
አቶ ዮሐንስ ቧያለው በክልላቸው ምክር ቤት ፊት ስለ ማዳበሪያ አቅርቦት ዕጥረት አምርረው በተናገሩና የክልሉ ገብርና ቢሮ ሥራ መሥራት ያልቻለ ደመወዝ በነጻ የሚበላ ነው ብለው ባፌዙበት ማግስት በአማራ ክልል 400 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ በሕገወጥ መልኩ ሲሰራጭ መያዙን ኢቢሲ ዘግቧል። በአማራ ክልል ማዳበሪያን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ ሲወራ የሰነበተው ሤራ ምን እንደሆነ ማሳያ ነው። የዜናው ሙሉ መረጃ ከዚህ በታች ቀርቧል።
400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር በቁጥጥር ሥር ዋለ
መነሻውን ከጅቡቲ ወደብ አድርጎ መዳረሻውን ወረታ ከተማ ለማድረግ የተንቀሳቀሰው 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ የጫነ ተሳቢ ተሽከርካሪ፤ ከታሰበው ቦታ ሳይደርስ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡
ሕገ ወጥ ድርጊቱ የተፈጸመው በባህርዳር ከተማ ሰባታሚት ቀበሌ ሐምሌ 16/2015 ሲሆን፤ አሽከርካሪው በአሳቻ ሰዓት በመጠበቅ ከሌሊቱ 6:00 ላይ የአፈር ማዳበሪያውን በሕገ ወጥ መንገድ ለግለሰቦች ሲያከፋፍል በኅብረተሰቡ ጥቆማ መያዙን የሰባታሚት ቀበሌ ፖሊስ ኦፊሰር ኮንስታብል ዮሐንስ ጥላሁን ተናግረዋል።

አብዛኛው ማዳበሪያ ሳይራገፍ ከነተሽከርካሪው ቢያዝም፤ ከ140 ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለግለሰቦች በሕገ ወጥ መንገድ መሰራጨቱ የተገለጸ ሲሆን፤ ፖሊስ ባደረገው ቤተ ለቤት ፍተሻ ከተሽከርካሪው ተራግፎ በግለሰቦች ቤት የተከዘነ በርካታ የአፈር ማዳበሪያ መገኘቱም ተነግሯል፡፡
በዚህም 89 ኩንታል ማዳበሪያ በአንድ ግለሰብ ቤት የተገኘ ሲሆን፤ 24 ኩንታል ማዳበሪያ ደግሞ በአንድ ግለሰብ ቤት በአልጋ ሥር እና በኩሽና ውስጥ መገኘቱ ተገልጿል።
አሽከርካሪው ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ኮንስታብል ዮሐንስ ገልጸው፤ ኅብረተሰቡ እንደዚህ አይነት ሕገ ወጥ ተግባርን እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
Leave a Reply