• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጩኸት ያፈናት ከተማ

July 1, 2021 12:13 pm by Editor 1 Comment

የድምጽ ብክለት መጨመር የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ለምሬት እየዳረገ ይገኛል፡፡ ከመጠን ያለፉት ረባሽ ድምጾች፡- ከንግድ ትርኢቶች፣ ከሐይማኖት ተቋማት፣ ከምጽዋት ጠያቂዎች፣ ከጎዳና ላይ ንግድ፣ ከምግብና መጠጥ ቤቶች፣ ጋራዥ፣ እንጨት ቤት እና ብረት ቤትን ከመሰሉ አገልግሎት ሰጪዎች፣ ከፊልምና ሙዚቃ መሸጫዎች፣ ከተሽከርካሪዎች እና ከመሳሰሉት ይመነጫሉ፡፡

ለመሆኑ የድምጽ ብክለት ማለት ምን ማለት ነው? ምን ጉዳት ያስከትላል? እንዴት መቆጣጠር ይቻላል? የሚለውን ጥያቄ አንስተናል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የባለሙያዎች አስተያየት እና የተጎጂዎች ሐሳብ ተካቷል፡፡

“የድምፅ ብክለት መደበኛውን የሕይወታችንን እንቅስቃሴ ይጎዳል፣ ያስተጓጉላል፣ እንቅልፍ ይነሳል፤ ውይይቶቻችንንና መደማመጣችንን ይቀንሣል፣ በአጠቃላይ የአኗኗራችን ሁኔታ የተረበሸ እንዲሆን ያደርጋል።” የሚሉት የቀድሞ የኢትዮጵያ ህክምና ማኅበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገመቺስ ማሞ ናቸው፡፡

ዶ/ር ገመቺስ ሐሳባቸውን ሲቀጥሉ “የድምፅ ብክለት በጤና ላይ በቀጥታ ከሚያደርሰው ጉዳት በተጨማሪ የምርታማነት መቀነስ፣ የትራፊክ አደጋ መበራከት፣ የማኅበራዊ ሕይወት መደፍረስ፣ የቤተሰብ መመሳቀል፣ የልጆች አዕምሮ መድከም፣ በውጤቱም የትውልድ ጉዳት ይከተላል።” በማለት ከዘረዘሩ በኋላ ይህ መረበሽና መስተጓጎል ከሚያደርሳቸው የበረቱ የጤና ችግሮች መካከል ከጭንቀት፣ የደም ግፊት፣ የአንደበት መተሳሰር (መንተባተብ)፣ የመስማት ችሎታን መቀነስ ግፋ ሲልም ማጣት፣ የልብና የደም ዝውውር ሥርአት መስተጓጎል፣” እንደሚገኙበት ዘርዝረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የአካባቢ ደህንነት መብትን በሰብአዊ መብት ደረጃ በሕገ መግሥታቸው ከደነነጉ ጥቂት ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት፡፡ የድምጽ ቁጥጥር ሕጉ ከንግድ አካባቢዎችና ከኢንዱስትሪ ዞኖች መውጣት የሚገባው የድምጽ መጠን በድምጽ መለኪያ አስቀጧል፡፡ በዚህም መሰረት ሰዎች በሚንቀሳቀሱበት የቀኑ ክፍለ ጊዜ በከባቢ አየሩ የሚረጨው ድምጽ 55፣ 65 እና 75 ዲሲቢል መብለጥ እንደማይገባው፤ ለሌሊት ደግሞ 45፣ 57 እና 70 ዲሲቢል መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡

በመሆኑም አንድ ግለሰብ የድምጽ ብክለት ገደቡን ተላልፎ ጥፋተኛ ሆኖ ሲገኝ በገንዘብ ከብር ከ1,000 እስከ 5,000 በሚደርስ መቀጮ ወይም በእስራት ከ1 ዓመት ባላነሰ ከ10 ዓመት ባልበለጠ እስራት እንደሚቀጣ በአዋጁ ተደንግጓል፡፡ ጥፋተኛው የሕግ ሰውነት የተሰጠው (ተቋም) ከሆነ ደግሞ ከብር 5,000 እስከ 25,000 በሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይጣልበታል፡፡ የድርጅቱ ኃላፊም ከ5 እስከ 10 ዓመት እስራት ወይም ከብር 5,000 እስከ 10,000 በሚደርስ እስራት ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ደንግጓል፡፡

ሕጉ ይህንን ቢልም ተፈጻሚነቱ ላይ ግን ችግሮች ያሉ ይመስላል፡፡ አንዳንድ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ላይ ቅኝት ያደረገችው አዲስ ዘይቤ የድምጽ ብክለት ችግርን ለመቅረፍ የወጡ ሕግጋትን ከማስፈጸም አኳያ ሰፊ ጉድለት እንዳለ ተመልክታለች፡፡

ሐሳባቸውን የሰጡን የከተማዋ ነዋሪዎች የድምጽ ብክለቱ ከእለት ወደ እለት እየተባባሰ ስለመሆኑ ይናገራሉ፡፡ “ከየአቅጣጫው የሚለቀቀው ረባሽ ድምጽ ተረጋግተን ሥራችንን እንዳንሰራ፣ ቤት ገብተንም በቂ እረፍት እንዳናገኝ፣ ልጆቻችን የተረጋጋ እረፍትና ጥናት እንዳይኖራቸው፣ አድርጓቸዋል” ሲሉ ያማርራሉ፡፡

እነዚህንና መሰል አቤቱታዎችን በመከተል የድምፅ ብክለት ችግርን ለመቅረፍ የወጡ ሕጎችን ማስፈጸም ስላልተቻለበት ምክንያት የጠየቅናቸው የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ወይሳ ፈይሳ

“አካባቢን በድምጽ የሚበክሉ ድርጅቶች እና አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ላይ የክትትል እና ቁጥጥር ተግባራት ተከናውነዋል፡፡እርምጃ የተወሰደባቸውም አሉ፡፡ የሕግ አስከባሪዎች የድምፅ መጠን የሚለኩ መሳሪያዎችን ይዘው እንደሚቀሳቀሱና ሕጉን ተላልፈው የተገኙ አካላት ላይ እርምጃ ሲወስድ መቆየቱንም ይገልጻሉ፡፡ ሆኖም በቁጥጥር ሥራ ላይ የተሰማሩ አንዳንድ ባለሙያዎች ለሙስና የተጋለጡ በመሆናቸው ምክንያት የሚፈለገው ውጤት አለመምጣቱን አልሸሸጉም፡፡    

ከሃይማኖት ተቋማት የሚለቀቁ ድምጾችን በተመለከተ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን ዳሰሳ ጥናት በማካሄድ ላይ እንደሆነ ኮሚሽነሩ አስታውሰው ችግሩ ያለበትን ደረጃ የመረዳት እና በቀጣይም ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጋር በመነጋገር እና የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የማስተካከል እርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል፡፡

የአካባቢ ጥበቃ እና ደህንነት ባለሙያና የጥናቱ ተሳታፊ የሆኑትን አቶ ጉሌድ አብዲም “የጥናቱ ዓላማ የእምነት ተቋማት የሚገኙበትን አካባቢ የሚያማክል መጠነኛ ድምፅ ገዳቢ መመሪያዎችን መከለስ፣ ኅብረተሱቡንም ሆነ ባለድርሻ አካላትን ያማከለ ምክክር ማድረግ እና በሚቻለው መጠን ነዋሪው ጤናማ መስተጋብር እንዲኖረው የሚረዳ ነው” ሲሉ አብራርተዋል።

Nigist Berta አዲስ ዘይቤ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions, Social Tagged With: addis ababa, addis ababa is a city state, noise

Reader Interactions

Comments

  1. Ereso Negi says

    July 1, 2021 12:17 pm at 12:17 pm

    ሕግ ይውጣለት። ተግባራዊም ይጀረግ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule