• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እርሳስና ላጲስ

October 21, 2014 05:51 am by Editor 3 Comments

እርሳስ በጓደኛው፤ በብዕር እስክሪፕቶ

ባለው ገደብ የለሽ፤ ነጻነቱ ቀንቶ

እንዳሻው ቢናገር፤ የልቡን አውጥቶ

እንዲህ አልክ ብሎ፤ ያለውን አጥፍቶ

የሚያስወግድበት፤ በላጲስ አንሥቶ

ስለማይከላ፤ ሲናገር አፍ ከፍቶ ፡፡

እሱ ግን ዘለዓለም፤ በላጲሱ ጠፍቶ

መኖሩ አስመርሮት፤ በእጅጉ ተከፍቶ

እኔስ ለምን እንዴት? ማለት ጀመረና

ጠየቀ አፋጠጠ፤ ተሰማው ፍነና

ነጻነቱን ሊያውጅ፤ ተነሣ ይሄ ጀግና

ከእንግዲህ በኋላ፤ አለ ቆፍጠን ብሎ

የነበረውን ፍርሐት፤ ከልቡላይ ነቅሎ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ አለ አንሥቶ ክንዱን

ባናቴ ያለው ላጲስ፤ ገደብ የለሽ ሥልጣን

አብቅቷል ብያለሁ፤ ይሰማ አዋጀ

የሚጸና ይሆናል፤ በትውልድ ልጅ ልጀ

ከዚህች ቀን በኋላ፤ ማንም ያላወቀ

በእውቀት ያለበቃ፤ ከንቱ ያልጠነቀቀ

ዐሥሬ እየጻፈ፤ እየለቀለቀ

ዐሥሬ የሚያጠፋ፤ መሀይም የወደቀ

ውሸት የሚደጋግም፤ በላጲስ እየፋቀ

በእጁ አይይዘኝም፤ አለቀ ደቀቀ

ከቶም አይገዛኝም፤ ብሎ አስታወቀ ፡፡

ከእንግዲህ ወዲህ፤ መብቴን ተገፍፌ

አልኖርም ብያለሁ፤ እያለ መዳፌ

እኔም እንደ ብዕር፤ ያሻኝን ብል ጽፌ

ወይም ተናግሬ፤ በዓለም ሕግ ታቅፌ

ያ የተናገርኩት፤ የጻፍኩት ቃል ርኡስ

ይቀመጣል እንጅ፤ እዛው ሳይደመሰስ

ማንም አይፍቀውም፤ እያነሣ ላጲስ

ይሄው አውጃለሁ፤ ይሁን እንደ ቃል ቅዱስ፡፡

ከእንግዲህ በኋላ፤ በዚህ አዋጅ ሥሩ

ስሕተት እንኳን ቢሆን፤ የጻፍኩት ቃል ዘሩ

ይቀመጣል እንጂ፤ ልክ እንደ ብዕሩ

ሠረዝ ተደርጎበት፤ ሳይጠፋ ነገሩ

ለታሪክ ለትምህርት፤ ጠቀምጦ በክብሩ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ የማንም ምን ውላጅ

ከቶም አይፍቀኝም፤ እኔን በላጲስ ፈንጅ፡፡

መስከረም 2007ዓ.ም.

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    October 21, 2014 10:05 am at 10:05 am

    **************************
    አርሳስ…
    እርሳስ በእስክሪብቶ ሁልግዜ ተዛብቶ
    እኔ እየጠፋሁኝ አንተ አትጠፋ ከቶ?
    እስክሪብቶ…
    አንተማ ሞኝ ነህ አጥፊህን በራስህ ተሸክመህ
    ለእግር ሸንካይ በመቅረጫ ተሸራርፈህ
    እኔማ ቀለሜ ላይፈስ ታፍኜ ከላይም ከታችም
    የሚፃፍ ሞልቶ አንድም ዘጋቢና ፀሐፊ አልተገኘም።
    ላጲስ…
    እኔ የሰማሁት የዓሳ ሽታ ከራስ ነው
    የእርሳስ ላይ ጭንቅላትን አጥፊ ማነው ያለው
    እርሳስማ አጠፋኝ ሲል ስሜን አጠፋው
    እስኪሪብቶ ተሳለቀብኝ እንደማላጠፋው
    የተፃፈን ቀበኛ የሚፅፍን የሚያጠፋው ማነው!?
    በለው!

    Reply
  2. Amsalu Gebrekidan says

    October 23, 2014 10:03 pm at 10:03 pm

    ይሄንን ግጥም ብዙ ሰው እንዳልገባው ሳይ አዘንኩ፡፡ ለነገሩ እንኳን ቅኔያዊው ይቅርና የትውልዱ በቋንቋው ራሱን ሐሳቡን የመግለጽ ችሎታ እጅግ ከመድከሙ የተነሣ የቋንቋው ጥራት አሽቆልቁሎ ተራ ንግግር እንኳን በአግባቡ መግለጽ የምንቸገር ትውልድ እየሆንን ከመሆኑ የተነሣ ቅኔ ለምን አልገባህም ብሎ ማለት ምጸት ነው የሚሆነው፡፡

    ይሄውላቹህ እርሳሱ የሚወክለው ሐሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብቶቹን አጥቶ ተረግጦ የሚኖረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይወክላል፡፡ ላጲሱ ደግኖ ገደብ የለሽ ሥልጣን ይዘው የሚረግጡትን ግፈኛ ገዥዎቹን ይወክላል፡፡ እስክሪፕቶና ብዕሩ ደግሞ በነጻነት ሐሳቡን የመግለጽ መብት ያለውን የምዕራቡን ዓለም ሕዝብ ይወክላል፡፡ አሁንስ?

    Reply
    • ሳባ says

      November 7, 2014 01:32 pm at 1:32 pm

      አመሰግናለሁ አምሳለው ግን አኔ ገና ሳነበው ቅኔ መሆኑ ገብቶኝ ነበር. ልንገርህ አኔ ethiopia ውስጥ አደለም ያደኩት ግን የላፕሱና የርሳሱ ቅኔ ስለገባኝና አንተ ደግሞ sure ስላደርክልኝ አመሰግናለሁ.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule