• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እርሳስና ላጲስ

October 21, 2014 05:51 am by Editor 4 Comments

እርሳስ በጓደኛው፤ በብዕር እስክሪፕቶ

ባለው ገደብ የለሽ፤ ነጻነቱ ቀንቶ

እንዳሻው ቢናገር፤ የልቡን አውጥቶ

እንዲህ አልክ ብሎ፤ ያለውን አጥፍቶ

የሚያስወግድበት፤ በላጲስ አንሥቶ

ስለማይከላ፤ ሲናገር አፍ ከፍቶ ፡፡

እሱ ግን ዘለዓለም፤ በላጲሱ ጠፍቶ

መኖሩ አስመርሮት፤ በእጅጉ ተከፍቶ

እኔስ ለምን እንዴት? ማለት ጀመረና

ጠየቀ አፋጠጠ፤ ተሰማው ፍነና

ነጻነቱን ሊያውጅ፤ ተነሣ ይሄ ጀግና

ከእንግዲህ በኋላ፤ አለ ቆፍጠን ብሎ

የነበረውን ፍርሐት፤ ከልቡላይ ነቅሎ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ አለ አንሥቶ ክንዱን

ባናቴ ያለው ላጲስ፤ ገደብ የለሽ ሥልጣን

አብቅቷል ብያለሁ፤ ይሰማ አዋጀ

የሚጸና ይሆናል፤ በትውልድ ልጅ ልጀ

ከዚህች ቀን በኋላ፤ ማንም ያላወቀ

በእውቀት ያለበቃ፤ ከንቱ ያልጠነቀቀ

ዐሥሬ እየጻፈ፤ እየለቀለቀ

ዐሥሬ የሚያጠፋ፤ መሀይም የወደቀ

ውሸት የሚደጋግም፤ በላጲስ እየፋቀ

በእጁ አይይዘኝም፤ አለቀ ደቀቀ

ከቶም አይገዛኝም፤ ብሎ አስታወቀ ፡፡

ከእንግዲህ ወዲህ፤ መብቴን ተገፍፌ

አልኖርም ብያለሁ፤ እያለ መዳፌ

እኔም እንደ ብዕር፤ ያሻኝን ብል ጽፌ

ወይም ተናግሬ፤ በዓለም ሕግ ታቅፌ

ያ የተናገርኩት፤ የጻፍኩት ቃል ርኡስ

ይቀመጣል እንጅ፤ እዛው ሳይደመሰስ

ማንም አይፍቀውም፤ እያነሣ ላጲስ

ይሄው አውጃለሁ፤ ይሁን እንደ ቃል ቅዱስ፡፡

ከእንግዲህ በኋላ፤ በዚህ አዋጅ ሥሩ

ስሕተት እንኳን ቢሆን፤ የጻፍኩት ቃል ዘሩ

ይቀመጣል እንጂ፤ ልክ እንደ ብዕሩ

ሠረዝ ተደርጎበት፤ ሳይጠፋ ነገሩ

ለታሪክ ለትምህርት፤ ጠቀምጦ በክብሩ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ የማንም ምን ውላጅ

ከቶም አይፍቀኝም፤ እኔን በላጲስ ፈንጅ፡፡

መስከረም 2007ዓ.ም.

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    October 21, 2014 10:05 am at 10:05 am

    **************************
    አርሳስ…
    እርሳስ በእስክሪብቶ ሁልግዜ ተዛብቶ
    እኔ እየጠፋሁኝ አንተ አትጠፋ ከቶ?
    እስክሪብቶ…
    አንተማ ሞኝ ነህ አጥፊህን በራስህ ተሸክመህ
    ለእግር ሸንካይ በመቅረጫ ተሸራርፈህ
    እኔማ ቀለሜ ላይፈስ ታፍኜ ከላይም ከታችም
    የሚፃፍ ሞልቶ አንድም ዘጋቢና ፀሐፊ አልተገኘም።
    ላጲስ…
    እኔ የሰማሁት የዓሳ ሽታ ከራስ ነው
    የእርሳስ ላይ ጭንቅላትን አጥፊ ማነው ያለው
    እርሳስማ አጠፋኝ ሲል ስሜን አጠፋው
    እስኪሪብቶ ተሳለቀብኝ እንደማላጠፋው
    የተፃፈን ቀበኛ የሚፅፍን የሚያጠፋው ማነው!?
    በለው!

    Reply
  2. Amsalu Gebrekidan says

    October 23, 2014 10:03 pm at 10:03 pm

    ይሄንን ግጥም ብዙ ሰው እንዳልገባው ሳይ አዘንኩ፡፡ ለነገሩ እንኳን ቅኔያዊው ይቅርና የትውልዱ በቋንቋው ራሱን ሐሳቡን የመግለጽ ችሎታ እጅግ ከመድከሙ የተነሣ የቋንቋው ጥራት አሽቆልቁሎ ተራ ንግግር እንኳን በአግባቡ መግለጽ የምንቸገር ትውልድ እየሆንን ከመሆኑ የተነሣ ቅኔ ለምን አልገባህም ብሎ ማለት ምጸት ነው የሚሆነው፡፡

    ይሄውላቹህ እርሳሱ የሚወክለው ሐሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብቶቹን አጥቶ ተረግጦ የሚኖረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይወክላል፡፡ ላጲሱ ደግኖ ገደብ የለሽ ሥልጣን ይዘው የሚረግጡትን ግፈኛ ገዥዎቹን ይወክላል፡፡ እስክሪፕቶና ብዕሩ ደግሞ በነጻነት ሐሳቡን የመግለጽ መብት ያለውን የምዕራቡን ዓለም ሕዝብ ይወክላል፡፡ አሁንስ?

    Reply
    • ሳባ says

      November 7, 2014 01:32 pm at 1:32 pm

      አመሰግናለሁ አምሳለው ግን አኔ ገና ሳነበው ቅኔ መሆኑ ገብቶኝ ነበር. ልንገርህ አኔ ethiopia ውስጥ አደለም ያደኩት ግን የላፕሱና የርሳሱ ቅኔ ስለገባኝና አንተ ደግሞ sure ስላደርክልኝ አመሰግናለሁ.

      Reply
  3. Alex says

    September 20, 2025 12:55 am at 12:55 am

    ግጥምህ የራሱ የተለየ ጥላቻ እና አስተሳሰብ ይዞታ አለው። የተጠቀሰው የ“እርሳስ፣ እስክሪብቶ እና ላጲስ” ምሳሌ በሰው ሕይወት ውስጥ የትርጉም ትዕይንት ነው። እኔ እንደ ግለጽ እንዲህ እቀርብልሃለሁ: so እኔ ለአንተ በግልጽ ቅርጽ እንዲታይ ትንሽ በርዕስና ንዑስ ተከፋፍሎ እመልስልሃለሁ፦

    እርሳስ
    በእስክሪብቶ ሁልጊዜ ተዛብቶ
    እኔ እየጠፋሁኝ አንተ አትጠፋ ከቶ?” ይላል።

    እስክሪብቶ (በእውቀት)
    አንተ ሞኝ ነህ፣
    አጥፊህን በራስህ ተሸክመህ፤
    ለእግር ሸንካይ በመቅረጫ ተሸራርፈህ።
    እኔ ቀለመ ላይፈስ ታፍኜ
    ከላይም ከታችም የሚፃፍ ሞልቶ
    አንድም ዘጋቢና ፀሐፊ አልተገኘም።

    ላጲስ
    እኔ የሰማሁት የዓሳ ሽታ ከራስ ነው፤
    የእርሳስ ላይ ጭንቅላትን አጥፊ ማነው ያለው?
    እርሳስ አጠፋኝ ሲል ስሜን አጠፋው፤
    እስክሪብቶ ተሳለቀብኝ እንደማላጠፋው።

    እንዲሁ በማድረግ እያንዳንዱ ተናጋሪ የራሱን ድምፅ ያሳያል፤ እርሳስ ከጠፉ ጋር ተጋጭቶ ይናገራል፣ እስክሪብቶ እውቀት እንደ መምህር ይመስላል፣ ላጲስ ደግሞ የጭቅጭቅ ቅሬታ ይዞ እንደ አይነት ምስክር ይቀርባል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule