• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሰማያዊ፣ መኢዴፓና ኢብአፓ የምርጫ ቦርድን ስብሰባ ረግጠው ወጡ

October 17, 2014 10:04 am by Editor Leave a Comment

ምርጫ ቦርድ በጊዜ ሰሌዳ ላይ ለመወያየት በጊዮን ሆቴል የጠራውን ስብሰባ “ጥያቄዎቻችን የሚመልስ አይደለም” በሚል የሰማያዊ ፓርቲ ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ በተጨማሪም የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (መኢዴፓ) እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው ወጥተዋል፡፡ ፓርቲዎቹ በትናንትናው ዕለት ከምርጫ 2007 ዓ.ም በፊት ውይይት ሊደረግባቸውና ሊፈቱ ይገባል ያሏቸውን ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ ያስገቡ ቢሆንም በዛሬው ስብሰባ በደብዳቤ ካሳወቋቸው ችግሮች ይልቅ የጊዜ ሰሌዳ ቅድሚያ የተሰጠው በመሆኑ የምርጫ ምህዳሩን ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም ብለው ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ስብሰባውን ረግጠው ከወጡት መካከል የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ዋና ጸኃፊ ወ/ት መሊሃ ጀሃድ “ትናንትና 12 ፓርቲዎች ሆነን ፈርመን ያስገባነው ደብዳቤ ነበር፡፡ በዚህ ደብዳቤ ባነሳናቸው ጥያቄዎች ላይ መልስ ካልተሰጠን በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ላይ እንደማንነጋገር ገልጸን ነበር፡፡ ቦርዱ ደግሞ ትናንትና ባስገባነው ደብዳቤ ላይ ከመነጋገርና ለጥያቄዎቹ መልስ ከመስጠት ይልቅ በጊዜ ሰሌዳው ላይ ነው የምንነጋገረው አለን፡፡ ምርጫ ቦርድ ኃላፊዎች ስለ ጊዜ ሰሌዳው እንድንነጋገር ሲያደርጉ እኛ በአካሄድ ጥያቄዎቻችን መልስ እንዲሰጥ ጠየቅን፡፡ የቦርዱ ተወካዮች እሱን በሌላ ጊዜ ስብሰባዎች ላይ እንፈታዋለን፣ ዛሬ ስለ ጊዜ ሰሌዳው እንነጋገር በማለታቸው ስብሰባውን ረግጠን ወጥተናል” ስትል ረግጠው የወጡበትን መነሻ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻለች፡፡

eth electionበተመሳሳይ የመኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ኑሪ ሙደሂር “ምርጫ ቦርድ ነጻና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አደርጋለሁ የሚለው አባባሉ ተግባራዊ እንዲሆን ጥያቄዎችን አቅርበን ነበር፡፡ ይህን ጥያቄ የዛሬ 5 አመትም ጠይቀናል፡፡ ትናንትም በጋራ በደብዳቤ አስገብተናል፡፡ ገዥው ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ከጀመረ 5 አመቱ ነው፡፡ ይህን ቅስቀሳ የሚያደርገው በመንግስት ገንዘብ ነው፡፡ የእኛ ጥያቄ የምርጫ ምህዳሩ መስፋት አለበት ነው፡፡ ትርጉም ያለው ምርጫ መደረግ አለበት ነው የእኛ እምነት፡፡ ይህን ለማድረግ የሚያስችሉ ጥያቄዎችን ለመመለስ ፈቃደኛ ስላልሆኑ ነው እኛ ስብሰባውን ረግጠን የወጣነው” ብለዋል፡፡

ሌላኛው የመኢዴፓ ተወካይና የፓርቲው ዋና ጸኃፊ አቶ ዘመኑ ሞላ በበኩላቸው “እነሱ ካቀረቡት የጊዜ ሰሌዳ ይልቅ የሚቀድመው ሜዳውን ማስፋት ነው፡፡ ትናንትና 12 ፓርቲዎች ተፈራርመን ያስገባነው ደብዳቤ ነበር፡፡ እኛም ቀድመን በተነጋገርነው መሰረት የጊዜ ሰሌዳው ጉዳይ ቀዳሚ አጀንዳ መሆን የለበትን የሚል አቋም ይዘናል” ሲሉ ስብሰባውን ካዘጋጀው ምርጫ ቦርድ ጋር ያላቸውን ልዩነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ምርጫ ቦርድ በሚቀጥለው ስለ ችግሮቻችሁ ቁጭ ብለን እንወያያለን በሚል የማባበል ስራ እንደያዘ የገለጹት አቶ ዘመኑ “የ2002ትን ምርጫን ገምግመናል፡፡ ፓርቲዎች ያስገባነው ደብዳቤ አለ፡፡ አሁንም ገዥው ፓርቲ ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሜዳውን እያጠበበና ራሱ ብቻ እየተጫወተበት ይገኛል፡፡ ትክክለኛ ምርጫ ለማድረግ ከታሰበ እናንተም ከገዥው ፓርቲ ጋር ያላችሁን ግንኙነት ቆም ብላችሁ አስቡበት ብለናቸዋል፡፡ ያቀረብናቸው ጥያቄዎች ቅድሚያ ስላልተሰጣቸው ስብሰባውን ረግጠን ለመውጣት ተገደናል” ብለዋል፡፡

ዘግይቶ በደረሰን መረጃ የኢትዮጵያ ማህረ ዴሞክራሲ ደቡብ ህብረት አንድነት ፓርቲ ተወካይ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስም ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸው ተግልጾአል፡፡

በትናንትናው ዕለት 12 የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ከምርጫ ከጊዜ ሰሌዳው በፊት በውይይት መፈታት አለባቸው ብለው ያመኑባቸውን ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ በደብዳቤ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ (ምንጭ፤ ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule