1. መግቢያ
የጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊን ህልፈተ-ህይወት ተከትሎ በኢህአዴግ እና በተቃዋሚ ኃይሎች የሚታየው የመረበሽና ትርምስምስ በመሰረታዊነት ምንጮቹ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ቢሮክራሲያዊ ስልጣኖችን በአጠቃለለ ሁኔታ ጠ/ሚ መለስ በእጃቸው ማስገባታቸውና በእሳቸው ህልፈተ-ህይወት ምክንያት የተከፈተውን የስልጣን ክፈተት የሚሞላ ተቋማዊ አቅም አለመገንባቱና ሁለተኛ ግለሰብ በስርአቱ ውስጥ አለመኖር ናቸው:: ስለዚህም በእርሳቸው ህልፈተ-ህይወት የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት… (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል)
በለው ! says
፩)”የሞቱትጠ/ሚር አለመኖር በገዢው ሃይል ውስጥ የሚከፍተው ክፍተት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊሞላ የሚችልና ውስጣዊ የስልጣን ሽግግሩ በቀላሉ ሊካሄድ የሚችል አይደለም::
**ክቡርነትዎ መጀመሪያ …የሥልጣን መደላደል፣መተካካት፣ዝውውር፣መወራረስ፣መቧደን ያጥኑ ያጥናኑ(መልስ: group leadership)የአንድ ሀገር ከተማና የሠፈር ልጅ ፤በአቻ ጋብቻ፤ በታማኝነት ላይ የተመሠረተ ማለት ነው።አራት ነጥብ። (ኃይለመልስ ፡collective leadership) የባለዕራዩን ትምህርት በአጥንኦት የተከታተለና በቂ ግንዛቤ ያገኘ በቅርብ የተገኝ ወዳጃችን ሁሉ ይመራል።”ሥራው ከባድ ነው ከኋላም ከፊትም ሆናችሁ ምሩኝ”፩ኛ/ የሱኳር ሚኒስትሩ የሃይማኖት ጉዳይ አስፈፃሚና በላይ አካል ፪/የመንግስት ኮምንኬሽን ቃል አቀባይ የሱዳን የሰላም ውል አፈራራሚ በረዳት ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ ፫ኛ/ኃይለማርያም ደስአለኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በጠ/ሚኒስትር ማዕረግ ፬ኛ/ዶ/ር ገብረጺዮን ገ/ሚካኤል ረዳት ጠ/ሚ በም/ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚና የክላስተር ቦንብ አጥማጅና የመገናና ኢንፎርሜሽን ሚ/ር በዚህ መልኩ እንግዲህ (አመራር በደቦ)ተወቃናት በለው!
፪) “ሁሉም ተቃዋሚ ኃይሎች የሚያነጣጥሩት ስርአት ስለመቀየር እንጂ በምንመልኩ መሬት ላይ ያለውን ፖለቲካዊ ስርአትና ባህል በመሰረታዊነት ስለመለወጥ አይደለም::”
**ይህ የሚገርም! የሚያሳዝን! ብቻ ሳይሆን አስቂኝም ነው!!። የርዮተዓለም ሥም ማብዛት ከቃላት ማብዛትና የሰውደም ብዛት ከመጨመሩ በስተቀር ፋይዳ የለውም።ሥርዓት መቀየር ሰው ከመቀየር ጋር የተያያዘ (የዱላ ቅብብል)አደለም መሠረታዊ ለውጥ መሚየለያዩና ቅራኔ በሚፈጥሩ የጋራ የዕድገት እና አብሮ መኖርን ጠላቶች ለማስወገድ ካለፈው ሥርዓትም ሆነ አሠራር በተሻለ መልኩ መቀረፅ አለበት። የሠፊው ሕዝብ ፍላጉትና ምኞት እንጂ የግለሰብ ራዕይ አስፈላጊም አደለም።የህን ከማድረግ ፈንታ ተፎካካሪው ጎራ ይባስ ገዢው መንግስት እንዴት መደራጀት እና መተካካት እንዳለበት የሕገ መንግስቱን ፅሁፍ ሲያብጠለጥሉ እንጂ እኛ የተሻለውን የመሥራት ችሎታና ብቃት አለን የሚሉ((ከጥቂት ግለሰቦች በስተቀር)) እምብዛም አልተደመጡም ይህንኑ አጋጣሚ ኢህአዴግ በመጠቀም” የምታውቁትን ሁሉ ንገሩን ተባበሩን እኛ እናስፈፅመዋለን”፤ ሲልም በድፍረትና በቁጣ ሲናገር ይሰማል።በዚህም ጊዜ ደንግጠው “ሁላችንም ተፎካካሪዎች አንድ አይነት አመለካከት እና ንድፍ የለንም” ብለው እጅ ወደላይ ሲሉም (ኢዴፓ)አይተን ስቀን ተሳቀናል።ሌሎችንም ሲደነብሩም በእየተራ ነጣትሎ በልቷቸዋል።
፫) “የብሔር ብሔረሰቦች ጥያቄ የያ ትውልድ እንዲሁም የአሁኑንም ትግል ማዕከላዊ አጀንዳ ነው:: ይህ ጥያቄ በሶሻሊስታዊ በተለይ ደግሞ በሌኒኒስታዊ-ስታሊኒናዊ ዕይታ…
**’ሌኒንና ስታሊን’ የኢትዮጵያን የብሔር ጥያቄ ለማስታወስም ይሁን ለችግሩ መፍትሔ ለማድረግ የወሰደባቸው ጊዜ ያጡት እንቅልፍ በሰዓት ተቀምሮ አልተደረሰበትም። የፈለፈሉልን ተምቾች ወታቦአቸው እዚያ እንደነበር ታሪክ ይናገራል በለው! ህወአት,ሻቢያ,ኢህአዴግ,ኢህአፓ፣መኢሶን እና የዋለልኝ ቀደዳ በውል ባይታወቅም ለአንዳንድ አጭበርባሪዎች ጥሩ ቱልቱላ ለመንፋት የባንዳነት ተልዕኮአቸውን መሸፈኛ ሆኖላቸዋል!!።ታዲያ ቂጥ ገልቦ ከማንዛረጥ በቀር ብሔር ብሔረሰብ እና ህዘቦች ሸጡ አከራዩ እንጂ መች አተረፉ??
፬) “በአውሮፓውያን ፍልስፍና አድማስ እኔ ማለት እኔ ነኝ (I am because I am) ሲሆን፣ በአፍሪካውን ፍልስፍና ደግሞ እኔ ማለት እኛ (I am becasue we are) ማለት ነው::”
**’ኩረጃና ጉራ ጨርሶ አጫረሰን’ ኢህአዴግ የሚመራው በአውሮፓዎቹ ነው። እኔ የምናገረው የምፅፈው የማስበው ብቻ በቂ ነው እኔ ማለት እናንተ ናችሁ እና ህገ መንግስቱ ጽሑፍ መግቢያ ገፅ ፭ እና ፮ ያብራራል ። “በነፃ ፍላጎታችን በሕግ በላይነትና በራሳችን ፍቃድ ላይ በተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ ለመገንባት እንዲወክሉን መርጠን በላክናቸው ተወካዮቻችን አማካኝነት ኅዳር ፳፰/፲፱፻፹፯ አጽድቀነዋል።”መድብለ ፓረቲን ማን በላው በለው!” ለመሆኑ ሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ የትኛው ዳር ድንበር ላይ እንደሚቆም ይገልፃል? ?በህገመንግስቱ ሉዓላዊነት የተጻፈው ስለሀገሪቱ ነው ወይስ ስለግለሰብ? ታዲያ ጠ/ሚ ሲገልፁ ሀገር ማለት ወንዙ ሸንተረሩ ሜዳው ተራራው አደለም ሲሉን ይህ ሁሉ ‘ሌንንና ስታሊን’ የደከሙለት ኢህአዴግ ፈልጎ ያገኘው ብሔር የሚኖረው “እንደዓሳ በባሕር እንደአዕዋፍ በዛፍ ላይ” ይሆን?? ለዚህ ይሆን ከዳር ከዳሩ እየሰጡ መሃሉን ዳር ሊያደርጉ ቆርጠው የተነሱት??አዎን…!”ኢትዮጵያዊነትንና የብሔር ብሔርተኝነትን እንደ ሁለት የተለያዩ ማንነቶች ሳይሆን ተያይዘው በአንድነት ሊከበሩና ሊገለጹ የሚችሉ የአብሮነታችን ሁለትም አንድም፣ አንድም ሁለትም የሆኑ መብቶች ማድረግ በሚቻልበት መንገድ ላይ መስራት አለባቸው::”
፭) የእርቅና የመታደስ አስፈላጊነት…
**ለመሆኑ የሚጣላው ማን ነው ?ፀቡ ለምን እርቅስ ለምን አድዋ ሲዘመት ፀብ ነበር? ብሔር ተነስቶ ነበር? ይልቁንም እኔ ለሀገሬ ብሎ ተሰዋ! በዚህ በተሻለ የትብስ ትብሽ ያነድ ዓላማ ጎዞ እራሱ ኢህአዴግ አስታጠቃቸውን ዘጠኝ ባነዲራ ይዘው ዘጠኝ የፓረቲያቸውን ባንዲራ ጨምረውበት በአነገት ላይ ሻርፕ በካኒቴራና በቲሸርት ሀገሪቱን ሁልቀን ጃንሜዳ አደረጓት ምን ነበር የድሃው ልጅ ጥብቆ ቢሰፋለት ታዲያ ኢህአዴግ ውረድ ሳይሆን “ኢሰፓ ተነስ!” ማለት አይቀልምን?
፮)ውስጣዊ አቅምን በተመለከተ…”ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎችና ልሂቃኖች ልምድ ስንነሳ ግን በአብዛኛው የመናገኘው አስተሳሰብ ማደራጀት፣ ማስታጠቅና ማታገል የሚለውን ንድፈ-ሃሳባዊ ሃዲድ ነው::
**”ተደራጅ ፤ሰንቅ፤ ታጠቅ፤ዝመት፤ተዋጋ!” ሲባል ሠምተናል የድሃ ልጅ እንደቅጠል ረግፎ !ሆዳም ባንኮኒ ተደግፎ! የሴት ወገብ አቅፎ!ዘመን አለፈች በልፋፎ!… የተቃዋሚ ኃይል ለመቃወም ብቻ የሚቃወም የፖለቲካ ኃይል ሳይሆን የሚሆነው የገዢው መደብን ድክመቶችና ጥፋቶች እያመላከተ አማራጭ ሃሳብ የሚያቀርብ፤ከብዛት ጥራትን ከ፹፭ ወደ ፭ ዝቅ የፓርላማ ቁጥር ከ፭፻፶፯ ወደ ፫፻ ዝቅ ብሎ የሀገሪቱን ወጪም ማስተካከል ለመደማመጥም ያመቻል እንዲሁ በቁጥር ብዛት ቢያጨበጭቡና ቢገለፍጡ ምን ያደርጋል።?
፯)”ዶ/ር ነጋሶ በጻፉት ጹሁፍ ላይ “ህብረተሰባችን ብሶተኛና የሚያጉረመርም እንጂ ይህ ስሜቱ ወደ ህበረተሰባዊ ንዴት አልተለወጠም”! **ይህ የግለሰቡ ብቻ ሳይሆን የብዙሀኑ ጥያቄ ነው።ይህ ተሰጠውም ትረጓሜ በጭራሽ ትክክል አደለም ።ሕዝብ መምረጥ የመናገር መፃፍ መሰብሰብ መብቱ በመጣሱ ያጉረመርማል ሆኖም በኅበረት ሆኖ በሕገ መንግስታዊ ማለትም እራሳቸው ግለሰቡ ፈርመው ባፀደቁት ፅሑፍ ማለታአቸው ነው መብቱ እስከሆነ ድረስ በደሉን “በህብረተሰባዊ ንዴት”…(በአነድ ድምፅ)(ጮክ ብሎ)(መፈክርአሰምቶ)(ተሰብስቦ)(ሰልፍ ወጥቶ)(እጅለእጅ ተያይዞ)ድምፅ መጉሊያ ይዞ ስሜቱን መግለፅ መብቱ ነው አፉን ዘግቶ የተቀመጠው ተመችቶት ነው ?ፈርቶ ነው?ተሳቅቆ ነው?ተሸምቅቆ ነው? ቢሆንም መብቱ ነው!!።
፰)”የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ባህልና የተቃውሞ አደረጃጀት ታሪክ እንደሚያሳየው ከሆነ በወዳጅና ጠላት ክፍፍል ላይ የተመሰረተ ነው::”
**ይቺም አህአዴግ የሚነፋት ጡሩንባ ናት…”ተቃዋሞዎች እረስበእርስ አይስማሙም እንዴት ኢህዴግን ማሸነፍና ይህንን ታላቅ ሕዝብ መምራት ይችላሉ? ሲል ይሳለቃል እኔንም ሁልጊዜ ያስቀኛል…ሀገሪቱ ጠላቶች ብቻ የሚኖሩባት ናት ማለት ነው?ጠላት የሌለው የማይከፋፈል ወያኔ/ኢህአዴግ ብቻ ነው ማለት ነው?ታዲያ ሙሉ የራሱ አስተዳደር ,የኢኮኖሚ መዋቅር ያለውና ራስ ገዝ የጦርሠራዊት የመሠረተ፣ በልክ የተሠሩ አጋር ፓርቲ ያለው፣ሕዝብ የሚመለምሉለት የሃይማኖት ተቋም የፈጠረ፤የጦር መግዣ ወጪ የሚያደርጉ ኩባንያዎች እነዱስትሪዎች(በኢፈርት)በጥረት ከያዘ፣ተተኪ ትውልድ ዱላ ተቀባይ በውጭ ሀገር በህዘብ ገንዘብ ካስተማረ፣በመናቸውም አካከባቢ የመዘዋወር የመሸት መለወጥሙሉ ሥልጣን ያለው ዲያስፖራ(ፈላሽ)ከውጭ ካስገባ፣ከአውርቶ አደር እስከኪራይ ሰብሳቢ የሙሰኖች ተቋማት ከዘረጋ እና በማኅበር ካሳቀፈ ካስወለደ እና አስፈልፍሎ ካራባ ወሮ በላ እኩል የእስክሪብቶ አንጋች ተፎካካሪውን ለምን አስፈለገ ይህ ሁሉ ወቀሳና ሰደባ? ለመሆኑ ‘በሶ’ የጨበጠና ‘ቦንብ’ የጨበጠ አንድ ናቸውን? እየተስተዋለ! “አንገት የተሠራው አዘዋውሮ እንዲያይ ነው”። ስላሳተፋችሁን እናመሰግናለን!። በቸር ይግጠመን በለው!