• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ

October 23, 2014 08:15 pm by Editor Leave a Comment

ኢትዮ ቴሌኮም ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የሞባይል ማስፋፊያ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ አገልግሎቱ አሁንም በሞባይል አገልግሎት ላይ የሚታየውን ችግር ሊቀርፍ ባለመቻሉ፣ በተለይ ሰሞኑን ከአገልግሎት ጥራት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው በተወሰኑ ቦታዎች እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ይላል፡፡

በተለይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማዋ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች፣ የሞባይል መቆራረጥና የጥሪ መስተጓጎል ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም ባለፉት አምስት ቀናት ግን ችግሩ ይበልጥ መባባሱን አመልክተዋል፡፡

ካለፈው ዓርብ ማምሻውን ጀምሮ በሞባይል ስልኮች ለመጠቀም ከፍተኛ ችግር እንዳጋጠማቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሞባይል ጥሪ ቅዳሜና እሑድም ተባብሶ መቀጠሉን ደንበኞች በምሬት ገልጸዋል፡፡ ከጥሪ አገልግሎትም በተጨማሪ በአጭር ጽሑፍ መልዕክትና የሒሳብ መጠየቂያና የቅድመ ክፍያ ካርዶችን ለመሙላት እንኳን አዳጋች ሆኖ ነበር፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አብዱራሂም አህመድ  ሰሞኑን የባሰበትን የሞባይል አገልግሎት መስተጓጎልና መቆራረጥ አምነው፣ ‹‹በአሁኑ ጊዜ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በተለይ በአራዳ ክፍለ ከተማ አካባቢ የኃይል መቆራረጥ በማጋጠሙ ኦሲኤስ (OCS) የተባለው ኃይል አስተላላፊ ሥራ በማቋረጡ ችግሩ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ እንደ እሳቸው ገለጻ ችግሩ የተስተዋለው የቅድመ ክፍያ አገልግሎት የሚሰጡ (Prepaid) የሞባይል መስመሮች ላይ ነበር፡፡

አቶ አብዱራሂም ይህንን ቢሉም፣ ጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ከማለዳ ጀምሮ የጥሪ ችግሩ በሞባይል ስልኮች ላይና በመደበኛ የስልክ አገልግሎቶች ላይ ተስተውሏል፡፡ በተመሳሳይም ችግሩ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በዱከም፣ በቢሾፍቱና በአጎራባች ከተሞች ጭምር መከሰቱን ደንበኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

‹‹ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል የማስፋፊያ ሥራዎችን አጠናቅቄያለሁ፤ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን ቀርፌዋለሁ ባለ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ችግሩ በድጋሚ ተከስቷል፡፡ አሁን ደግሞ እንደሚታየው ላለፉት አምስት ቀናት ያህል ጭራሽ ኔትወርኩ ሞቷል፡፡ ወይ አንድ ፊቱኑ ሞባይል የሚባለውን ነገር ቢተውት ይሻላል፤›› ሲል ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚጓዝ ታክሲ ላይ ሪፖርተር ያነጋገርነው ተሳፋሪ ገልጿል፡፡

ባለፈው ዓመት መጨረሻ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ተከናውኗል ያለውን የሞባይል ማስፋፊያ ሥራ ሙሉ ለሙሉ በቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ አማካይነት ማከናወኑንና የነበሩት የአገልግሎት ችግሮች መቀረፋቸውን ኢትዮ ቴሌኮም መግለጹ ይታወሳል፡፡ ከመደበኛው የሞባይል ማስፋፊያ በተጨማሪ ‹‹3G›› እና ‹‹4G›› የተባሉት አገልግሎቶች መጠናቀቃቸውንና ለተጠቃሚዎች ዝግጁ መሆናቸውም ጨምሮ አስታውቆ ነበር፡፡ የ‹‹3G›› አገልግሎት የተጀመረ ቢሆንም እስካሁን የ‹‹4G›› አገልግሎት ግን አልተጀመረም፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ከቻይናዎቹ ሁዋዌ እና ዜድቲኢ ኩባንያዎች የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት በፊት ተፈራርሟል፡፡ እስካሁን ግን በስምምነቱ መሠረት የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ቢጀመርም፣ መላ አገሪቱን የሚያዳርሰው ግን አለመጀመሩ ይታወቃል፡፡

ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች እያንዳንቸው የ800 ሚሊዮን ዶላር ሥራ የተረከቡ ሲሆን፣ ዜድቲኢ የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ሙሉ በመሉ ለተቀናቃኙ ዜድቲኢ መሰጠቱ እንዳላስደሰተው እየተነገረ ነው፡፡ ረዥም ጊዜ የወሰደ ተጨማሪ ውይይት ከመንግሥት ጋር እያደረገ እንደነበር በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በዜድቲኢ ሥራ አለመጀመርና በአዲስ አበባ ተጠናቋል በተባለው ፕሮጀክት በመንግሥትና በኢትዮ ቴሌኮም ላይ የሕዝብ ጥያቄ እየተነሳ ነው፡፡

ባለፈው ዓመት ፓርላማው ጭምር በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ሲነሱበት መቆየቱም ይታወሳል፡፡ በተለይም ከመደበኛ ስብሰባዎች በተጨማሪ የመሠረተ ልማት፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የድርጅቱን ኃላፊዎች በተደጋጋሚ በመጥራት ማብራሪያ መጠየቁና ማሳሰቢያም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

አቶ አብዱራሂም አህመድ፣ በተደጋጋሚ ወደ ሕዝብ በመውጣት ድርጅቱን በሚመለከት በሕዝብ የሚነሱ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት በመገናኛ ብዙኃን ብቅ ማለታቸው የተለመደ ቢሆንም፣ ነገር ግን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አንዱአለም አድማሴንና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ቀርበው ያለውን ሁኔታ አለማስረዳታቸው የድርጅቱን አጠቃላይ አሠራር ግልጽ እንዳይሆን ተፅዕኖ ማድረጉንና በድርጅቱ አቅም ላይም ብዥታን እየፈጠረ መሆኑን የሚገልጹ አስተያየት ሰጪዎች አሉ፡፡

ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ በቀረው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መጨረሻ በአገር አቀፍ ደረጃ የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር 59 ሚሊዮን ለማድረስ የታቀደ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተጠቃሚዎች ቁጥር 29 ሚሊዮን መድረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule