• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በደብረ ኤሊያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም የታጠቀ ፅንፈኛ ኃይል መሽጎ ነበር” ጄኔራል አዘዘው መኮንን

June 12, 2023 10:51 am by Editor 2 Comments

በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ በጸረ ሰላም ኃይሎች ላይ በተወሰደ እርምጃ የተገኘውን ሰላም ለማስቀጠል እየተሠራ መሆኑን የመከላከያ ሠራዊት አስታወቀ።

መንግሥት በወሰደው የሕግ ማስከበር እርምጃ በአሁኑ ወቅት የአካባቢው ሰላም ተመልሶ የግብርና ሥራቸውን እያከናወኑ መሆናቸውን የአካባቢው አርሶ አደሮች መግለጻቸው ይታወሳል።

በመከላከያ ሠራዊት የምዕራብ ዕዝ 403ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዘዘው መኮንን ለኢዜአ እንደገለጹት በደብረ ኤሊያስ ወረዳ በስላሴ ገዳም አካባቢ የታጠቀ ፅንፈኛ ኃይል መሽጎ ነበር። 

በገዳሙ የመሸገው ኃይል ችግር ለመፍጠር በማለም ተጨማሪ ኃይል በማሰልጠንና በማደራጀት ሲሰራ መቆየቱን በተገኘው መረጃ ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል።

የአካባቢውን ህዝብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት አንቅስቃሴዎችን ከማስተጓጎሉም በላይ የጸረ ሰላም ኃይሉን አስተሳሰብ የማይቀበል ግለሰቦችን ሲገድሉ እንደነበረም አስታውሰዋል።

መከላከያ ሠራዊት ህግ ለማስከበር ወደ አካባቢው ሲገባም ቀድሞ ባዘጋጀው ምሽግ ውስጥ በመደበቅና ተኩስ በመክፈት ስርአት አልበኝነቱን አሳይቷል ብለዋል።

የመከላከያ ሠራዊት በወሰደው የህግ ማስከበር እርምጃ ጸረ ሰላም ሀይሉ የተመታ ሲሆን ተንጠባጥቦ በመሸሽ ላይ ያለውን የመከታተል ስራ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከአካባቢው መስተዳድርና ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበርም የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግም ከጽንፈኛ ኃይሉ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ለማዋል እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ሰላምና ደህንነት መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ላቃቸው አብጠው የተገኘውን ሰላም ለማጽናት በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።

በአካባቢው የጸረ ሰላም ሃይሎች እንቅስቃሴ መስተዋል ከጀመረ የቆየ ቢሆንም ችግሩ እየተባባሰና ስርአት አልበኝነቱ እየተስፋፋ የመጣው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በአመለካከት የማይደግፏቸውን ንፁሃን ዜጎች፣ አመራሮችና የሃይማኖት አባቶችን ሲገድሉ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

በቀጣይ ገዳሙ ትክክለኛ የሀይማኖት ስፍራ እንዲሆን ከጠቅላይ ቤተክህነትና ከዞኑ ሀገረ ስብከት ጋር እየተሠራ ነው ብለዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያው ምስሎችን በመቆራረጥና በማገናኘት ገዳሙ እንደወደመ ተደርጎ የሚነዛው ወሬ የፈጠራ ፕሮፓጋንዳ መሆኑን ሁሉም ህዝብ ሊያውቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

አሁን የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድርግም ሕዝቡ ሀይማኖትን ሽፋን በማድርግ የፖለቲካ ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ ሃይሎችን ማጋለጥና መታገል አለበት ሲሉም አሳስበዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: debre elias monastery church, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    June 14, 2023 07:58 pm at 7:58 pm

    ሲጀመር ከመቼ ወዲህ ነው የታጠቀ ሃይል በገዳማትና በቤተክርስቲያናቶች መካከል የሚመሽገው። መሻጊውም ሆነ አሳዳጅ ሃይል ሁለቱም ወስላቶች ናቸው። እንዲህ አይነቱ ገዳዳ እይታ ነው እምነታችን ባዶ የሚያደርገው። ጠበንጃ አንስተህ ውጊያ መግጠም ካማረህ መጠለያህ የእምነት ቤቶች ሊሆኑ አይገባም። መንግስት ተብዬውም በዚህም በዚያም ሰውን ማንገላታትና መግደሉም ሰላምን አያመጣም። ባጭሩ የሃበሻዋ ሃገር እሳት የማይጠፋባት፤ እፎይ አልን ሲባል ሌላ የሚቀጣጠልባት በዘር ፓለቲካ ጭንቅላታቸው የነጠበ የሚተራመሱባት ምድር ሆናለች። የሃገራችን ጉዳይ ልብ ላለው ከቀን ወደ ቀን አሳዛኝ እየሆነ መጥቷል። ዛሬ ጊዜ ሰጥቷቸው የሚፍነሸነሹት የዘርና የቋንቋ ጥርቅሞች የሌላው ሰው ሞትና መፈናቀል ደንታ የማይሰጣቸው ጭፍን አላሚዎችና ደንቆሮዎች ናቸው። ሰው በስብዕናው መለካቱ ቀርቷል። ጠበንጃ አንጋቾችና ለእነርሱ ያደሩ ህዝቡን ያተራምሱታል። በቅርቡ በአዋሳ ከተማ አፈቀራት በተባለው ታጣቂ ታፍና ለ 10 ቀናት ሃበሳዋን አይታ የተለቀቀችው ጸጋ ለምድሪቱ የሻገተ አስተሳሰብ ማሳያ ናት። ሰው እንዴት በዚህ ዘመን ሴትን ይጠልፋል? ግን በሴቶች ላይ የሚፈጸመውን ግፍ ማስቆም የሚቻለው የሴቶች ህብረትና አንድነት ሲኖር ነው። ይህና ፓለቲካው ምን አገናኘው የሚል የወሬ ጨላጭ ሊኖር ይችላል። በደንብ ነው የሚገናኘው። ፍትህ ባጣ ምድር ላይ አለቃውም አዛዡም ታጣቂ ሃይል ነውና!
    ጄ/አዘዘው መኮነን “ታጣቂ ሃይል መሽጎ ነበር” ይለናል። መቀሌ ላይ የመሸገውንና አሁንም በሰው ህይወት የሚቀልደውን ወያኔን ለምን ሂዳችሁ አትገጥሙትም። ወያኔ የአሜሪካ ጥብቅና ስላለው ፍርሃት ይሆን? ወይስ ከኦሮሞ ጋር ዞሮ ስለተጣመረ? ወታደራዊ ስልት ለገባው ወታደር መሆን ሁሌ ተኳሽ ብቻ እንዳልሆነ መገንዘብ ቀላል ነው። ኢላማን ሳይለዪ እየተኮሱ ሰውን መግደል ለሰማይ አድረናል በማለት በዚያው የተቀመጡትና ታጣቂ ሃይል የሚባለውን መለየት ያልቻለ የጅምላ ፍርድ ነው። ባጭሩ ህይወት በሃበሻዋ ምድር በነሲብ የሚኖርባትና የሚሞትባት ሆናለች። ለአማራ ቤት አታከራዪ የሚሉ ኦሮሞዎች እንደ አሸን በፈሉበት ምድር ላይ ሰው ነኝ ብሎ መቆም ከሰው አውሬ ጋር ያጋጫል። ህጻናትና እናቶች እያለቀሱ እየዘፈነ ቤት የሚያፈርስና የቆመውን እንጨትና ቆርቆሮ ዘርፎ በሚወሰድበት ከተማ ተቀምጦ ለወያኔ ግማሽ ቢሊዪን ብር ለእርዳታ ተሸክሞ መቀሌ ድረስ መሄድ የፓለቲካው ትልቅ ውስልትና ነው። ግን የሃበሻ ፓለቲካ በየተራ የመገዳደልና የማፈራረስ ፓለቲካ ነው። ላስረዳ።
    በመጀመሪያው የጣሊያን ወረራ ከየክፍለ ሃገሩ ተሰባስበው በሰሜን ኢትዮጵያ በመገኘት ጣሊያንን ማሳፈራቸው የማይካድ ሃቅ ነው። ግን ከድል በህዋላ የሞቱላት ሳይሆን ለጠላት ያደሩት ነበር ከፍታ ላይ የወጡት። ያ አልፎ ዳግመኛ ጣሊያን ወረራ ሲያደርግ ከመጀመሪያው ጦርነት የተረፉትና በእድሜ የገፉት ጭምር ነበር ዳግም ወደ ሰሜን በመሄድ የተሰውት። ደርግ ሊፈራርስ ሲል ጡረታ የወጡ ወታደሮችን በመጥራት ለወያኔና ለሻቢያ የጥይት ራት አድርጓቸዋል። ወያኔ በባድሜ ሰበብ ከሻቢያ ጋር ሲፋታ ከሁለቱም ወገን ያለቁት ከልዪ ልዪ ጦርነቶች የተረፉት ጭምር ነበር። ይህ የሚያሳየው እረፍ ያላለው የከብት ቆዳ ከበሮ ይሆናል እንዲሉ ነው። ሁሌ መደለቅ። እልፈት የለሽ መገዳደልና መጎሻሸም።
    አሁን እንሆ አሜሪካኖች ኢትዮጵያን ከኤርትራ ጋር ለማላተም ያለ የሌለ ሴራቸውን ተያይዘውታል። ኤርትራን ራሺያና ቻይና ሊያስታጥቋት ይችላሉ፤ ወያኔ ያው ሶስት ጊዜ ወረራ እንዲያደርግ የገፋፉት አሜሪካኖች እሳት ያቀብሉታል። ሱዳን ላይ እሳቱ ተቀጣጥሏል። ስለሆነም አሳራችን በውጭ ሃይሎችና በዘርና በቋንቋ በሰከሩ የብሄር ድርቡሾች እየታገዘ ይቀጥላል። የዛሬው ገዳይ የነገ ሟች፤ የዛሬው አፈናቃይና ዘራፊ የነገ ነፍሱን ሊያተርፍ ሯጭ፤ የዛሬው ጄኔራልና ወገንተኛ ነገ ቆሞ ለማኝ እንደሚሆን የሃገሪቱ ታሪክ በተደጋጋሚ አሳይቶናል። ለዚህም ነው የጨነቀው እርጉዝ ያገባል የሚሉት አበው። አሁን ማን ይሙት ብልጽግና ከወያኔ ይሻላል? ፍርድን ላንባቢ። ገና ግን ብዙ ጉድ እናያለን። እንሰንብት። በቃኝ!

    Reply
  2. Selma Atnafu says

    June 24, 2023 03:15 am at 3:15 am

    ለምን ትዋሻላችሁ፦ ሀገር ያወቀዉን ፀሐይ የሞቀውን እውነት መደበቅ የትም እያደርሰም።

    ረቡዕ ሰኔ 14 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥር ባሉ አራት ገዳማት ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት፤ በገዳማቱ አንድ መነኩሴ ብቻ መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስታውቃለች፡፡

    በገዳማቱ ከግንቦት 18 እስከ 23/2015 ለተከታታይ አምስት ቀናት “የታጠቁ ኃይሎች በገዳሙ ውስጥ ይገኛሉ” በሚል በተደረገ ኦፕሬሽን እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ መነኮሳት መሞታቸውን፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓበርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት አሥተዳደር መምሪያ ኃላፊ መጋቤ ካህናት አባ ሀብተጊዎርጊስ አሥራት ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡

    ኃለፊው አክለውም፤ በአራቱም ገዳማት አቢያተ ክርስቲያናት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ለአዲስ ተናግረዋል፡፡ በዚህም በገዳሙ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች “ሕግ ማስከበር” ያሉትን ዘመቻ ከማካሄዳቸው በፊት በርካታ መነኮሳት እና አገልጋዮች ይኖሩ እንደነበር ገልጸው፣ የገዳማት አስተዳደር መምሪያው ወደ ሥፍራው ባቀናበት ወቅት የተገኙት አንድ መነኩሴ ብቻ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

    “መሞታቸው ከታወቀው መነኮሳቱና አገልጋዮች ውጭ ሌሎቹ የት እንደገቡ አይታወቅም፡፡” ያሉት ኃላፊው፤ በገዳሙ ውስጥ ባለው ሰፊ የአትክልት እርሻ በርካታ ያልተቀበሩ አስከሬኖች መኖራቸውንና በአካባቢው ከፍተኛ የአስከሬን ሽታ መኖሩንም ተናግረዋል፡፡

    የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች “በገዳሙ የታጠቁ ኃይሎች መሽገዋል” በሚል ኦፕሬሽን ቢያደርጉም፤ በተለያዩ ጊዜያት ሽፍታዎች የገዳሙን ንብረት ለመዝረፍ ወደ ሥፍራው ይመጡ ስለነበር፣ መነኮሳቱ ምሽግ ቆፍረው ንብረቱን ከዝርፊያ ለማዳን እና ሕይወታቸውንም ለመታደግ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

    በተደረገው ዘመቻ ጉዳት የደረሰባቸው አቢያተ ክርስቲያናት የሥላሴ፣ ኪዳነምሕረት፣ የኤልያስ እና የጊዎርጊስ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ አቢያተ ክርስቲያናቱ የውጭ ክፍላቸው ጨምሮ ቅኔ ማሕሌቱ፣ ቅድስቱ እና ቤተመቅደሱ ላይ የደረሰው ድብደባ እጅግ ከፍተኛ መሆኑንም አስረድተዋል።

    “በተለይ በኪዳነምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ላይ የደረሰው ጉዳት ከኹሉም የከፋ ነው፡፡” ያሉት ኃላፊው፣ ንዋተ ቅድሳትን ጨምሮ የቤተ መቅደስ መገልገያዎች መውደማቸውን እና ጉልላቱም ተመትቶ መውደቁን ገልጸዋል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule