ኢትዮ ቴሌኮም ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የሞባይል ማስፋፊያ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ አገልግሎቱ አሁንም በሞባይል አገልግሎት ላይ የሚታየውን ችግር ሊቀርፍ ባለመቻሉ፣ በተለይ ሰሞኑን ከአገልግሎት ጥራት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው በተወሰኑ ቦታዎች እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ይላል፡፡ በተለይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማዋ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች፣ የሞባይል መቆራረጥና የጥሪ መስተጓጎል ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም ባለፉት አምስት ቀናት ግን ችግሩ ይበልጥ መባባሱን አመልክተዋል፡፡ ካለፈው ዓርብ ማምሻውን ጀምሮ በሞባይል ስልኮች ለመጠቀም ከፍተኛ ችግር እንዳጋጠማቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሞባይል ጥሪ … [Read more...] about የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ
Archives for October 2014
ከምርጫ ’97 “የተማረው” ኢህአዴግና የሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የ2007 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ከሰሞኑ ለመነሻ ያህል የቀረበ ነው በሚል ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ለፓርቲዎቹ ለማስተዋወቅ ሞክሮ ነበር፡፡ ይህን የጊዜ ሰሌዳና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ከፓርቲዎቹ ጋር ለመምከር በሶስት ዋና ዋና ከተሞች (አዲስ አበባ፣ አዳማ እና ሀዋሳ) ፓርቲዎቹን ከፋፍሎ ለውይይት ጠርቶ የነበረ ቢሆንም ጥቂት የማይባሉ ፓርቲዎች መድረኩን ጥለው መውጣታቸው የሚታወስ ነው፡፡ ፓርቲዎቹ የምርጫ ጊዜውን በተመለከተ ከመነጋገራችን በፊት በርካታ ልንነጋገርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገቡና በደብዳቤ ለምርጫ ቦርድ የገለጽናቸው ጉዳዮች ስላለሉ ለእነዚያ ጉዳዮች ቅድሚያ መሰጠት ይገባዋል ከሚል መነሻ ነበር፡፡ ምንም እንኳ ቦርዱ የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ እንዳለ የቀጠለ ቢሆንም፡፡ ያም ሆነ ይህ ምርጫ ቦርድ ለውይይት ያቀረበው ረቂቅ የምርጫ ጊዜ … [Read more...] about ከምርጫ ’97 “የተማረው” ኢህአዴግና የሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ
“አርማጌዶን” የፍጻሜያችን ፍጻሜ!
በዚያው ሰሞን ነው የወያኔ ባለሥልጣናት ሲያሾፉብን “ይሄንን ሁሉ ሰይጣናዊ ድርጊት የሚፈጽሙት በዓላማ እነሱ መሆናቸው ተረስቶ” ከመሀከላቸው አንዱ ምን አለ “የሕወሀት መሪዎች በዚህ ወቅት በብሔሮች መካከል ያለው የጥላቻ መንፈስና የወደፊት የሀገሪቱ ሁኔታ እጅግ አሳስቧቸዋል በጣምም እየተጨነቁበት ያሉበት ጉዳይ ነው የብሔራዊ እርቅ ጉዳይ አስፈላጊነቱ የግድ እንደሆነ ያስባሉ እንዴትና ከማን ጋራ እንደሚጨርሱት ተቸግረው ነው እንጅ….” ብሎ ቀለደብን፡፡ ከእኛም ወገን ደግሞ ጅሎቹ የዋሀኑ ተላሎቹ እውነት መስሏቸው በየፊናቸው አንዳንድ ነገሮችን እስከማለት ደረሱ፡፡ ወያኔ ግን ወያኔ ነውና ንጹሕ መስለው አሳሰበን ካሉ በኋላም እንደትናንቱ ሁሉ ዛሬም በዓላማ ይሄንን ሰይጣናዊ የዘርና የሃይማኖት ግጭት ፍጅት ለመፍጠር ሴራውንና ድርጉቱን እየፈጸመ ይገኛል ተፈጥሯዊ ባሕርይው ነውና እስካለ ጊዜ … [Read more...] about “አርማጌዶን” የፍጻሜያችን ፍጻሜ!
እርሳስና ላጲስ
እርሳስ በጓደኛው፤ በብዕር እስክሪፕቶ ባለው ገደብ የለሽ፤ ነጻነቱ ቀንቶ እንዳሻው ቢናገር፤ የልቡን አውጥቶ እንዲህ አልክ ብሎ፤ ያለውን አጥፍቶ የሚያስወግድበት፤ በላጲስ አንሥቶ ስለማይከላ፤ ሲናገር አፍ ከፍቶ ፡፡ እሱ ግን ዘለዓለም፤ በላጲሱ ጠፍቶ መኖሩ አስመርሮት፤ በእጅጉ ተከፍቶ እኔስ ለምን እንዴት? ማለት ጀመረና ጠየቀ አፋጠጠ፤ ተሰማው ፍነና ነጻነቱን ሊያውጅ፤ ተነሣ ይሄ ጀግና ከእንግዲህ በኋላ፤ አለ ቆፍጠን ብሎ የነበረውን ፍርሐት፤ ከልቡላይ ነቅሎ ከእንግዲህ ወዲህ፤ አለ አንሥቶ ክንዱን ባናቴ ያለው ላጲስ፤ ገደብ የለሽ ሥልጣን አብቅቷል ብያለሁ፤ ይሰማ አዋጀ የሚጸና ይሆናል፤ በትውልድ ልጅ ልጀ ከዚህች ቀን በኋላ፤ ማንም ያላወቀ በእውቀት ያለበቃ፤ ከንቱ ያልጠነቀቀ ዐሥሬ እየጻፈ፤ እየለቀለቀ ዐሥሬ የሚያጠፋ፤ መሀይም የወደቀ ውሸት … [Read more...] about እርሳስና ላጲስ
የጅዳው ት/ቤታችን እንደ አረቡ አብዮት ከድጡ ወደ ማጡ!
የጅዳ የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህርት ቤት በተወሳሰበ የአሰራር፣ አመራር ሂደት ውስጥ በማለፍም ቢሆን የመማር ማስተማር ሒደቱን ከጀመረ ሁለት ወር ደፍኗል። በሁለት ወራት ልጆቻችን ተምረው ተመለሱ ብሎ ለጠየቀ ምላሹ ቆሽት ያሳርራል። በእስካሁኑ የትምህርት ቅበላ ባለው ከስድስት ያላነሰ ክፍለ ጊዜ የሚማሩት ከሁለትና ሶስት ክፍለ ጊዜ ሲሆን አልፎ አልፎ አራት ክፍለ ጊዜ ብቻ ተምረው ይመለሳሉ። ይህን እውነታ ልጆቹን እንደማዋያ ጥሎ ዘወር የሚለው ባይተዋር ወላጅ ከልጆቹ ይሰማዋል። የልጆቹን ደብተር አገላብጦ የሚመለከት የእኔ ቢጤ ብስጩ አባት ደግሞ ከልጆቹ ከመስማት አልፎ በማስረጃ ደብተሩን ሲያገላብጥ የሚታዘበው እውነታ ነው። በአንዳንድ ክፍሎች ዘመናዊውን ትምህርት ትምህርት የሚያሰኙት የእንግሊዝኛና የሒሳብን ጨምሮ ከፍ ሲል የኬሚስትሪ፣ የፊዚክስ፣ የባዮሎጂና የኮምፒውተር ትምህርቶች … [Read more...] about የጅዳው ት/ቤታችን እንደ አረቡ አብዮት ከድጡ ወደ ማጡ!
“የዲግሪና የዲፕሎማ ወፍጮ ቤቶች”
በእንግሊዝኛው አጠራር የዲፕሎማ/የዲግሪ ወፍጮ ቤት (diploma/degree mills) ይባላሉ፡፡ በርካታዎቹ ሠለጠነ በሚባለው ዓለም ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ “ወፍጮ ቤቶች” የ“ትምህርት መረጃ” ለማግኘት በጣም ቀላል ነው፡፡ ዋናው መስፈርት አስፈላጊውን “የትምህርት ክፍያ” መፈጸም ብቻ ነው ፡፡ ከዚያ በወርቅ ቅብ የተንቆጠቆጠ “የባችለር” ወይም “የማስተርስ” ወይም “የዶክትሬት (ፒ.ኤች.ዲ.)” ዲግሪዎችን ማፈስ ነው፡፡ በቀጣይ የሚሆነው የ…ሚ/ር ወይም የ…ሚኒስትር ደኤታ ወዘተ መሆንና “በሹመት መዳበር” ነው፡፡ ከዚያ ህዝብ አናት ላይ "በስያሜ" ተቀምጦ መጋለብ ነው። ከዓመታት በፊት የአሜሪካው የመንግሥት ተጠያቂነት ቢሮ በዚህ ጉዳይ ላይ ምርመራ አካሂዶ ነበር፡፡ ያገኘውንም ውጤት ለእንደራሴዎች ምክር ቤት ሲያቀርብ “የወፍጮ ቤቶቹን” አሠራር በግልጽ ዘርዝሯል፡፡ ለምርመራው ያነሳሳው … [Read more...] about “የዲግሪና የዲፕሎማ ወፍጮ ቤቶች”
ሰማያዊ፣ መኢዴፓና ኢብአፓ የምርጫ ቦርድን ስብሰባ ረግጠው ወጡ
ምርጫ ቦርድ በጊዜ ሰሌዳ ላይ ለመወያየት በጊዮን ሆቴል የጠራውን ስብሰባ “ጥያቄዎቻችን የሚመልስ አይደለም” በሚል የሰማያዊ ፓርቲ ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ በተጨማሪም የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (መኢዴፓ) እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው ወጥተዋል፡፡ ፓርቲዎቹ በትናንትናው ዕለት ከምርጫ 2007 ዓ.ም በፊት ውይይት ሊደረግባቸውና ሊፈቱ ይገባል ያሏቸውን ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ ያስገቡ ቢሆንም በዛሬው ስብሰባ በደብዳቤ ካሳወቋቸው ችግሮች ይልቅ የጊዜ ሰሌዳ ቅድሚያ የተሰጠው በመሆኑ የምርጫ ምህዳሩን ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም ብለው ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ስብሰባውን ረግጠው ከወጡት መካከል የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ዋና … [Read more...] about ሰማያዊ፣ መኢዴፓና ኢብአፓ የምርጫ ቦርድን ስብሰባ ረግጠው ወጡ
The honorable Ato Gebru Asrat and his politics
The honorable Ato Gebru Asrat has written a very fat book that is five hundred pages long. I am assuming that the purpose of the book was to present himself as a person of vision and to show us his leadership ability and a map of the road to the future. Unfortunately, he has a handicap that cannot be glossed over since for many years he has operated as member of that infamous organization TPLF (ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) that is still creating havoc in the life of our people and our country. It is a … [Read more...] about The honorable Ato Gebru Asrat and his politics
ሥነ-ኪን ወይስ ኪነ-ጥበብ?
ብዙውን ጊዜ ሥነ-ኪን ወይም የጥበብ ሥራ፣ ነገረ-ጥበብ ማለት እንፈልግና ኪነ-ጥበብ የሚለውን ቃልና ሥነ-ጥበብ የሚለውን ቃል እያጣረስን ስንጠቀም እንስተዋላለን፡፡ ኪነ-ጥበብ ወይም ኪነ-ጥበባት የሚለው ቃል ራሱ ግራ የተጋባ ቃል ነው፡፡ ልንጠቀምበት ፈልገን በምንጠቀምበት ቦታ ሁሉ ሰዋስዉ የተሳሳተ (Grammatically wrong) በሆነ መንገድ ነው፡፡ ቃሉ የግዕዝ ቃል ቢሆንም እነኝህን ሁለት ቃላት ማጣመር ግን የሰዋስው ስሕተትን ይፈጥራል፡፡ ምክንያቱም ኪን የሚለው ቃል ትርጉም ራሱ ጥበብ ማለት ነውና፡፡ ስለዚህም ኪነ-ጥበባት ስንል ጥበበ ጥበባት ማለታችን ነው ማለት ነው፡፡ ይሄም ማለት የጥበቦች ጥበብ ወይም ከጥበቦች ሁሉ የበላይ ጥበብ የሚል ትርጉምን ይሰጣል እንጅ አጠቃላይ የጥበብ ሥራ ዘርፍ ማለት አይደለም፡፡ ንጉሠ ነገሥታት ማለት የነገሥታት ንጉሥ ማለት እንደ ሆነ ሁሉ ማለት … [Read more...] about ሥነ-ኪን ወይስ ኪነ-ጥበብ?
የእርቅና መግባባት ዳሰሳ ጥናት ውጤት
የሚከተለው ውጤት ድህረ ገፆች ላይ ከወጡት ፅሁፎቼ ሊንክ በማድረግ በዚህ ድህረ ገፅ ላይ የተሰበሰበ የዳሰሳ ጥናት ነው። ጥናቱ ሳይንሳዊ ያልሆነ ቢሆንም ለመንደርደሪያ ጥናትና አሳብ ሊረዳ ይችል ይሆናል ብዬ አስባለው። ይህ ማለት ስለ እርቅና መግባባት ውስብስብ ጥያቄ እልባት ለማግኘት አይደለም። ያ በእኔ አይሞከርም ከአቅሜ በላይ ነውና። ዓላማዬ ስለ እርቅ ቅድመ ሁኔታዎች መንደርደሪያ አሳብ ለመሰብሰብ በማሰብ ነው። እነሆ ድምፅ የሰጡትን ሰዎች አሳቦች አጠርና ጠቅለል አድርጌ ከዚህ በታች በጥሬው አቅርቤያለው። የራሴን ትንታኔ ትቸዋለሁ። ያንን ለአንባቢው እተዋለሁ። በዚህ ዳሰሳ ጥናት ላይ የተሳተፉትን ከልብ አመሰግናለው። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ። ፍቅርም ይስጠን። Q1: Which generation are you? የትኛው ትውልድ ነዎት? 77.5% I am 30 years old or … [Read more...] about የእርቅና መግባባት ዳሰሳ ጥናት ውጤት