• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል

September 27, 2023 08:41 am by Editor Leave a Comment

“በተፈጠረው የሰላም እጦት ክልሉ ከፍተኛ ገቢ እያጣ ነው” ሲል የክልሉ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ እየታየ ያለው የሰላም እጦት በኢንቨስትመንቱ ላይ ቀጥተኛ የኾነ ተጽእኖ እያሳደረ እንደኾነ ነው የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የገለጸው፡፡

እየታየ ያለው አለመረጋጋት ወደ ክልሉ እየገባ ያለውን እና ለመግባት በሂደት ላይ የነበረውን ኢንቨስትመንት እንደሚያስቀር ተገልጿል። ይህ ደግሞ በክልሉ ምጣኔ ሃብት ላይ ጉዳት እንደሚያስከትል ነው ቢሮው ያስገነዘበው።

የአማራ ክልል ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊ ይሄነው ዓለም እንዳሉት ሰላም የሌለው ክልል አልሚዎችን ሊስብ አይችልም፡፡ አልሚዎች ለዳግም ኢንቨስትመንት በተለይም አዳዲስ ማሽኖችን ለማስገባት ያላቸውን ፍላጎት እንደሚቀንስም አብራርተዋል፡፡

ሰላም ከሌለ ኢንቨስትመንቱ አትራፊ ስለማይኾን አዳዲስ የሥራ እድል መፍጠር እንደሚሳነው እና ምርትም ማምረት እንደማይቻል አስገንዝበዋል፡፡

አሁን ላይ ያለው አለመረጋጋት የጥሬ እቃ ዝውውርን እየገታ በመኾኑ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ማምረት እንዳልተቻለ የሚናገሩት የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊው ጉዳዩ የውጭ ምንዛሬን ለማግኘት አስቸጋሪ ነው ብለዋል፡፡

አቶ ይሄነው በሰላም መደፍረሱ ምክንያት ተጨማሪ ምርት አምርቶ በገበያው ላይ የሚታየውን የዋጋ መናር ለመቀነስ አስቸጋሪ እንዳደረገውም ነው ያስገነዘቡት፡፡

እየተፈጠረ ባለው ችግር ዋነኞቹ ተጠቂዎች ፋብሪካዎች ኾነዋል ፤ ይህም በፋብሪካዎቹ የሚሠሩ ሠራተኞችን ከሥራ እያፈናቀለ ስለመኾኑ ነው ያብራሩት፡፡ ባለፈው ጊዜ በተከሰተው አለመረጋጋት ብቻ ከ3 ሺህ በላይ የፋብሪካ ሠራተኞች ከሥራ ገበታቸው ስለመፈናቀላቸው ነው የገለጹት፡፡

በተለይም እስከ 8 የሚጠጉ የእርሻ ኢንቨስትመንቶች ላይ ጉዳት በመድረሱም ክልሉ እየተጎዳ ስለመኾኑ ነው ያስገነዘቡት፡፡

ከዘጠኝ በላይ በሚኾኑ የአበባ ልማት ዘርፎች ላይ ጉዳት በመድረሱ በዓመት ከ9 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መታጣቱንም አብራርተዋል፡፡

የክልሉን ኢኮኖሚውን ለማሳደግ በክልሉ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እና አሁን የተጀመረውን አንጻራዊ ሰላም ለማስቀጠል የሁሉንም የክልሉን ሕዝብ ለሰላም መረባረብን ይጠይቃል። (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara region, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule