• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ!

February 10, 2023 12:48 am by Editor 3 Comments

ጃዋር መሐመድ “የኦሮሞ ፕሮቴስት” ብሎ የጀመረ ሰሞን ብዙ የፌስቡክ ተከታታይ አልነበረውም። ወዲያው አገር ቤት ከኦህዴድ ጋር በነበረው ግንኙነት የተቃውሞ ሰልፎችንና የፖሊስ ግፎችን የሚያሳዩ ፎቶዎችን መለጠፍ ሲጀምር የተከታታዩ መብዛት ጀመረ።ዝግጅቱም፣ ትምህርቱም፣ ሥራውም፣ በሚዲያ ዙሪያ ስለነበር ሚዲያን እንዴት እንደሚቆጣጠርና የሕዝቡን ቀልብ እንዴት እንደሚስብ ጠንቅቆ ያውቅ ነበር። በመሆኑም ከማኅበራዊ ሚዲያ እስከ ዋንኛ (mainstream) ያለውን በቀላሉ ተቆጣጠረው። ለመረጃ፣ ለዘገባ፣ ለዜና፣ … እንደ ምንጭ የሚጠቀስ ሆነ። ትልልቅ የሚባሉት የውጪዎቹ የሚዲያ አውታሮች እሱን ሳያናግሩ ዜና መሥራት አልታያቸው አላቸው። በፍጥነት ወጣ፣ ተመነደገ፣ ከፍ አለ! የዚያኑ ልክ እሱም እያበጠ መጣ።

ዕብጠቱ ገና አፍላ በነበረበት ጊዜ ባደባባይ የዕብሪት ንግግር ለጠፈ። አሁን በማላስታውሰው አንድ ከተማ በተደረገ የተቃውሞ ሰልፍ ተማሪዎች ወጥተው ነበር። ትህነግ አሰልጥኖ ያሰማራቸው የአጋዚ ፖሊሶች ለደረታቸው ተኩሰው የተወሰኑትን ይገድላሉ። የሞቱትን ልጆች ፎቶ እንደተላከለት ጃዋር ወዲያው በፌስቡክ ገጹ ለጠፈው። ፎቶው መሬት ላይ የተዘረሩ በአስራዎቹ የዕድሜ ክልል የሚገኙ ወጣቶች በደማቸው ተነክረው የሚያሳይ እጅግ ዘግናኝ ነበር። ከፎቶዎቹ ጋር  እንዲህ በማለት በእንግሊዝኛ ለጠፈ፤ “ጨምራችሁ ግደሉ ሒሳቡ በእኛ ነው”። ይህንን ሲል እርሱ በሞቀ ቤቱ በአሜሪካ ሜነሶታ ጠቅላይ ግዛት ደኅንነቱ ተጠብቆ እየኖረ ነበር።

ዕብሪተኛው በዚሁ ቀጥሎ አገር ቤት ከገባ በኋላ “ሁለት መንግሥት ነው ያለው” ብሎ እስከመናገርና ራሱን እንደ አገር መሪ እስከ መቁጠር ደርሶ ነበር። ሌላም ብዙ መጥቀስ ይቻላል። ወደ አገር ሲገባ ከነበረው ወደ አንድ ቢሊዮን የሚጠጋ ጥሬ ብር በተጨማሪ ሌሎች በርካታ የገቢ ምንጮች ነበሩት። ይህም የእብሪት ፊኛውን ለመወጠር አዎንታዊ አስተዋጽዖ ያደረገ ነበር።

የ21ኛው ክፍለ ዘመን አሕመድ ግራኝ ነኝ ሲል የነበረው ጃዋር አሁን የት ነው? ገና በወጣትነቱ የተጠናወተውን በሽታ እያስታመመ፤ አመጋገቡን እየተቆጣጠረ፤ ደግ ደጉን እያወራ ተራራ የሚወጣ (ኪሊማንጃሮን ማለቴ ነው) ኃላፊነቱን የተገነዘበና በትጋት የዜግነት ድርሻውን የሚወጣ “መልካም ወጣት”፣ ጥሩ የሕግ ታራሚ ሆኗል።

ዘመድኩን ይህንን ሁሉ እንደ መግቢያ የጻፍኩት አንተ ራስህን ልክ እንደ ጃዋር ጊዜ “የኦሮሞ ፕሮቴስት” የሰሞኑ “የኦርቶዶክስ ንቅናቄ” ተብሎ በተሰየመልህ አጀንዳ ራስህን መሪ እያደረግህ በመምጣትህን በማየቴ ነው። በነገራችን ላይ ስሜን ያልነገርኩህ ፈርቼ ወይም በሃሰት መረጃ በድብቅ አንተን ለማጥቃት ሳይሆን ያንተን ያህል ባይሆንም የተወሰነ የሚያውቀኝ ሰው ስላለ ነገር ላለማባባስ ነው። እኔና አንተ ግን በደንብ ነው የምንተዋወቀው። አሁንም በአጻጻፌ በደንብ ልታውቀኝ ትችላለህ። በበርካታ ጉዳዮች ላይ ብዙ ተከራክረናል፤ “ተው ተጠንቀቅ፤ እንዳትጠለፍ” እያልኩ መክሬሃለሁ፣ አስመስክሬሃለሁ።

በቤተክርስቲያናችን የደረሰውን አስከፊና አንገት አስደፊ ነገር የእኔን እና የበርካታ ተዋህዶ ልጆችን ቅስም የሰበረ ነው። እንዳንተ እየወጣን አዛኝ ተቆርቋሪ መስለን አጀንዳ ፈጻሚ ባንሆንም መከራና ስቃያችንን ለሚያይ አምላክ በየሰዓቱ እንቃትታለን። አንተ ግን ለተዋህዶ ቤታችን የተጨነቅህ መስለህ የምትጽፋቸው እጅግ ዘግናኝ ልጥፎች እጅግ የዘቀጡ ናቸው።

በቴሌግራም ብዙ ተከታዮች አሉህ። ሰሞኑን በቲክቶክ ደግሞ ዝነኛ ሆነሃል፤ ተከታዮችህ እና የቀጥታ ሥርጭቶችህ ተመልካች ቁጥር በሚያስገርም ሁኔታ በፍጥነት አድጓል። እንዲያውም በቲክቶክ መንደር የአንደኛነትን ደረጃ መጎናጸፍህን ራስህ በቴሌግራምህ ላይ ለጥፈሃል። እንኳን ለዚህ በቃህ። ግን አትርሳ የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም።

የመረጃ ድርቀት ስላለብህና ከስድብ በስተቀር ከዕውቀትም የጸዳህ ስለሆነ አንዲት ነገር ልጥቀስልህ። የዛሬ 11 ዓመት አካባቢ በመጋቢት ወር ውስጥ (እኤአ 2012) አንድ አሜሪካዊ ጋዜጠኛ የዩጋንዳ አማጺ ቡድን መሪ የሆነው ጆሴፍ ኮኒ እንዴት ሕጻናትን ለውትድርና መልምሎ ግፍ እንደሚሰራባቸው የሚያሳይ ቪዲዮ ለቀቀ። በሁለት ቀናት ውስጥ 30 ሚሊዮን ተመልካች አገኘ። ይህ በዕቅድ የተለቀቀው ቪዲዮ በኋላ ለእንዴት ዓይነት መሰሪ ተግባር ታቅዶ ለዕይታ እንደቀረበና የተሠራውም ለህጻናቱ ታስቦ ሳይሆን ወረራ ለመፈጸም እንደሆነ በኋላ የታወቀ ሆኗል። አትርሳ የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም።                

በማኅበራዊ ድረገጾችህ ያለማቋረጥ ትጽፋለህ፤ ስትጀምር በተለመደው ኦርቶዶክሳዊ ቡራኬ ነው፤ ከቡራኬው በኋላ ግን በአማርኛ መዝገበ ቃላት ውስጥ ያሉት ለስድብህ ስለማይበቁህ የራስህን ጨምረህ እጅግ ጸያፍ ስድብ ትሳደባለህ። ተከታዮችህን በመንፈሳዊ ትምህርት እና ክርስቶሳዊ በሆነ ትህትና ከማነጽ ይልቅ ስድብ ስትግታቸው ትውላለህ። አስበኸዋል አንድ ቀን ልጆችህ አድገው ምን ስታደርግ እንደነበር ቢረዱ ምን እንደሚሉህ? ባለቤትህስ? የሚያውቁህ ዘመዶችህስ? በዚህ ላይ ይህንን ስድብህን ለመትፋት “አገልግሎቴን በገንዘብ ደግፉ” እያልህ ሳንቲም ትለቃቅማለህ። ጊዜ ያልፋል፤ ኢንተርኔት የያዘው ግን አያልፍም። ለቤተሰብህ የውርደት ስንቅ በየቀኑ እየቋጠርህላቸው እንደሆነ እወቅ።

የወሊሶው ቡድን አስነዋሪውን ተግባር በፈጸመ ዕለት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተግባሩን ፍጹም ካወገዘ በኋላ ጉዳዩ በውይይት ይታይ፤ እንነጋገር ቢል ተሰምቶ የማያውቅ የስድብ ዶፍ አወረድህበት። ግን የደቡብ ካሊፎርኒያው አባታችን ብጹዕ አቡነ በርናባስ መድሎት ሚዲያ ላይ ባደረጉት ውይይት መፍትሔው ውይይት እና ንግግር እንደሆነ በግልጽ ተናግረዋል። አንተ በመንፈሳዊ ተግባር ስም ቤተክርስቲያናችንን ልታፈርስ የተነሳህ ቅጥረኛ ፖለቲከኛ ካልሆንህ በስተቀር ምን ቤት ሆነህ ነው ውይይት የለም የምትለው? ቀጠልህና አባታችን አቡነ ኤርምያስን ከፍ ዝቅ አድርገህ አጥረገረሃቸው። ወጥተው እንዲናገሩና ሚናቸውን እንዲለዩ የምትመራውን “መንፈሳዊ ቄሮ” መንጋ ላክህባቸውና አዋረድኻቸው። እርሳቸውም በነጋታው በዩትዩብ ቀርበው ቃላቸውን ሰጡ።

በዚህም አላበቃህ ቅዱስ ሲኖዶሱ ጉዳዩ መንፈሳዊ ነው እንጂ ምንም የፖለቲካ ዓላማ የለውም በማለት በተደጋጋሚ ቢናገርም አንተ ግን ፖለቲካዊ በማድረግ መንግሥትን በኃይል የመናድ ተግባር በገሃድ እንዲፈጸም እየጎተጎትህ ነው። አንተ ጀርመን ተቀምጠህ ነው ይህንን የምትለው፤ ለሚሞቱም “ሰማዕትነት ነው፤ ገነት ትገባላችሁ” እያልህ “ክርስቲያናዊ ጂሃድ” ታውጃለህ። ልክ ጃዋር ተመሳሳይ ተግባር ይፈጽም የነበረው ከሞቀ ኑሮው፤ ደህንነቱ ከተጠበቀበት ሚነሶታ እንደ ነበር ማለት ነው። አንተን ከጃዋር እንዴትና በምን ልለይህ?

አሁን ብዙ ተከታይና ደጋፊ አለህ። አንተ ከዕውቀት የራቅህ ስለሆነ ነው እንጂ ማኅበራዊ ሚዲያ ለትራምፕም አልበጀው። ባንዴ ሁሉንም ሲዘጉበት ያንን ሁሉ በሚሊዮን የሚቆጠር ተከታዩን በሰከንድ ውስጥ ነው ያጣው። ስለዚህ ትንሽ ቆም ብለህ አስብ! ቀን ያልፋል፤ ገናና መንግሥታትም አልፈዋል፤ ከፈለግን በጥቂት ደቂቃ መንግሥትን መቆጣጠር እንችላለን ያለው ጃዋርም የተነፈሰ ፊኛ ሆኖ ልክፍት እንደያዘው በየተራራው ይሽከረከራል።

ስለዚህ ወዳጄ ልምከርህ፤ የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም። ከወዳጅ ይልቅ ብዙ ጠላቶች ይከተሉሃል፤ ይፈልጉሃል፤ ምክንያቱም አጀንዳቸውን ታስፈጽምላቸዋለህ። ወዳጅ መስለው ያበረታቱሃል፤ “ወጥር ዘመዴ” ይሉሃል፤ ስታወራ ያዳምጡሃል፤ “እግዚአብሔር ይመስገን” በሉ ብለህ ስትጀምር ማኅበራዊ ሚዲያህን ያጧጡፍልሃል፤ ምክንያቱም ሥራቸውን በነጻ እየፈጸምህላቸው ስለሆነ። አጀንዳቸውን አስፈጽመህ ስታበቃ እንደ ሸንኮራ መጥጠው ይወረውሩሃል፤ እንደ ሲጋራ አጭሰው ይረጋግጡሃል። አትርሳ የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም።

ገና ለገና ሽምግልና ውስጥ ገብታለች ብለህ ከፍ ዝቅ አድርገህ የሰደብሃት ኮማንደር ደራርቱ በርግጥም በሒደቱ ውስጥ እንዳለች የሲኖዶሱ የሕዝብ ግንኙነት ሲሳውቅ አንተም “ደርዬን አገኘኋት” ብለህ ብቻ ነው የፖሰትኸው። ቢያንስ እሷንም፣ ተከታዮችህንም ስለፈጸምኸው ነውር ይቅርታ ልትጠይቅና ምሕረት ልትለምን ይገባሃል። ደራርቱን በስልክ ደውዬ አነጋገርኋት፤ እንደለመደቸው መልካም ነገሮችን ነገረችኝ ካልህ በኋላ አንድ ቃል ከሷ ንግግር ጠቀሰህ። እኔም በዚያች የደራርቱ ቃል ልሰናበትህ “አንተም ዘመዴ ተረጋጋ” ነበር ደራርቱ ያለችህ! አትርሳ የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም።

ባለማተቡ ነኝ (trinity123@aol.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: operation dismantle tplf, zemedkun bekele

Reader Interactions

Comments

  1. Ahoon says

    February 10, 2023 05:26 pm at 5:26 pm

    Ishohin be ishoh indemibalew ishoh hono yegebawun gareTa beishoh taweTawaleh inji 5 amet mulu bemeqlesles yameTanew negher alneberem. 2 million yetewahido lijoch inde qiTel siregfu lelaw sew min adereghe?

    Qidus qidus bemeChawet ye weyanne inna ye ohded jibim yihun yihuda altemelesem. Lela sint million yileq? Hagheris iske yet dires tiferars? Igna Chewa Chewa siniChawet arba amet hagherachin dirashua Teffa.
    Jiraf hono le hagerachin dersolatal. Igziabher YisTew.

    Le sidbu atcheneq. Hararghe bitihed, ye Zemede quanqua ijig ye Chewa yihoibihal. Siraw tesertola. Meswa’itnet tekeflobet.

    100 million chewa quanqua teTeqami hagherun asdefere inji alaskeberem.

    Zemede iskahun beseraw botaw kene Abdisa Agga, kene Zerai Deres, kene Belay Zeleke, kene Abune Petros gar new. Keziyam belay.. ye and teQuam yahil new yeseraw.

    Awo. LequrT qen yemiyasfelighew miTmiTTA inji alicha aydelem.

    Tebarek Zemede. Ante kifu mesleh lelochachin neTsanetin indinaTaTim adirghehal.

    Ye Qurt Qen Lij.

    Reply
    • Dedeboch says

      August 22, 2023 08:08 pm at 8:08 pm

      ለእነዚህ ተከፋይ ከርሣም ካድሬዎችና ድረ ገፃቸው ይህን ያህል ቦታ መሥጠት አያሥፈልግም። ሢጀመር ማን በድጋሚ ሢጎበኛቸው ነው? ጣዕም ላላቸው ገፆች እንኳን ጊዜው በበቃን። ለሆዳቸው ዓይናቸውን በልጥጠው ከዲያቢሎሡ የተወዳጁ ናቸና: ከእነዚህ ለዘለዓለሙ ያርቀን።

      Reply
  2. Dedebich says

    August 22, 2023 08:01 pm at 8:01 pm

    የምን ኮሜንት ይሆን የምትፈልጉት? መቼም ይህ ሚዲያ የሚሉት መድረክ ሁሉን እኩል በአንድ ቤንች ያሠልፋል። አቤት አቤት አቤት። ለመጀመሪያ ቀን አነበብኳችሁ። እሥከመጨረሻውም ተፀየፍኳችሁ። የነብሠ ገዳዩ የወንበር ጥመኛው ዐብይ ተከፋይይይይይ ድልብ ካድሬዎች። ሁለተኛ ? የእናንተን ገፅ ከማይይይይ: እንቅልፌን በሠላም በደሥታ ብኮመኩም ይጠቅመኛል። ዘመናዊ ከርሣሞች።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule