• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዐቢይን ግንባሩን ብለህ ዳዊት ሁን” ያሉት አቡነ ሉቃስ ክስ ተመሰረተባቸው

January 25, 2024 10:15 am by Editor 1 Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን እንደ ጎልያድ በማስመሰል በአንድ ምሳሌያዊ ዳዊት እንዲግደሉ የሃይማኖታዊ ግድያ ጥሪ ያስተላለፉት አቡን ሉቃስ የወንጀል ክስ ተመሠረተባቸው። አቡነ ሉቃስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 247 እና 251 ድንጋጌ ተላልፈዋል በሚል ክስ ተመሰረተባቸው፡፡

ክሱ የቀረበባቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ሕገመንግስታዊና በሕገመንግስት ስርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ነው። በአቡነ ሉቃስ ላይ ሁለት ክሶችን ያቀረበው የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ ነው፡፡

ይህም ተከሳሽ አቡነ ሉቃስ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 247 (ሐ) እና አንቀጽ 258(ሀ) ስር የተደነገገውን ድንጋጌ እንዲሁም የወንጀል ህግ አንቀጽ 251 (ሐ) እና አንቀጽ 258 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል የሚሉ ሁለት ክሶች ናቸው የተመሰረቱባቸው።

በተጨማሪም ተከሳሹ በፀረ ሰላም ሃይሎች የሚፈፀሙ የወንጀል ተግባሮችን ተከትሎ መንግስት ፈፃሚዎቻቸውን ለሕግ ለማቅረብ እና ሕግ ለማስከበር የሚያደርግባቸው ጥረቶችን ለማደናቀፍ እና ህዝብ መንግስት ላይ እምነት እንዲያጣ ማነሳሳታቸው በክሱ ተመላክቷል።

የክስ ዝርዝሩ የደረሰው ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ በጥር 27 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲቀርቡ ትዕዛዝ በመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። (ፋና)

አቡን ሉቃስ ይህንን የግድያ ጥሪ ካስተላለፉ በኋላ የኦርቶዶክስ ቤተክስቲያን ጳጳሱን እንድታወግዝ ከተለያዩ አካላት ጥያቄ ቢቅርብላትም ሳትፈጽመው ቀርታለች። ይህም በርካታ በሚባሉ ምዕምናኖቿ ዘንድ ቅሬታን የፈጠረ መሆኑ በስፋት ይነገራል።

በወቅቱ ካለው የፖለቲካ ትኩሳት አኳያ በአደባባይ ወጥተው ድምፃቸውን ባያሰሙም ጥቂት የማይባሉ የእምነቱ ተከታዮች “ጠቅላይ ሚኒስትሩን የምንቃወም ብንሆንም በዚህ ልክ ግን ግድያ እንዲፈጸምባቸው በተለይ ከሃይማኖት አባት መስማታችን አሳፍሮናል” በማለት በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ አስተያየታቸውን ሲሰጡ ተስተውለዋል።

“ጠላትህን ውደድ” የሚለውን የወንጌል ቃል ፍጹም በመጻረር በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ግድያ እንዲፈጸም ሃይማኖታዊ ጥሪ ያስተላለፉትን አቡን ሉቃስ ጉዳይ በተመለከተ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቡነ አብርሃም ከጥምቀት በዓል በፊት መልስ ሰጥተው ነበር። በአንድ በኩል ጉዳዩ በቅዱስ ሲኖዶስ መታየት ነው ያለበት ያሉ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ልናወግዝና መግለጫ ልንሰጥ አስበን ነበር ግን የሚያስከትለውን መጠላለፍ ተመልክተን ትተነዋል ማለታቸው ይታወሳል።

ይህንን የአቡነ አብርሃም ንግግር የሰሙ “እንደ ቅዱሱ ቃል የአቡነ ሉቃስን ንግግር ማውገዝ ተገቢ ነው፤ ግን ካወገዝን ደግሞ ከፋኖ እና ከደጋፊዎቻቸው ጋር ያጣላናል” በሚል የተረዱት እንዳሉ ብዙዎች ይስማማሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ   

በታሪክ አዱኛ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Social Tagged With: Abune Abraham, Abune Lukas, David and Goliath, EOTC, Kill Abiy

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    January 27, 2024 10:32 am at 10:32 am

    የእኛ ችግር ስለ ፍትህና የህዝቦች ሰላም በአደባባይ ከመሟገት ይልቅ ምላጭ መሳብና ማሳብ ይቀለናል። ለነገሩ ሁሉ በሚባል ደረጃ እምነቱ ሁሉ የማታለያና የመኖሪያ ብልሃት ምንጭ በመሆኑ እንዲህ አይነቱ ገድለህ ሙት የሚለው አስተሳሰብ እንደ ባህል ተወስዷል። ሲጀመር የጠ/ሚሩ መገደል በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ለውጥ አያስገኝም። ግን ያው በሃሳብም ሆነ በጦር ሜዳው የሚፋለሟቸው ሁሉ በሞታቸው ዳንኪራ ሊመቱ ይችላሉ። ያ ቢሆን ጊዜአዊ ጭፈራ ነው። ለገባው የጠ/ሚሩ ህልፈት የኢትዮጵያን ችግር አይፈታም። የምድሪቱ ችግር በሞትና በደም የሚፈታ ቢሆን ኑሮ እልፎች እረግፈዋል በመርገፍም ላይ ናቸው። ለውጥ ግን የለም። ከነብር የሸሽው እዘንዶ አፍ ገባ እንጂ!
    የሃገሪቷ ችግር የአፓርታይድ የቋንቋና የክልል ፓለቲካ ነው። ሰው በቋንቋው ያስብ የሚሉ እብዶች ያሉበት ሃገር ነው። ሰው በቋንቋው ሳይሆን የሚያስበው በጭንቅላቱ ነው። የአንድ ሃሳብ ጥንስስም በቋንቋ ብቻ ሳይሆን በልዪ ልዪ መንገድ ሊገለጥ ይችላል። ለምሳሌው ሰአሊዎች ምስልን ሲነድፉ በኦሮምኛ ወይም በአማርኛ እያሰቡ አይደለም። ወደ ጭንቅላታቸው የመጣውን ምናባዊ ነገር አለዚያም ከሚታየውና ከሚዳሰሰው ቆንጥረው ነው ስዕላቸውን ነፍስ የሚዘሩበት። ስለዚህ የቋንቋ አምልኮና የእኔ ብቻ እይታ ውሃ አይቋጥርም። ቋንቋ መግባቢያ እንጂ ሌላ ተግባር የለውምና!
    እነዚህ የዘመኑ የዘር ሰካራሞች ናቸው አሁን ምድሪቱን እያመሱ ያሉት። እድሜ ለሻቢያና ለወያኔ ኦነግን ጥሩ አርገው ከክፋት ጽዋቸው ስለ ጋቷቸው አሁን እውነት ፊታቸው ላይ ቆማ ተው ብትል ሰሚ ጀሮ የላቸውም። ስብዕና ያላቸውን ኦሮሞዎች እየገደሉና እያሰሩ ትግላችን ለህዝብ ነው ይሉናል። ተግባራቸው ሁሉ ሻቢያና ወያኔን ይሸታል። ሙት ይዞ ይሞታልና! የብሄር ፓለቲከኞች መከራ አዝናቢዎችን እንጂ ነጻነት አፍላቂዎች ሆነው አያውቁም። ታሪክን ማየት ነው።
    በእኔ እይታ የእምነት ሰዎች ስለ ፍትህ በአደባባይ ከማንባትና ከመከራከር አልፎ እከሌን ግደል ያን ያዝ የሚሉ ከሆነ እምነታቸው ብላሽ ነው። እይታቸው ከስሜት የጠራ፤ ብሄር ብሄረሰብ የሚባሉትን በእኩል አይን የሚያይ፤ ለሚበደሉ ሰዎች ያለ ምንም አድሎ ጥብቅና የሚቆም፤ የበደሉ ሰዎችን በመረጃ የሚሞግት መሆን ይገባዋል። ከዚህ በተረፈ በለውና በይውን መስቀል ሳይዙ ከባህር ማዶም ከሃገር ቤትም እሳቱ እንዳይበርድ ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርጉ ስላሉ የመንፈሳዊ አባቶች ሚና ከላይ እንደጠቀስኩት ቢሆን ለሃገርም፤ ለምዕመናንም ለቤ/ክርስቲያንም መልካም ይመስለኛልና። መገዳደሉን ለሚፈላለጉት ቢተውት ይሻላል ባይ ነኝ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule