• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ከአጎዋ መሰረዝ የአሜሪካ ኩባንያዎችንም አሳስቧል

December 7, 2021 11:17 am by Editor 1 Comment

አሜሪካ የአፍሪካ አገራት የተለያዩ ምርቶቻቸውን ከቀረጥ ነፃ ወደ ግዛቷ እንዲያስገቡ ከሚፈቅደው የአጎዋ ዕድል ተጠቃሚነት ኢትዮጵያን ለመሰረዝ መወሰኗ በአሜሪካ አልባሳት እና ጫማ ኢንዱስትሪዎች ላይ ድንጋጤ ፈጥሯል ተባለ።

የአሜሪካ አልባሳት እና ጫማ ማኅበር (AAFA) የቦርድ ሰብሳቢ፣ ፕሬዝዳንት እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ያገለገሉት ሪክ ሄልፌንቤይን ፎርብስ መጽሄት ላይ እንደፃፉት ውሳኔው ትልቅ ስህተት ነው ብለውታዋል።

ውሳኔው ማንም ያለጠበቀውና የአሜሪካ አልባሳት እና ጫማ ኢንዱስትሪዎች በአፍሪካ ያደረጉትን ኢንቨስትመንት ዋጋ የሚያሳጣ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት አሜሪካ አጎዋን የአገራትን ለመጫን እንደ መሳሪያ እየተጠቀመችበት መሆኗን ነው ሄልፌንቤይን በጽሁፋቸው የገለጹት። ይህ ደግሞ ፍጹም ስህተት ነው ሲሉም አካሄዱን እንደተቃወሙት ነው ኢዜአ የዘገበው።

አሜሪካ የአልባሳት እና የጫማ ኢንዱስትሪዎች በኢትዮጵያ መዋዕለነዋያቸውን እንዲያፈሱ አሜሪካ ስታበረታታ መቆየቷን አውስተው አሁን ግን ኩባንያዎች ከአገሪቱ ስለመውጣት እንዲያስቡ መፈለጓ ተገቢነት የለውም ብለዋል።

ኢትዮጵያ ያጋጠማትን ቀውስ ተከትሎ አሜሪካ እንዲህ ዓይነቱን ውሳኔ መወሰኗ በርካታ ባለኃብቶችን ለምን ሲሉ ጥያቄ እንዲያነሱ እንዳስገደዳቸው ገልጸዋል።

በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲህ ዓይነቱ ድንገተኛ ውሳኔ መወሰኑ ሌሎች ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት በኢንቨስትመንት መስክ በተሰማሩ ባለኃብቶች ላይ ሥጋትን ስለመደቀኑ ጠቁመዋል።

ውሳኔው አሜሪካ እኤአ በ2025 አጎዋን እንደማታራዝም ፍንጭ የሰጠ ከመሆኑ ባለፈ በአፍሪካ ለተሰማሩ አሜሪካውያን ባለኃብቶች የመንግሥት ድጋፍ እንደሚያሳጣቸው ነው ስጋታቸውን የገለጹት።

“ሃቁን ለመናገር አጎዋ አሜሪካ ከፈጠረቻቸው የንግድ መርሃ ግብሮች የላቀ ፋይዳ ያለው አይደለም” ያሉት ሄልፌንቤይን፤ ለ21 ዓመታት የአጎዋ አፈፃጸም በተወሰነ ደረጃ ደካማ እንደነበር በማሳያነት አንስተዋል።

እንዲያም ሆኖ በርካታ አገራት የአጎዋ ዕድል ጠቃሚ ሆኖ እንዳገኙት ነው ያስረዱት።

እናም አሉ ሪክ ሄልፌንቤይን አጎዋ ለአሜሪካውያን ሆነ አፍሪካውያን ያመለጠ ዕድል ሆኖ እንዳይቀር እስከ ጥር ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ አሜሪካ ውሳኔውን ዳግም ልታጤነው እንደሚገባ አሳስበዋል።

ሪክ ሄልፌንቤይን ከአንድ ሺህ በላይ ዓለም አቀፍ ዝና እና ዕውቅና ያተረፉ የምርት ስሞችን የሚወክል ማህበር በሊቀመነበርነት የመሩ ሲሆን ከኢንዱስትሪዎች ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሜሪካ መንግሥት ጋር በቅርበት ሲሰሩ ቆይተዋል።

በተጨማሪም የበርካታ እውቅ (ብራንድ) ፋሽን ኩባንያዎች ፕሬዝዳንት ሆነው ከማገልገላቸው ባለፈ በ CNBC፣ CNN፣ Bloomberg፣ BBC እና Fox News የኢንዱስትሪ ትንታኔ በማቅረብ ይታወቃሉ። (AMN)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: AGOA

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    December 31, 2021 01:38 pm at 1:38 pm

    የባይደን መንግስትና የቢል ክልንተን የሆባማና የናንሲ ፔሎሲ የግል ስውር ድርጅቶች የኣሜሪካንን አቋም ኣሳዩም በኣሜሪካ መንግስት ጀርባ ላይ ተቀምጠው የግል ጥቅማቸውን ከማሳደድ በቀር ለኣሜሪካ ሕዝብም ሆነ ለዓለም ሰላም ደንታ የላቸውም። በዓለማችን ካደረሱት ግፍ የተነሳ ረጅም ዕድሜ የላቸውም። ቡሽ ተሰናብቶ ይህችን ዓለም ተሰናብቶ ላይመለስ ሄዶኣል። ለጥቁሮች ሰቆቃ ምክንያት የሆነው ሱዛን ራይስና ሆባማ እስካ ኣሉ ድረስ ኢትዮጵያ እረፍት ኣታገኝም። ለአገራችን ሰላም ሲባል ያልጠበቁት፣ ያልስተዋሉት በድንገት የሆነ ለውጥ በኣሜሪካ ይመጣል እነዚህ ሁሉ የመከራችን ምክንያት የሆኑቱ የጥልቁ የስውር መንግስት ለኣንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ይጠፋል። ቀኑ ደርሶኣል መለከት ሊነፋና ድሉን ተጠባበቁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule