• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ

October 23, 2014 08:15 pm by Editor Leave a Comment

ኢትዮ ቴሌኮም ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የሞባይል ማስፋፊያ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ አገልግሎቱ አሁንም በሞባይል አገልግሎት ላይ የሚታየውን ችግር ሊቀርፍ ባለመቻሉ፣ በተለይ ሰሞኑን ከአገልግሎት ጥራት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው በተወሰኑ ቦታዎች እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ይላል፡፡

በተለይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማዋ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች፣ የሞባይል መቆራረጥና የጥሪ መስተጓጎል ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም ባለፉት አምስት ቀናት ግን ችግሩ ይበልጥ መባባሱን አመልክተዋል፡፡

ካለፈው ዓርብ ማምሻውን ጀምሮ በሞባይል ስልኮች ለመጠቀም ከፍተኛ ችግር እንዳጋጠማቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሞባይል ጥሪ ቅዳሜና እሑድም ተባብሶ መቀጠሉን ደንበኞች በምሬት ገልጸዋል፡፡ ከጥሪ አገልግሎትም በተጨማሪ በአጭር ጽሑፍ መልዕክትና የሒሳብ መጠየቂያና የቅድመ ክፍያ ካርዶችን ለመሙላት እንኳን አዳጋች ሆኖ ነበር፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አብዱራሂም አህመድ  ሰሞኑን የባሰበትን የሞባይል አገልግሎት መስተጓጎልና መቆራረጥ አምነው፣ ‹‹በአሁኑ ጊዜ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በተለይ በአራዳ ክፍለ ከተማ አካባቢ የኃይል መቆራረጥ በማጋጠሙ ኦሲኤስ (OCS) የተባለው ኃይል አስተላላፊ ሥራ በማቋረጡ ችግሩ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ እንደ እሳቸው ገለጻ ችግሩ የተስተዋለው የቅድመ ክፍያ አገልግሎት የሚሰጡ (Prepaid) የሞባይል መስመሮች ላይ ነበር፡፡

አቶ አብዱራሂም ይህንን ቢሉም፣ ጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ከማለዳ ጀምሮ የጥሪ ችግሩ በሞባይል ስልኮች ላይና በመደበኛ የስልክ አገልግሎቶች ላይ ተስተውሏል፡፡ በተመሳሳይም ችግሩ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በዱከም፣ በቢሾፍቱና በአጎራባች ከተሞች ጭምር መከሰቱን ደንበኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

‹‹ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል የማስፋፊያ ሥራዎችን አጠናቅቄያለሁ፤ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን ቀርፌዋለሁ ባለ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ችግሩ በድጋሚ ተከስቷል፡፡ አሁን ደግሞ እንደሚታየው ላለፉት አምስት ቀናት ያህል ጭራሽ ኔትወርኩ ሞቷል፡፡ ወይ አንድ ፊቱኑ ሞባይል የሚባለውን ነገር ቢተውት ይሻላል፤›› ሲል ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚጓዝ ታክሲ ላይ ሪፖርተር ያነጋገርነው ተሳፋሪ ገልጿል፡፡

ባለፈው ዓመት መጨረሻ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ተከናውኗል ያለውን የሞባይል ማስፋፊያ ሥራ ሙሉ ለሙሉ በቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ አማካይነት ማከናወኑንና የነበሩት የአገልግሎት ችግሮች መቀረፋቸውን ኢትዮ ቴሌኮም መግለጹ ይታወሳል፡፡ ከመደበኛው የሞባይል ማስፋፊያ በተጨማሪ ‹‹3G›› እና ‹‹4G›› የተባሉት አገልግሎቶች መጠናቀቃቸውንና ለተጠቃሚዎች ዝግጁ መሆናቸውም ጨምሮ አስታውቆ ነበር፡፡ የ‹‹3G›› አገልግሎት የተጀመረ ቢሆንም እስካሁን የ‹‹4G›› አገልግሎት ግን አልተጀመረም፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ከቻይናዎቹ ሁዋዌ እና ዜድቲኢ ኩባንያዎች የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት በፊት ተፈራርሟል፡፡ እስካሁን ግን በስምምነቱ መሠረት የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ቢጀመርም፣ መላ አገሪቱን የሚያዳርሰው ግን አለመጀመሩ ይታወቃል፡፡

ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች እያንዳንቸው የ800 ሚሊዮን ዶላር ሥራ የተረከቡ ሲሆን፣ ዜድቲኢ የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ሙሉ በመሉ ለተቀናቃኙ ዜድቲኢ መሰጠቱ እንዳላስደሰተው እየተነገረ ነው፡፡ ረዥም ጊዜ የወሰደ ተጨማሪ ውይይት ከመንግሥት ጋር እያደረገ እንደነበር በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በዜድቲኢ ሥራ አለመጀመርና በአዲስ አበባ ተጠናቋል በተባለው ፕሮጀክት በመንግሥትና በኢትዮ ቴሌኮም ላይ የሕዝብ ጥያቄ እየተነሳ ነው፡፡

ባለፈው ዓመት ፓርላማው ጭምር በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ሲነሱበት መቆየቱም ይታወሳል፡፡ በተለይም ከመደበኛ ስብሰባዎች በተጨማሪ የመሠረተ ልማት፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የድርጅቱን ኃላፊዎች በተደጋጋሚ በመጥራት ማብራሪያ መጠየቁና ማሳሰቢያም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

አቶ አብዱራሂም አህመድ፣ በተደጋጋሚ ወደ ሕዝብ በመውጣት ድርጅቱን በሚመለከት በሕዝብ የሚነሱ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት በመገናኛ ብዙኃን ብቅ ማለታቸው የተለመደ ቢሆንም፣ ነገር ግን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አንዱአለም አድማሴንና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ቀርበው ያለውን ሁኔታ አለማስረዳታቸው የድርጅቱን አጠቃላይ አሠራር ግልጽ እንዳይሆን ተፅዕኖ ማድረጉንና በድርጅቱ አቅም ላይም ብዥታን እየፈጠረ መሆኑን የሚገልጹ አስተያየት ሰጪዎች አሉ፡፡

ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ በቀረው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መጨረሻ በአገር አቀፍ ደረጃ የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር 59 ሚሊዮን ለማድረስ የታቀደ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተጠቃሚዎች ቁጥር 29 ሚሊዮን መድረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule