• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እርሳስና ላጲስ

October 21, 2014 05:51 am by Editor 4 Comments

እርሳስ በጓደኛው፤ በብዕር እስክሪፕቶ

ባለው ገደብ የለሽ፤ ነጻነቱ ቀንቶ

እንዳሻው ቢናገር፤ የልቡን አውጥቶ

እንዲህ አልክ ብሎ፤ ያለውን አጥፍቶ

የሚያስወግድበት፤ በላጲስ አንሥቶ

ስለማይከላ፤ ሲናገር አፍ ከፍቶ ፡፡

እሱ ግን ዘለዓለም፤ በላጲሱ ጠፍቶ

መኖሩ አስመርሮት፤ በእጅጉ ተከፍቶ

እኔስ ለምን እንዴት? ማለት ጀመረና

ጠየቀ አፋጠጠ፤ ተሰማው ፍነና

ነጻነቱን ሊያውጅ፤ ተነሣ ይሄ ጀግና

ከእንግዲህ በኋላ፤ አለ ቆፍጠን ብሎ

የነበረውን ፍርሐት፤ ከልቡላይ ነቅሎ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ አለ አንሥቶ ክንዱን

ባናቴ ያለው ላጲስ፤ ገደብ የለሽ ሥልጣን

አብቅቷል ብያለሁ፤ ይሰማ አዋጀ

የሚጸና ይሆናል፤ በትውልድ ልጅ ልጀ

ከዚህች ቀን በኋላ፤ ማንም ያላወቀ

በእውቀት ያለበቃ፤ ከንቱ ያልጠነቀቀ

ዐሥሬ እየጻፈ፤ እየለቀለቀ

ዐሥሬ የሚያጠፋ፤ መሀይም የወደቀ

ውሸት የሚደጋግም፤ በላጲስ እየፋቀ

በእጁ አይይዘኝም፤ አለቀ ደቀቀ

ከቶም አይገዛኝም፤ ብሎ አስታወቀ ፡፡

ከእንግዲህ ወዲህ፤ መብቴን ተገፍፌ

አልኖርም ብያለሁ፤ እያለ መዳፌ

እኔም እንደ ብዕር፤ ያሻኝን ብል ጽፌ

ወይም ተናግሬ፤ በዓለም ሕግ ታቅፌ

ያ የተናገርኩት፤ የጻፍኩት ቃል ርኡስ

ይቀመጣል እንጅ፤ እዛው ሳይደመሰስ

ማንም አይፍቀውም፤ እያነሣ ላጲስ

ይሄው አውጃለሁ፤ ይሁን እንደ ቃል ቅዱስ፡፡

ከእንግዲህ በኋላ፤ በዚህ አዋጅ ሥሩ

ስሕተት እንኳን ቢሆን፤ የጻፍኩት ቃል ዘሩ

ይቀመጣል እንጂ፤ ልክ እንደ ብዕሩ

ሠረዝ ተደርጎበት፤ ሳይጠፋ ነገሩ

ለታሪክ ለትምህርት፤ ጠቀምጦ በክብሩ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ የማንም ምን ውላጅ

ከቶም አይፍቀኝም፤ እኔን በላጲስ ፈንጅ፡፡

መስከረም 2007ዓ.ም.

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    October 21, 2014 10:05 am at 10:05 am

    **************************
    አርሳስ…
    እርሳስ በእስክሪብቶ ሁልግዜ ተዛብቶ
    እኔ እየጠፋሁኝ አንተ አትጠፋ ከቶ?
    እስክሪብቶ…
    አንተማ ሞኝ ነህ አጥፊህን በራስህ ተሸክመህ
    ለእግር ሸንካይ በመቅረጫ ተሸራርፈህ
    እኔማ ቀለሜ ላይፈስ ታፍኜ ከላይም ከታችም
    የሚፃፍ ሞልቶ አንድም ዘጋቢና ፀሐፊ አልተገኘም።
    ላጲስ…
    እኔ የሰማሁት የዓሳ ሽታ ከራስ ነው
    የእርሳስ ላይ ጭንቅላትን አጥፊ ማነው ያለው
    እርሳስማ አጠፋኝ ሲል ስሜን አጠፋው
    እስኪሪብቶ ተሳለቀብኝ እንደማላጠፋው
    የተፃፈን ቀበኛ የሚፅፍን የሚያጠፋው ማነው!?
    በለው!

    Reply
  2. Amsalu Gebrekidan says

    October 23, 2014 10:03 pm at 10:03 pm

    ይሄንን ግጥም ብዙ ሰው እንዳልገባው ሳይ አዘንኩ፡፡ ለነገሩ እንኳን ቅኔያዊው ይቅርና የትውልዱ በቋንቋው ራሱን ሐሳቡን የመግለጽ ችሎታ እጅግ ከመድከሙ የተነሣ የቋንቋው ጥራት አሽቆልቁሎ ተራ ንግግር እንኳን በአግባቡ መግለጽ የምንቸገር ትውልድ እየሆንን ከመሆኑ የተነሣ ቅኔ ለምን አልገባህም ብሎ ማለት ምጸት ነው የሚሆነው፡፡

    ይሄውላቹህ እርሳሱ የሚወክለው ሐሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብቶቹን አጥቶ ተረግጦ የሚኖረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይወክላል፡፡ ላጲሱ ደግኖ ገደብ የለሽ ሥልጣን ይዘው የሚረግጡትን ግፈኛ ገዥዎቹን ይወክላል፡፡ እስክሪፕቶና ብዕሩ ደግሞ በነጻነት ሐሳቡን የመግለጽ መብት ያለውን የምዕራቡን ዓለም ሕዝብ ይወክላል፡፡ አሁንስ?

    Reply
    • ሳባ says

      November 7, 2014 01:32 pm at 1:32 pm

      አመሰግናለሁ አምሳለው ግን አኔ ገና ሳነበው ቅኔ መሆኑ ገብቶኝ ነበር. ልንገርህ አኔ ethiopia ውስጥ አደለም ያደኩት ግን የላፕሱና የርሳሱ ቅኔ ስለገባኝና አንተ ደግሞ sure ስላደርክልኝ አመሰግናለሁ.

      Reply
  3. Alex says

    September 20, 2025 12:55 am at 12:55 am

    ግጥምህ የራሱ የተለየ ጥላቻ እና አስተሳሰብ ይዞታ አለው። የተጠቀሰው የ“እርሳስ፣ እስክሪብቶ እና ላጲስ” ምሳሌ በሰው ሕይወት ውስጥ የትርጉም ትዕይንት ነው። እኔ እንደ ግለጽ እንዲህ እቀርብልሃለሁ: so እኔ ለአንተ በግልጽ ቅርጽ እንዲታይ ትንሽ በርዕስና ንዑስ ተከፋፍሎ እመልስልሃለሁ፦

    እርሳስ
    በእስክሪብቶ ሁልጊዜ ተዛብቶ
    እኔ እየጠፋሁኝ አንተ አትጠፋ ከቶ?” ይላል።

    እስክሪብቶ (በእውቀት)
    አንተ ሞኝ ነህ፣
    አጥፊህን በራስህ ተሸክመህ፤
    ለእግር ሸንካይ በመቅረጫ ተሸራርፈህ።
    እኔ ቀለመ ላይፈስ ታፍኜ
    ከላይም ከታችም የሚፃፍ ሞልቶ
    አንድም ዘጋቢና ፀሐፊ አልተገኘም።

    ላጲስ
    እኔ የሰማሁት የዓሳ ሽታ ከራስ ነው፤
    የእርሳስ ላይ ጭንቅላትን አጥፊ ማነው ያለው?
    እርሳስ አጠፋኝ ሲል ስሜን አጠፋው፤
    እስክሪብቶ ተሳለቀብኝ እንደማላጠፋው።

    እንዲሁ በማድረግ እያንዳንዱ ተናጋሪ የራሱን ድምፅ ያሳያል፤ እርሳስ ከጠፉ ጋር ተጋጭቶ ይናገራል፣ እስክሪብቶ እውቀት እንደ መምህር ይመስላል፣ ላጲስ ደግሞ የጭቅጭቅ ቅሬታ ይዞ እንደ አይነት ምስክር ይቀርባል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule