• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እርሳስና ላጲስ

October 21, 2014 05:51 am by Editor 3 Comments

እርሳስ በጓደኛው፤ በብዕር እስክሪፕቶ

ባለው ገደብ የለሽ፤ ነጻነቱ ቀንቶ

እንዳሻው ቢናገር፤ የልቡን አውጥቶ

እንዲህ አልክ ብሎ፤ ያለውን አጥፍቶ

የሚያስወግድበት፤ በላጲስ አንሥቶ

ስለማይከላ፤ ሲናገር አፍ ከፍቶ ፡፡

እሱ ግን ዘለዓለም፤ በላጲሱ ጠፍቶ

መኖሩ አስመርሮት፤ በእጅጉ ተከፍቶ

እኔስ ለምን እንዴት? ማለት ጀመረና

ጠየቀ አፋጠጠ፤ ተሰማው ፍነና

ነጻነቱን ሊያውጅ፤ ተነሣ ይሄ ጀግና

ከእንግዲህ በኋላ፤ አለ ቆፍጠን ብሎ

የነበረውን ፍርሐት፤ ከልቡላይ ነቅሎ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ አለ አንሥቶ ክንዱን

ባናቴ ያለው ላጲስ፤ ገደብ የለሽ ሥልጣን

አብቅቷል ብያለሁ፤ ይሰማ አዋጀ

የሚጸና ይሆናል፤ በትውልድ ልጅ ልጀ

ከዚህች ቀን በኋላ፤ ማንም ያላወቀ

በእውቀት ያለበቃ፤ ከንቱ ያልጠነቀቀ

ዐሥሬ እየጻፈ፤ እየለቀለቀ

ዐሥሬ የሚያጠፋ፤ መሀይም የወደቀ

ውሸት የሚደጋግም፤ በላጲስ እየፋቀ

በእጁ አይይዘኝም፤ አለቀ ደቀቀ

ከቶም አይገዛኝም፤ ብሎ አስታወቀ ፡፡

ከእንግዲህ ወዲህ፤ መብቴን ተገፍፌ

አልኖርም ብያለሁ፤ እያለ መዳፌ

እኔም እንደ ብዕር፤ ያሻኝን ብል ጽፌ

ወይም ተናግሬ፤ በዓለም ሕግ ታቅፌ

ያ የተናገርኩት፤ የጻፍኩት ቃል ርኡስ

ይቀመጣል እንጅ፤ እዛው ሳይደመሰስ

ማንም አይፍቀውም፤ እያነሣ ላጲስ

ይሄው አውጃለሁ፤ ይሁን እንደ ቃል ቅዱስ፡፡

ከእንግዲህ በኋላ፤ በዚህ አዋጅ ሥሩ

ስሕተት እንኳን ቢሆን፤ የጻፍኩት ቃል ዘሩ

ይቀመጣል እንጂ፤ ልክ እንደ ብዕሩ

ሠረዝ ተደርጎበት፤ ሳይጠፋ ነገሩ

ለታሪክ ለትምህርት፤ ጠቀምጦ በክብሩ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ የማንም ምን ውላጅ

ከቶም አይፍቀኝም፤ እኔን በላጲስ ፈንጅ፡፡

መስከረም 2007ዓ.ም.

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    October 21, 2014 10:05 am at 10:05 am

    **************************
    አርሳስ…
    እርሳስ በእስክሪብቶ ሁልግዜ ተዛብቶ
    እኔ እየጠፋሁኝ አንተ አትጠፋ ከቶ?
    እስክሪብቶ…
    አንተማ ሞኝ ነህ አጥፊህን በራስህ ተሸክመህ
    ለእግር ሸንካይ በመቅረጫ ተሸራርፈህ
    እኔማ ቀለሜ ላይፈስ ታፍኜ ከላይም ከታችም
    የሚፃፍ ሞልቶ አንድም ዘጋቢና ፀሐፊ አልተገኘም።
    ላጲስ…
    እኔ የሰማሁት የዓሳ ሽታ ከራስ ነው
    የእርሳስ ላይ ጭንቅላትን አጥፊ ማነው ያለው
    እርሳስማ አጠፋኝ ሲል ስሜን አጠፋው
    እስኪሪብቶ ተሳለቀብኝ እንደማላጠፋው
    የተፃፈን ቀበኛ የሚፅፍን የሚያጠፋው ማነው!?
    በለው!

    Reply
  2. Amsalu Gebrekidan says

    October 23, 2014 10:03 pm at 10:03 pm

    ይሄንን ግጥም ብዙ ሰው እንዳልገባው ሳይ አዘንኩ፡፡ ለነገሩ እንኳን ቅኔያዊው ይቅርና የትውልዱ በቋንቋው ራሱን ሐሳቡን የመግለጽ ችሎታ እጅግ ከመድከሙ የተነሣ የቋንቋው ጥራት አሽቆልቁሎ ተራ ንግግር እንኳን በአግባቡ መግለጽ የምንቸገር ትውልድ እየሆንን ከመሆኑ የተነሣ ቅኔ ለምን አልገባህም ብሎ ማለት ምጸት ነው የሚሆነው፡፡

    ይሄውላቹህ እርሳሱ የሚወክለው ሐሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብቶቹን አጥቶ ተረግጦ የሚኖረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይወክላል፡፡ ላጲሱ ደግኖ ገደብ የለሽ ሥልጣን ይዘው የሚረግጡትን ግፈኛ ገዥዎቹን ይወክላል፡፡ እስክሪፕቶና ብዕሩ ደግሞ በነጻነት ሐሳቡን የመግለጽ መብት ያለውን የምዕራቡን ዓለም ሕዝብ ይወክላል፡፡ አሁንስ?

    Reply
    • ሳባ says

      November 7, 2014 01:32 pm at 1:32 pm

      አመሰግናለሁ አምሳለው ግን አኔ ገና ሳነበው ቅኔ መሆኑ ገብቶኝ ነበር. ልንገርህ አኔ ethiopia ውስጥ አደለም ያደኩት ግን የላፕሱና የርሳሱ ቅኔ ስለገባኝና አንተ ደግሞ sure ስላደርክልኝ አመሰግናለሁ.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule