• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጩኸት ያፈናት ከተማ

July 1, 2021 12:13 pm by Editor 1 Comment

የድምጽ ብክለት መጨመር የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ለምሬት እየዳረገ ይገኛል፡፡ ከመጠን ያለፉት ረባሽ ድምጾች፡- ከንግድ ትርኢቶች፣ ከሐይማኖት ተቋማት፣ ከምጽዋት ጠያቂዎች፣ ከጎዳና ላይ ንግድ፣ ከምግብና መጠጥ ቤቶች፣ ጋራዥ፣ እንጨት ቤት እና ብረት ቤትን ከመሰሉ አገልግሎት ሰጪዎች፣ ከፊልምና ሙዚቃ መሸጫዎች፣ ከተሽከርካሪዎች እና ከመሳሰሉት ይመነጫሉ፡፡

ለመሆኑ የድምጽ ብክለት ማለት ምን ማለት ነው? ምን ጉዳት ያስከትላል? እንዴት መቆጣጠር ይቻላል? የሚለውን ጥያቄ አንስተናል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የባለሙያዎች አስተያየት እና የተጎጂዎች ሐሳብ ተካቷል፡፡

“የድምፅ ብክለት መደበኛውን የሕይወታችንን እንቅስቃሴ ይጎዳል፣ ያስተጓጉላል፣ እንቅልፍ ይነሳል፤ ውይይቶቻችንንና መደማመጣችንን ይቀንሣል፣ በአጠቃላይ የአኗኗራችን ሁኔታ የተረበሸ እንዲሆን ያደርጋል።” የሚሉት የቀድሞ የኢትዮጵያ ህክምና ማኅበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገመቺስ ማሞ ናቸው፡፡

ዶ/ር ገመቺስ ሐሳባቸውን ሲቀጥሉ “የድምፅ ብክለት በጤና ላይ በቀጥታ ከሚያደርሰው ጉዳት በተጨማሪ የምርታማነት መቀነስ፣ የትራፊክ አደጋ መበራከት፣ የማኅበራዊ ሕይወት መደፍረስ፣ የቤተሰብ መመሳቀል፣ የልጆች አዕምሮ መድከም፣ በውጤቱም የትውልድ ጉዳት ይከተላል።” በማለት ከዘረዘሩ በኋላ ይህ መረበሽና መስተጓጎል ከሚያደርሳቸው የበረቱ የጤና ችግሮች መካከል ከጭንቀት፣ የደም ግፊት፣ የአንደበት መተሳሰር (መንተባተብ)፣ የመስማት ችሎታን መቀነስ ግፋ ሲልም ማጣት፣ የልብና የደም ዝውውር ሥርአት መስተጓጎል፣” እንደሚገኙበት ዘርዝረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የአካባቢ ደህንነት መብትን በሰብአዊ መብት ደረጃ በሕገ መግሥታቸው ከደነነጉ ጥቂት ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት፡፡ የድምጽ ቁጥጥር ሕጉ ከንግድ አካባቢዎችና ከኢንዱስትሪ ዞኖች መውጣት የሚገባው የድምጽ መጠን በድምጽ መለኪያ አስቀጧል፡፡ በዚህም መሰረት ሰዎች በሚንቀሳቀሱበት የቀኑ ክፍለ ጊዜ በከባቢ አየሩ የሚረጨው ድምጽ 55፣ 65 እና 75 ዲሲቢል መብለጥ እንደማይገባው፤ ለሌሊት ደግሞ 45፣ 57 እና 70 ዲሲቢል መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡

በመሆኑም አንድ ግለሰብ የድምጽ ብክለት ገደቡን ተላልፎ ጥፋተኛ ሆኖ ሲገኝ በገንዘብ ከብር ከ1,000 እስከ 5,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም በእስራት ከ1 ዓመት ባላነሰ ከ10 ዓመት ባልበለጠ እስራት እንደሚቀጣ በአዋጁ ተደንግጓል፡፡ ጥፋተኛው የሕግ ሰውነት የተሰጠው (ተቋም) ከሆነ ደግሞ ከብር 5,000 እስከ 25,000 በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይጣልበታል፡፡ የድርጅቱ ኃላፊም ከ5 እስከ 10 ዓመት እስራት ወይም ከብር 5,000 እስከ 10,000 በሚደርስ እስራት ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ደንግጓል፡፡

ሕጉ ይህንን ቢልም ተፈጻሚነቱ ላይ ግን ችግሮች ያሉ ይመስላል፡፡ አንዳንድ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ላይ ቅኝት ያደረገችው አዲስ ዘይቤ የድምጽ ብክለት ችግርን ለመቅረፍ የወጡ ሕግጋትን ከማስፈጸም አኳያ ሰፊ ጉድለት እንዳለ ተመልክታለች፡፡

ሐሳባቸውን የሰጡን የከተማዋ ነዋሪዎች የድምጽ ብክለቱ ከእለት ወደ እለት እየተባባሰ ስለመሆኑ ይናገራሉ፡፡ “ከየአቅጣጫው የሚለቀቀው ረባሽ ድምጽ ተረጋግተን ሥራችንን እንዳንሰራ፣ ቤት ገብተንም በቂ እረፍት እንዳናገኝ፣ ልጆቻችን የተረጋጋ እረፍትና ጥናት እንዳይኖራቸው፣ አድርጓቸዋል” ሲሉ ያማርራሉ፡፡

እነዚህንና መሰል አቤቱታዎችን በመከተል የድምፅ ብክለት ችግርን ለመቅረፍ የወጡ ሕጎችን ማስፈጸም ስላልተቻለበት ምክንያት የጠየቅናቸው የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ወይሳ ፈይሳ

“አካባቢን በድምጽ የሚበክሉ ድርጅቶች እና አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ላይ የክትትል እና ቁጥጥር ተግባራት ተከናውነዋል፡፡እርምጃ የተወሰደባቸውም አሉ፡፡ የሕግ አስከባሪዎች የድምፅ መጠን የሚለኩ መሳሪያዎችን ይዘው እንደሚቀሳቀሱና ሕጉን ተላልፈው የተገኙ አካላት ላይ እርምጃ ሲወስድ መቆየቱንም ይገልጻሉ፡፡ ሆኖም በቁጥጥር ሥራ ላይ የተሰማሩ አንዳንድ ባለሙያዎች ለሙስና የተጋለጡ በመሆናቸው ምክንያት የሚፈለገው ውጤት አለመምጣቱን አልሸሸጉም፡፡    

ከሃይማኖት ተቋማት የሚለቀቁ ድምጾችን በተመለከተ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን ዳሰሳ ጥናት በማካሄድ ላይ እንደሆነ ኮሚሽነሩ አስታውሰው ችግሩ ያለበትን ደረጃ የመረዳት እና በቀጣይም ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጋር በመነጋገር እና የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የማስተካከል እርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል፡፡

የአካባቢ ጥበቃ እና ደህንነት ባለሙያና የጥናቱ ተሳታፊ የሆኑትን አቶ ጉሌድ አብዲም “የጥናቱ ዓላማ የእምነት ተቋማት የሚገኙበትን አካባቢ የሚያማክል መጠነኛ ድምፅ ገዳቢ መመሪያዎችን መከለስ፣ ኅብረተሱቡንም ሆነ ባለድርሻ አካላትን ያማከለ ምክክር ማድረግ እና በሚቻለው መጠን ነዋሪው ጤናማ መስተጋብር እንዲኖረው የሚረዳ ነው” ሲሉ አብራርተዋል።

Nigist Berta አዲስ ዘይቤ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions, Social Tagged With: addis ababa, addis ababa is a city state, noise

Reader Interactions

Comments

  1. Ereso Negi says

    July 1, 2021 12:17 pm at 12:17 pm

    ሕግ ይውጣለት። ተግባራዊም ይጀረግ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule