• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ

October 23, 2014 08:15 pm by Editor Leave a Comment

ኢትዮ ቴሌኮም ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የሞባይል ማስፋፊያ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ አገልግሎቱ አሁንም በሞባይል አገልግሎት ላይ የሚታየውን ችግር ሊቀርፍ ባለመቻሉ፣ በተለይ ሰሞኑን ከአገልግሎት ጥራት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው በተወሰኑ ቦታዎች እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ይላል፡፡

በተለይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማዋ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች፣ የሞባይል መቆራረጥና የጥሪ መስተጓጎል ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም ባለፉት አምስት ቀናት ግን ችግሩ ይበልጥ መባባሱን አመልክተዋል፡፡

ካለፈው ዓርብ ማምሻውን ጀምሮ በሞባይል ስልኮች ለመጠቀም ከፍተኛ ችግር እንዳጋጠማቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሞባይል ጥሪ ቅዳሜና እሑድም ተባብሶ መቀጠሉን ደንበኞች በምሬት ገልጸዋል፡፡ ከጥሪ አገልግሎትም በተጨማሪ በአጭር ጽሑፍ መልዕክትና የሒሳብ መጠየቂያና የቅድመ ክፍያ ካርዶችን ለመሙላት እንኳን አዳጋች ሆኖ ነበር፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አብዱራሂም አህመድ  ሰሞኑን የባሰበትን የሞባይል አገልግሎት መስተጓጎልና መቆራረጥ አምነው፣ ‹‹በአሁኑ ጊዜ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በተለይ በአራዳ ክፍለ ከተማ አካባቢ የኃይል መቆራረጥ በማጋጠሙ ኦሲኤስ (OCS) የተባለው ኃይል አስተላላፊ ሥራ በማቋረጡ ችግሩ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ እንደ እሳቸው ገለጻ ችግሩ የተስተዋለው የቅድመ ክፍያ አገልግሎት የሚሰጡ (Prepaid) የሞባይል መስመሮች ላይ ነበር፡፡

አቶ አብዱራሂም ይህንን ቢሉም፣ ጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ከማለዳ ጀምሮ የጥሪ ችግሩ በሞባይል ስልኮች ላይና በመደበኛ የስልክ አገልግሎቶች ላይ ተስተውሏል፡፡ በተመሳሳይም ችግሩ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በዱከም፣ በቢሾፍቱና በአጎራባች ከተሞች ጭምር መከሰቱን ደንበኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

‹‹ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል የማስፋፊያ ሥራዎችን አጠናቅቄያለሁ፤ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን ቀርፌዋለሁ ባለ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ችግሩ በድጋሚ ተከስቷል፡፡ አሁን ደግሞ እንደሚታየው ላለፉት አምስት ቀናት ያህል ጭራሽ ኔትወርኩ ሞቷል፡፡ ወይ አንድ ፊቱኑ ሞባይል የሚባለውን ነገር ቢተውት ይሻላል፤›› ሲል ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚጓዝ ታክሲ ላይ ሪፖርተር ያነጋገርነው ተሳፋሪ ገልጿል፡፡

ባለፈው ዓመት መጨረሻ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ተከናውኗል ያለውን የሞባይል ማስፋፊያ ሥራ ሙሉ ለሙሉ በቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ አማካይነት ማከናወኑንና የነበሩት የአገልግሎት ችግሮች መቀረፋቸውን ኢትዮ ቴሌኮም መግለጹ ይታወሳል፡፡ ከመደበኛው የሞባይል ማስፋፊያ በተጨማሪ ‹‹3G›› እና ‹‹4G›› የተባሉት አገልግሎቶች መጠናቀቃቸውንና ለተጠቃሚዎች ዝግጁ መሆናቸውም ጨምሮ አስታውቆ ነበር፡፡ የ‹‹3G›› አገልግሎት የተጀመረ ቢሆንም እስካሁን የ‹‹4G›› አገልግሎት ግን አልተጀመረም፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ከቻይናዎቹ ሁዋዌ እና ዜድቲኢ ኩባንያዎች የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት በፊት ተፈራርሟል፡፡ እስካሁን ግን በስምምነቱ መሠረት የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ቢጀመርም፣ መላ አገሪቱን የሚያዳርሰው ግን አለመጀመሩ ይታወቃል፡፡

ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች እያንዳንቸው የ800 ሚሊዮን ዶላር ሥራ የተረከቡ ሲሆን፣ ዜድቲኢ የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ሙሉ በመሉ ለተቀናቃኙ ዜድቲኢ መሰጠቱ እንዳላስደሰተው እየተነገረ ነው፡፡ ረዥም ጊዜ የወሰደ ተጨማሪ ውይይት ከመንግሥት ጋር እያደረገ እንደነበር በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በዜድቲኢ ሥራ አለመጀመርና በአዲስ አበባ ተጠናቋል በተባለው ፕሮጀክት በመንግሥትና በኢትዮ ቴሌኮም ላይ የሕዝብ ጥያቄ እየተነሳ ነው፡፡

ባለፈው ዓመት ፓርላማው ጭምር በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ሲነሱበት መቆየቱም ይታወሳል፡፡ በተለይም ከመደበኛ ስብሰባዎች በተጨማሪ የመሠረተ ልማት፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የድርጅቱን ኃላፊዎች በተደጋጋሚ በመጥራት ማብራሪያ መጠየቁና ማሳሰቢያም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

አቶ አብዱራሂም አህመድ፣ በተደጋጋሚ ወደ ሕዝብ በመውጣት ድርጅቱን በሚመለከት በሕዝብ የሚነሱ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት በመገናኛ ብዙኃን ብቅ ማለታቸው የተለመደ ቢሆንም፣ ነገር ግን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አንዱአለም አድማሴንና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ቀርበው ያለውን ሁኔታ አለማስረዳታቸው የድርጅቱን አጠቃላይ አሠራር ግልጽ እንዳይሆን ተፅዕኖ ማድረጉንና በድርጅቱ አቅም ላይም ብዥታን እየፈጠረ መሆኑን የሚገልጹ አስተያየት ሰጪዎች አሉ፡፡

ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ በቀረው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መጨረሻ በአገር አቀፍ ደረጃ የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር 59 ሚሊዮን ለማድረስ የታቀደ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተጠቃሚዎች ቁጥር 29 ሚሊዮን መድረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule