” በመጀመሪያ ደረጃ የደቡብ አፍሪቃን ነፃነት ከአፍሪቃ ብሔራዊ ኮንግሬስ ለይቶ ማስቀመጥ፤ የአፍሪቃ ብሔራዊ ኮንግረስን ከኡምክሆንቶ ዊ ሲዚዌ ( Umkhonto we Sizwe – Spear of the Nation) ለይቶ ማየት አይቻልም። የዚህ የኡምክሆንቶ ዊ ሲዚዌ አቅምና ድርጊት ለአፓርታይድ ውድመት ምን ያህል አስተዋፅዖ እንዳደረገ ያጠና፤ የትጥቅ ትግልን ሚና ሊዘነጋ አይችልም። የደቡብ አፍሪቃዊያን ነፃነት በሰላምም ሆነ በውጭ ሀገሮች ተዐቅቦ የተገኘ አይደለም። የቮርስተር መንገስት ሲወጠር የመጨረሻ ምርጫው ሆኖ ስላገኘው ነው።

በርግጥ ከአቶ ጋሻው አለሙ ጋር የምስማማው፤ ይኼ የደቡብ አፍሪቃ ትግል ከቅኝ ግዛት ነፃ ለመውጣት የተደረገ ትግል ነው። ለኔ ደግሞ፤ ከአምባገነኖች ጋር የሚደረገው ትግል፤ በሕዝቡና በአምባገነኖች፤ በግልፅ በሁለት መከፈልና ትግሉ መፋፋም አለበት። እዚህ ላይ ላጠብቀው የምፈልገው፤ በምንም ሰዓት ቢሆን፤ ሰላማዊ ትግል ቀደምተኛና የማያቋርጥ መሆን እንዳለበት ነው። በቅኝ ግዛትም ሆነ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማምጣት የሚደረግ ትግል፤ አይለወጤው ስልት ሰላማዊ ትግሉ ነው። የትጥቅ ትግሉ የሚቀነቀነው፤ በገዢዎችና በሕዝቡ መካከል ያለው ቅራኔ ተካሮ፤ የአጥፊና ጠፊ ደረጃ ላይ ሲደርስ ብቻ ነው። የቅኝ ግዛትም ሆነ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ፈላጊዎች ትግል፤ ተካሮ የመጨረሻው ላይ ሲደርስ፤ ያን ደረጃ ላይ፤ የሕዝቡን ታጥቆ መነሣት ግድ ይላል። እንዴት መታጠቅና መነሣት እንዳለበት፣ ስለ አመራሩና ስለአካሄዱ፤ ከሰላማዊ ትግሉ ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት፤ የያንዳንዱ ትግል የራሱ የሆነ መንገድ ይኖረዋል። እዚህ ላይ እኛ የመንወያየው በሃሳብ ደረጃ ነው። በሃሳብ ደረጃ ደግሞ፤ ሌላ ቦታ ተሳካም አልተሳካም፤ በትክክል ተካሄደም አልተካሄደም፤ አማራጭነቱ አይሰረዝም። በርግጥ እንዴት መሆን አለበት? የሚለውን ጉዳይ በሌላ ጊዜ መነጋገር እንችላለን፤ እዚህ ላይ ላሠምረው የምፈልገው፤ አማራጭነቱ መሠረዝ የሌለበት ግዴታ ነው ብዬ ነው።

የሌሎች የትጥቅ ትግሎችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የማስገኘትን ወይንም አለማስገኘትን ጉዳይ ወደ ኋላ እንተውና፤ ለምን የትጥቅ አስፈላጊ ነው በሚለው ላይ ሃሳቤን ልሰንዝር። የገዥው ክፍል በሕግና ደንብ የሚመራና፤ ራሱ የሚያወጣቸውንና ዓለም አቀፍ ሕጎችን የሚያከብር ሆኖ ሲገኝ፤ ሰላማዊ ትግል አንደኛና ትክክለኛው መንገድ ነው። የተጣመሙና ለሱ የሚረዱ ቢሆኑም እንኳ፤ ሕዝቡ የገዥው ክፍል ራሱ ባወጣቸው ሕጎች ተገዝቶ አቸናፊ ይሆናል። ማኅተመ ጋንዲ እንግሊዞችን ሊያንበረክኩ የቻሉት፤ እንግሊዞቹ የማይደፍሯቸው መሠረታዊ ሕጎች ስለነበሩዋቸው ነው። በሌላ በኩል፤ አምባገነኖች ባሉበት ቦታ፣ ሕግ ትርጉም በሌለው ቦታ፣ ገዥው ክፍል በፈለገው መንገድና ሰዓት ሕጎቹን የሚቀያይርና የማያከብር በሆነበት ቦታ፤ ሰላማዊ ትግሉ ከሮ አንድ ደረጃ ላይ ሲደርስ፤ ከሰላማዊ ትግሉ ጎን፤ ሕዝቡ ራሱን መከላከያ ማዘጋጀቱ ግዴታ ነው።

አንድ ሀቅ በግልፅ መቀመጥ አለበት። በሥልጣን ለይ ያለ ቡድን፤ ራሱን በቋሚ መንግሥትነት አስመስሎ፣ ራሱን በሀገሪቱ ሕልውና አስመስሎ፤ እኔን መንካት ሀገሪቱን መንካት ነው፣ እኔን መንካት የሀገሪቱን መንግሥት ሕልውና መንካት ነው ብሎ እስከመጨረሻው ሕዝቡን እየጨረሰ በሥልጣን ለመቆየት ከወሰነ፤ ያለ አማራጭ ይህ እኛና እነሱ የሚል ክልል ይፈጥራልና፤ ወይ መጥፋት ወይ ማጥፋት የዕለቱ ጨብጥ ሀቅ። እናም በዚህ ሰዓት፤ ሕዝቡ ትጥቅ ማንሳት ግዴታው ይሆናል – ሕልውናውን ለመጠበቅ። ይኼን ካላደረገ፤ ሕዝቡ ጠፊ ይሆናል ማለት ነው። ይኼን የመሰለ ቡድን፤ የትግሉን ምንነት ይቀይረዋል። ከቅኝ ገዥዎች ያልተለዬ ነው። በመሆኑም፤ ትግሉ ራሱ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ከመሆኑ አልፎ፤ የነፃነት ጥያቄ ይሆናል። የነፃነት ጥያቄ ደግሞ በልመና አይፈታም። አሁንም፤ የነፃነት ጥያቄ፤ የተለያዩ ቡድኖች በየራሳቸው የሚያደርጉት ትግል ከሆነ፤ ውጤቱ የጉልቻ መቀያየር ብቻ ይሆናል። ሀገራዊ አንድ ድርጅት አማራጭ የሌለው ግዴታ ነው።

ይኼን ስል፤ በሀገራችን ሰላማዊ ትግሉ ተሟጦ አልቆለታል ወይንም የትጥቅ ትግሉን የሚያካሂድ ሕዝባዊ ክፍል አለ ከሚል እንዳልሆነ አንባቢ ይረዱልኝ። በኔ እምነት የትጥቅ ትግሉን በሕዝብ ስም ሊያካሂድ የተዘጋጀ ክፍል የለም። ሰላማዊ ትግሉ የትጥቅ ትግል አጋር እያስፈለገው መምጣቱን ግን እቀበላለሁ። ችግራችን ግን፤ ሰላማዊ ትግሉንም በትክክል የሚመራ የሕዝብ የሆነ አንድ አጠቃላይ ማዕከል የለንም። ይኼ በሌለበት የትጥቅ ትግሉን የሚመራ ክፍል ማግኘት ምኞት ነው። አስፈላጊነቱ ግን ጊዜው ነው።

አንዱ ዓለም ተፈራ

ጥር ፮ ቀን ፳፻፭ ዓመተ ምህረት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    January 17, 2013 11:40 am at 11:40 am

    There is only Ethiopian people who speaks different languages and religion. Ethiopian elites are trying to promote their masters agenda of disintegrating Ethiopia. Yes there is injustice in Ethiopia before and now and the point should be how to build a free and democratic Ethiopia without any ethnic and religious dominance. The Americans did not try to disintegrate the USA of Washington instead they tried to democratize it so that all live freely and equally. Menelik is the Bismarck of the Black race and his admired and hated depending on how you see it. He is hated by the WEST as a symbol of liberty for all the black race and his loved by the black and other freedom loving people for saying no to Colonialism.
    As in USA, there has been bloodshed in the making of Ethiopia. Sadly enough blood is even now shed by the home grown fascists who are promoting ethnic supermacy/Tigrian in the name of federalism and ethnic equality.
    21 years of rule/misrule by cheating, looting and terrorizing should be stopped. What the woyane ethnic fascists are doing in the name of the Tigrians is not beneficial even for the Tigrians themselves. We are in 21st Century and slavery or ethnic/religious dominance should not be allowed and all peace loving Ethiopians should stand against the home grown fascists. http://vimeo.com/18242221
    http://www.ecadforum.com/2012/12/19/from-ethnic-liberator-to-national-atrocities-the-tale-of-tplf
    http://www.ethiotoday.eu/politics.html
    http://www.ethiomarket.com/effort/effort_companies.htm
    http://www.ecadforum.com/articles/torture-and-arbitrary-detention-in-ethiopia
    http://www.genocidewatch.org/ethiopia.html

    Reply
  2. አንዱ ዓለም ተፈራ says

    January 18, 2013 04:00 am at 4:00 am

    በቀረበው ሃሳብ ሙሉ ለሙሉ እስማማለሁ። ትክክል ቀርቧል። ቁም ነገሩ፤ ሁላችን የምንስማማባቸው ሀገራዊ ዕሴቶች አስቀምጠን፤ ለነዚህ ነው የምንታገለው ብለን ካልተነሳን፤ የጥቅል ትግሉ ተንገዳጋጅ ነው። ለዚህ የረዳ ዘንድ አምስት ነጥቦችን አቅርቤያለሁ። እነዚህ ነጥቦች ፍፁም አይደሉም። ሊስተካከሉ ይችላሉ። ቁጥራቸውም ሊለወጥ ይችላል። ቁም ነገሩ ግን፤ እስኪ ጉዳያችን ብለን እንወያይባቸው ነው።
    ፩ኛ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብን አንድነት በተመለከተ፤ አንድ ሕዝብ ነን ወይንስ አይደለንም?
    ፪ኛ፤ ሀገራችንን በተመለከተ፤ ኢትዮጵያ፤ የቆዳ ስፋቷና ክልሏ ተጠብቆላት፤ አንድ ሀገር ናት ወይንስ አይደለችም?
    ፫ኛ፤ የዴሞክራሲያዊ መብትን በተመለከተ፤ እያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ የግለሰብ መብቷ ተከብሮላት፣ በየትኛውም የሀገሪቱ ክልል ሠርታ የመጠቀም፣ መኖሪያ የማበጀት፣ ሀብት የማፍራት፣ በኢትዮጵያዊነቷ (ከሃይማኖትና የዘር ትውልድ ባልተዛመደና ማንኛውንም ኢትዮጵያዊ በማያገልል መንገድ) ከመሰል የአስተሳሰብ አንድነት ካላቸው ኢትዮጵያዊያን ግለሰቦች ጋር የፖለቲካ ተሳትፎዋን ማድረግ የምትችልበት እንድትሆን ነው ወይ ትግሉ?
    ፬ኛ፤ የሕግ የበላይነትን በተመለከተ፤ ከግለሰቦችና ድርጅቶች ውጪ፤ በሕገ ደንብና አሠራር ለመገዛትና ለመተማመን ነው ወይ የምንታገለው?
    ፭ኛ፤ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን በተመለከተ፤ ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ጠላት ዘረኛው አምባገነን የወያኔ አስተዳደር ነው። ይህ መንግሥት ሊታረም የማይፈልግና የማይችል ነው። ይህ መንግሥት መወገድ አለበት ወይስ የለበትም?

    Reply
  3. ዱባለ says

    January 18, 2013 09:42 pm at 9:42 pm

    እኔ እንደሚታየኝ ለነዚህ አምስት ጥያቄዎች መልስ መስጠት አሁን ላለው ችግር ምንም መፍትሄ አያስገኝም:: ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት የፕኦለቲካ ልዩነቶች ጎልተው ወጥተው ሁሉም በፕኦለቲካው ጎራ የራሱ መልስ አለው:: በአብዛኛው በህገር ውስጥ በሚኖረው በዝምታ የሚኖረው ህዝብን ስነ ልቦና ያጤነው ከሆነ ለተዘረዘሩት ጥያቄዎች በሙሉ አዎንታዊ መልስ ያገኛል:: የኢትዮጵያን አንድነት እያለ የሚዖህው ወገን ለብሄረሰብ መብት እታገላለሁ የሚለውን ጨምሮ አዎንታዊ መልስ ይሰጣል:: መገንጠልን እንደ ብሄረስብ መብት አድርጎ የሚታገለው ወገን አሉታዊ መልስ ይሰጣል:: ወያኔ ኢትዮጵያን 20 አመት ገዝቶ እንኳ የመሪዎቹ ትክክለኛ አቋም እስከ አሁን ድረስ ግልጽ አይደለም:: የሚያደርጉት ሁሉ ስንመለከት የአንድነት ስሜት አይታይባቸውም:: ለዚህ ይመስለኛል የከረረ እርምጃ በማንኛውም የአንድነት አቀንቃኝ ላይ የሚወስዱት:: ይሄ እንደተጠበቀ ሆኖ ትልቁ ጥያቄ ሁሉንም ጥያቄዎች በአዎንታዊ የሚመልሱት ወገኖች ለምን ተስማምተው አንድ በሆነ ሀይል አሁን ያለውን የወያኔ መንግስት መታገል አቃታቸው ነው:: ለዚህ ትልቅ ችግር ነው መልስና መፍትሄ መፈለግ ያለብት:: ለአንድነት ከሚታገለው ይልቅ ለመገንጠል የሚታገለው የበለጠ መተባበር ያሳያል:: በኔ አመለካከት ለዚህ አለመስባስብ ዋናው ችግር ያለው የግሩፕ ስነ ልቦና በተቃዋሚ መሪዎችና አባሎቻቸው ላይ ስለሚያይል ነው:: ይሄንን ስነ ልቦና ነው ማኮላሽት የሚያስፈልገው::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule