• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሱዳን ለትህነግ ሊሰጥ የነበረ 260 ገጀራ እና 1 ሺህ 149 ሕገ ወጥ መታወቂያ ተያዘ

September 24, 2021 11:01 am by Editor Leave a Comment

ከሱዳን ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ ለነበረው የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን የተዘጋጀ ገጀራ እና የሐሰት መታወቂያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሽንፋ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ከሱዳን በቲሀ በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ ለነበረው እና በጀግናው የፀጥታ ኀይል ለተደመሰሰው የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን ሊሰጥ የነበረ 260 ገጀራ እና 1 ሺህ 149 ሕገ ወጥ መታወቂያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የሽንፋ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ጉባይ ቀበሌ በቀድሞው የሰሜን ጎንደር ዞን ጉባይ ጀጀቢት ቀበሌ በሚል ስያሜ ተዘጋጅቶ ከሱዳን ሊገቡ ለነበሩ የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን አባላት ሊሰጥ የነበረ 1 ሺህ 149 ሕገ ወጥ መታወቂያ የቅማንት ጽንፈኛ ቡድን መሪ በሆነው አቶ ሻንቆ አየልኝ ቤት መገኘቱን የሽንፋ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ተወካይ መርማሪ ፖሊስ ምክትል ሳጅን ወርቅዬ ዋለልኝ አሰታውቀዋል።

መታወቂያው ለሳምሪና በቲሃ በኩል ሊገባ ለነበረው የሽብር ቡድን በመስጠት የአማራ ተወላጅ መስለው በአካባቢው የሽብር ተልኮን ለመፈጸም ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን መርማሪ ፖሊሱ ጠቅሰዋል።

የአካባቢው ማኅበረሰብ ባደረገው አሰሳና ፍተሻ በጽንፈኛው ቅማንት ቡድን አባል አቶ መከተ ብርቄ የንግድ መካዝን ስሪቱ የእንግሊዝ የሆነ 260 ገጀራ መገኘቱንም የሽንፋ ከተማ ቀበሌ አስተዳደሪ አቶ በለጠ ዳምጤ ተናግረዋል።

በቅማንት ጽንፈኛ ቡድን መሪነት ከሱዳን በቲሀ በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ሊገባ የነበረው የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን ሽንፋን ለመቆጣጠር ጦርነት ቢከፍትም በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ በልዩ ኃይል፣ ሚሊሻ፣ ፋኖና በአካባቢው ማኅበረሰብ መደምሰሱን መዘገባችን ይታወሳል።

ሽንፋን ዳግማዊ ማይካድራ ለማድረግ የሞከረው የሽብርተኛው ትህነግ ወራሪ ቡድን ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመቀናጀት ዳግም ላይመለስ ቀብረነዋል ያሉት በመተማ ወረዳ የሽንፋ ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ተሾመ በሪሁን ናቸው፡፡ ሽንፋ በሽብር ቡድኑና በተላላኪዎች ላትደፈር ወጣቱን ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በማቀናጀት አካባቢያቸውን እየጠበቁ መሆናቸውን ገልጸዋል። (አሚኮ: ቴዎድሮስ ደሴ – ከሽንፋ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, qimant terrorist, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule