አቶ ጀዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ በፌዴራል የጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ኦሮሚያ ሚድያ ኔትወርክ ዘገበ። ኦሮሚያ ሚድያ ኔትወርክ ከደቂቃዎች በፊት በሰራው ዘገባ እንዳለው ጀዋርን በቁጥጥር ሥር ለማዋል በተደረገው ጥረት የኦሮሚያ ክልል የጸጥታ ኃይሎች ከፌዴራል የጸጥታ ኃይሎች ጋር ግጭት ውስጥ ገብተው ነበር። በሁለቱ ኃይሎች መካከል በተፈጠረው ፍጥጫ ጉዳት ስለመድረሱ የዘገበው ኦኤምኤን ተጨማሪ ማብራሪያ ግን አልሰጠም። የፌዴራል የጸጥታ አስከባሪዎች ኃይል ጨምረው የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አመራሮችን በቁጥጥር ሥር እንዳዋሉ የቴሌቭዥን ጣቢው ዘግቧል። ኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ጀዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ «ለጊዜው የታሰሩበት ቦታ አልታወቀም» ብሏል። በውጭ አገር የተመሠረተው እና አቶ ጀዋር መሐመድ በኃላፊነት ሲመሩት የነበሩት … [Read more...] about ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ
Archives for June 2020
አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም
ለዚህ ሃሳብ ማብራሪያ የሰጡት የህወሓት ሊቀ መንበርና የትግራይ ክልል መንግሥት ምክትል ርዕስ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ውይይቱ የተናጠል ሳይሆን ሁሉንም አካላት ማካተት እንዳለበት መናገራቸውን ጠቅሷል። "የውውይት መድረክ መፈጠር ካለበት፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ድርጅቶች፣ ብሔር ብሔረሰቦችን የሚወክሉ ፌደራሊስት ኃይሎች የሚሳተፉበት አገራዊ መድረክ መዘጋጀት አለበት እንጂ ከህወሓት/ትግራይ መንግሥት ጋር በድብቅ የሚደረግ ውይይት አንቀበልም፤ ትርጉምም አያመጣም" ማለታቸውን ቢሮው ገልጿል። ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ "ውይይቱ በመጨረሻ ሰዓት የተጀመረ ቢሆንም መሞከሩ ግን ጥሩ ነው" ያሉ ሲሆን ጨምረውም "የአገሪቱን ችግር ለመፍታት የሚንቀሳቀስ አካል ችግሩ የተፈጠረው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ በአገሪቱ አምባገናናዊ ሥርዓት ለመገንባት እየተሯሯጠ በሚገኘው … [Read more...] about አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም
ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት
(በዶክተር ኃይለልዑል መኮንን) ዛሬ ላይ በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያዎች በስፋት አየተዘገበ ስላለው የኮሮና መድሀኒት ተገኘ የተባለው ዴክሳሜታሶን መድሀኒት አዲስ የተገኘ ሳይሆን ከዚህ በፊት እኛም ሀገር ላይ በስፋት ስንጠቀምበት የነበረ መድሀኒት ነዉ። ዴክሳሜታሶን (Dexamethasone) የሚባለው ስቴሮይድስ (Steroids) ከሚባለው ቤተሰብ የሚመደብ የመድኃኒት ዓይነት እ.ኤ.አ ከ1960 ጀምሮ ለተለያዩ በሽታዎች ጥቅም ላይ ሲዉል የቆየ ነው። ዛሬ ቢቢሲ ላይ የተዘገበዉ መድሀኒት የመተንፈስ ችግር እና በጽኑ የኮሮና ቫይረስ ሕመም ላይ ያሉ ሰዎችን እንጂ መጠነኛ (Mild Symptoms) ምልክት ላላቸው እንደማይጠቅም በጥናቱ ላይ አስፍረዋል። በተጨማሪ ስቴሮይድስ (Steroids) ' በከፍተኛ ጥንቃቄ' የሚሰጡ መድኃኒቶች ሲሆኑ በርካታ 'የጎንዮሽ ጉዳት' እንዳላቸው … [Read more...] about ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት
የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ!
ሙሉ የጸሃይ ግርዶሽ በየ3 ዓመት ሁለት (2) ጊዜ ሲከሰት፤ በአንድ ሥፍራ ላይ በድጋሚ ለመከሰት እስከ 400 ዓመት ሊፈጅ ይችላል። ከዚህ በኋላ በሀገራችን ብዙ ሰዎች የሚመለከቱት ከሰኔ 14ቱ ጋር ተመሳሳይ ግርዶሽ የሚከሰተው ከ54 ዓመት በኋላ ሲሆን ሐረር፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ፣ ደብረ ብርሃን እና ደብረ ማርቆስ እሳታማ ቀለበት ለመመልከት ዕድለኛ ሥፍራዎች ይሆናሉ። ማሳሰቢያ፦ የጸሃይ ግርዶሽ በዓይን መመልከት ቋሚ ጉዳት በዓይን ላይ ያደርሳል፤ “ሶላር ኢክሊፕስ” መነፅር በመጠቀም፣ በጨለማ ክፍል ውስጥ በቀዳዳ የሚገባ የጸሃይ ብርሃን የሚስለውን ቅርፅ በመመልከት ወይም ፒን ሆል ካሜራ በመሥራት መመልከት ይቻላል። የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ማኅበረሰብ … [Read more...] about የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ!
የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል
የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ደግም ለተጀመረው ድርድር እንቅፋት መሆኑን የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ገለፁ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አምስተኛ ቀኑን በያዘው የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ የሶስትዮሽ ድርድር የእስካሁን ውጤት ላይ እየሰጡት ባለው መግለጫ የግብፅ የእኔ ጥቅም ብቻ ይጠበቅ አቋም ድርድሩን እየተፈታተነ ነው ብለዋል። ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፥ ግብፅ በድርድሩ በተለመደው ሁለት አካሄዷ ቀጥላበታለች ነው ያሉት። ግብፅ አንድ እግሯን ድርድሩ ላይ አንድ እግራን የፀጥታው ምክር ቤት አስቀምጣ መደራደርን መምረጧን በማንሳት። በድርድሩ ግብፃውያኑ የፈለጉት እና የጠየቁት ሁሉ እንዲሰጣቸው ይፈልጋሉ የሚሰጡት ግን የላቸውም ነው ያሉት። ግብፅ የጋራ ስምምነት ላይ ሳይደረስ ኢትዮጵያ ውሃ መሙላት አትችልም የሚል ተቀባይነት የሌለው … [Read more...] about የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል