ከአንድ መቶ ሺ በላይ ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለውና እጅግ ደም አፋሳሽ በሆነው የሶሪያ የእርስበርስ ጦርነት የአማጺያኑ ኃይል ከሚጠቀመው ቤት ሰራሽ መሣሪያዎች ሌላ የቴክኖሎጂ እሴቶችን በመቀላቀል የሚጠቀሙ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የሬውተር ዘጋቢ የሆነው መሐመድ አብደላ ባነሳው በዚህ ፎቶ ላይ እንደሚታየው የነጻ ሶሪያ ሠራዊት አማጺያን ከደማስቆ ወጣ ብሎ በሚገኝ ቦታ ላይ አዳፍኔ ለመተኮስ በ iPad ሲታገዙ ይታያል፡፡ የጦር መሣሪያ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ አማጺያኑ በፎቶግራፉ ላይ እንደሚታየው በቴክኖሎጂ ቢታገዙም የመተኮሻው ቱቦ አቅጣጫና አቀማመጥ በጣም በቅርብ በሚገኝ ዒላማ ለመምታት አስበው ካልሆነ በስተቀር አዳፍኔውን የሚተኩሱት ራሳቸውን ለማጥፋት ይመስላል፡፡ በምስሉ እንደሚታየው አማጺያኑ በጉዳዩ የረቀቁበት ቢመስልም አነጣጠራቸውና አተኳኮሳቸው “ቦምብ ጥሎ የመጸለይ” ዓይነት … [Read more...] about አዳፍኔ ለመተኮስ የ “iPad” ዕገዛ
Archives for September 2013
የኤርትራ ጉዳይ በሶስት ትውልዶች ውስጥ
የኤርትራው ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ እንደቀልድ እና እንደ እልህ የጀመሩት ''ኤርትራ ኢትዮጵያዊ አይደለችም'' ብሎም ''የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው'' አጀንዳን የሻብያ አጀንዳ እንዲሆን ካስደረጉ በኃላ ከእሳቸው በፊት የነበረው ትውልድ ባይቀበላቸውም የእሳቸውን ትውልድ ''የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው'' የሚለውን ገለፃ ለመንገር አላንገራገሩም። አቶ ኢሳያስ በአንድ ጎናቸው ተንቤን ትግራይ ቢወለዱም ያነሷት ጉዳይ ግን ኢትዮጵያን ለማዳከም ለዘመናት ከሚያልሙ አንዳንድ የአረብ ሀገራትም ሆነ ጎረቤት ሱዳንን የሚያማልል ብሎም ዳጎስ ያለ ድጎማ የሚያስገኝ የወቅቱ አዋጪ ''የገበያ ማስታወቅያ'' መሆኑን የተረዱት ይመስላሉ። ቀዳማዊ አፄ ሃይለስላሴ ዩንቨርስቲ በነፃ ትምህርት ዕድል ይማሩ የነበሩት አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ ''የኤርትራ ነፃነት ግንባር'' (ELF) … [Read more...] about የኤርትራ ጉዳይ በሶስት ትውልዶች ውስጥ
መስከረም ሲጠባ አደይ ሲፈነዳ …
የዘመን መለወጫ ክብረ በዓል በየትኛውም አገር እንደ አገሩ ወግና ልማድ በድቅመት የሚከበር በዓል ነው፤ በእኛ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ደግሞ ልማድና ወጋቻን እጅግ ከመጠንከሩ የተነሳ ለአዲስ ዓመት ወይም ለዘመን መለወጫ ክብረ በዓል ዝግጅታችንም ሆነ አከባበራችን እጅግ በጣም ጠንካራና ደስ የሚል ነው፡፡ አዲስ ዓመት የሁሉ ነገር መጀመሪያ ነው ለዚህም ነው ብዙ እቅዶቻችን ከመስከረም ወር የሚጀምረው፤ ያቀድነው ነገር በዓመቱ መጨረሻ ሊሳካ ወይም ላይሳካ ይችል ይሆናል ቁም ነገሩ ግን በዓመቱ መጀመሪያ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ለማሳካት የታሰበ እቅድ መኖሩ ነው፤ ለእቅዱ አለመሳካት ውጫዊና ውስጣዊ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ እነዚህን እንቃፋት የሆኑ ምክንያቶች ለይቶ ማወቅ በራሱ የእቀዱ አንድ አካል በማደረግ እንደገና ለመጪው አዲስ ዓመት ለተሻለ እቅድ ግባት ይሆናል፡፡ የዘንድሮ አዲስ ዓመት … [Read more...] about መስከረም ሲጠባ አደይ ሲፈነዳ …
Anuak Justice Council (AJC)
Reports Emerge of TPLF/ERPDF Efforts to Suppress Testimony in World Bank’s Investigation Regarding the Misuse of WB Funds in the Forced Displacement of Anuak and Related Land Grabs in Ethiopia’s Gambella Region Press Release (Vancouver, BC, Canada)— The Anuak Justice Council (AJC) has received disturbing reports from on-the-ground sources in refugee camps in the Republic of South Sudan and Kenya as well as from sources in Gambella, Ethiopia that the TPLF/EPRDF Government of Ethiopia is … [Read more...] about Anuak Justice Council (AJC)
“የበሰበሱት” ህወሃት እና ሻዕቢያ
አምባገነነኖች ከሚታወቁበት አንዱና ዋንኛ መለያቸው መካከል ሁለተኛ ሰው አለማዘጋጀታቸው ነው። አቶ መለስ በድንገት ሲስፈነጠሩ በውል የታየው አስከሬን ደብቆ ድብብቆሽም የዚሁ ውጤት ነው። ኢሳያስ ከስልጣን ቢወገዱ ማን ይተካቸዋል? የሚለው ችግርም ጎልቶ የሚታየው ከዚሁ የአምባገነኖች በሽታ አንጻር ነው። ግጭትና ችግር ከመፈጠሩ በፊት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ደወል የሚያንጫርረው ዓለምአቀፉ የግጭት ቡድን (International Crisis Group) ፍርሃቻም ከዚሁ የመነጨ ይመስላል። በኤርትራ ህዝቡ በቃኝ ወደ ማለቱ ደረጃ መቃረቡን የሚጠቁመው የዘንድሮው ዓመት ሪፖርት ኤርትራ በቅርቡ መንግስት አልባ የመሆን እድሏ ሰፊ እንደሆነ ያወሳል። በቅርቡ "የሚከሽፉ መንግስታት" በሚል ስማቸው ከተዘረዘሩት ውስጥ አገሮች መካከል ኢትዮጵያም ተመልክታለች። እኩል ወደ ስልጣን የመጡት ሻዕቢያና ወያኔ … [Read more...] about “የበሰበሱት” ህወሃት እና ሻዕቢያ
ሰንደቅዓላማችን (ትእምርተ-ኪዳናችን) ከየት መጣ ማንስ አጠፋው?
ስለ ሰንደቅ ዓላማ ትርጉም ስናወራ ሰንድቅ ዓላማ ማለት በዘንግ ወይም በመስቀያ ያለ ሰንደቅ ማለት ነው፡፡ መስቀያው ዓላማ ሲባል የሀገር ዓርማ የሆነው ባለቀለሙ መለያ ምልክት ደግሞ ሰንደቅ ይባላል፡፡ የሚለው አንዱ ሲሆን ሌላኛው ትርጉሙ ደግሞ ሰንደቅ ዓላማ የሚባለው ባለቀለሙ የመለያ ምልክት ብቻ እንጅ መስቀያውን አይጨምርም ሰንደቅ ዓላማ መባሉም ሰንደቁ የራሱ የሆነ ዓላማ እንዳለው ለማመልከት ነው የሚሉም አሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የመንግሥት ሰንደቅ ከመሆኑ በፊት ከኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ንዋዬ ቅድሳት አንዱና እንዲያውም የመጀመሪያው የቤተክርስቲያን ሰንደቅ ነበር፡፡ በቤተክርስቲያን እነዚያ ሦስት ቀለማት አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ወይም ቀይ ቢጫ አረንጓዴው ቀለማት በንዋዬ ቅድሳቶቿ ሁሉ ላይ ከብራና መጻሕፍቶቹ እስከ መንበረ ታቦታተሕጉ ድረስ ይገኛል፡፡ ከጥንታዊ የብራና መጻሕፍት … [Read more...] about ሰንደቅዓላማችን (ትእምርተ-ኪዳናችን) ከየት መጣ ማንስ አጠፋው?
ስምና ገመድ!!
በተለያዩ ምክንያቶች ለረጅም ጊዜ አቋርጠነው የነበረውን የግጥም ጨዋታ እንደገና ጀምረናል፡፡ ከዚህ በፊት እናደርገው እንደነበረው አንባቢያን ይህንን ግጥም አንብባችሁ አስተያየታችሁን በግጥም እንድትሰጡና ጨዋታውን እንድታደምቁት እንጋብዛለን፡፡ ለዛሬ የመረጥነውን ግጥም ከነፎቶግራፉ ያገኘነው ከደመቀ ከበደ የፌስቡክ ገጽ ላይ ነው፡፡ገጣሚ ደመቀ ከበደን ለግጥሙና ለፎቶው ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ ስምና ገመድ!! አዝማሪ እንዲህ አለ፤ "ሰው ሰበበኛ ነው - ምክንያት አያጣም እንኳን ዝናብ ዘንቦ - ሲዳምን አይወጣም፤" እኔ ግን እላለሁ፤ አተተ በተተ ወዘተ ወዘተ በሚል አርቲ ቡርቲ - ዕድሜ ከምንጨርስ ህይወት ከምናጣ ፋይዳ ላለው ነገር - ቁልቁለት እንውረድ አቀበት እንውጣ፤ ያኔ አላስወርድ ካለህ - ወይም አላስወጣ ማሰሪያ ከሆነህ - አሊያም ጋሬጣ ያኔ አይንህን … [Read more...] about ስምና ገመድ!!
በአዲስ አመትም ያላባራው ስቆቃ
በግልም ቢሆን አዲሱን አመት በሰላም እና በደስታ መቀበሌ እውነት ነው! መስከረም ጠብቶ ብዙ ቀናት ሳንቆጥር ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚደርሰኝ የስደተኛ ወገን መከራ ግን ከአዲሱ አመት ዋዜማ ጀምሮ እስከ መባቻው አላባራም … አያንዳንዱን የወገን ስደት ሰቆቃ መከራ ጨክኘ ከመናገር ለመቆጥብ ያደረግኩት ትግል ላንዲት ቀን ቢሳካም ህሊናየ ግን እረፍት አላገኘም! በተለይ በአዲሱ አመት ዋዜማ "ብሪማን" ተብሎ በሚጠራው የጅዳው ትልቅ ማረሚያ ቤት የደረሰኝ መረጃ ያማል … ያሳለፍነው ሮመዳን ወር እንደገባ ጅዳ ውስጥ የትዳር ጓደኛውን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ በአሳር በመከራ ከተያዘ በኋላ ዘብጥያ የወረደው አዕምሮውን የሳተ ኢትዮጵያዊ ከጤነኛ ታሳሪ ሃበሾች ጋር ነብሰ ገዳይ ከተራ ወንጀለኛ ጋር ደባልቀው በማሰራቸው ደም እንዲፈስ ምክንያት ሆኗል በማለት ታሳሪዎች እያነቡ ገልጸውልኛል። ይህ ነፍሰ ገዳይ … [Read more...] about በአዲስ አመትም ያላባራው ስቆቃ
Ethiopians calling for Protest
The Unity for Democracy and Justice Party (UDJ), the most important opposition political party working under the narrowest political landscape in Ethiopia, in collaboration with other 33 opposition political parties is calling for massive anti government protest, urging people to take to the street of the capital Addis Ababa on 15 September 2013. The demonstration is the part of the campaign, “Millions of Voices for Freedom”, which has begun almost 3 months ago. Following the call, many are … [Read more...] about Ethiopians calling for Protest
የ፩ኛ ዓመት መልዕክት – የሚዲያ ተሃድሶ ግድ ነው!!
ዛሬ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከተቋቋመ አንድ ዓመቱ ነው። ባሳለፍነው አንድ ዓመት ውስጥ የደገፉን፣ ያበረታቱን፣ አስተያየት በመስጠት ያረቁንና በመድረካችን የተሳተፉ ያሉትን ያህል የምንሰራውን ስራ ለመቆጣጠር፣ የተመሰረትንበትን ግልጽ መስመር ለማስቀየር የሞከሩና ጨዋነት በጎደለው መልኩ የተዛለፉም አጋጥመውናል። ለሁላችም እንኳን ለአንደኛው ዓመት አደረሰን!! “ወፌ ቆመች በሉን" በማለት ከዓመት በፊት የሚዲያውን ሰፈር በአሃዱ ብለን ከተቀላቀልንበት ጊዜ አንስቶ የሰራነውን ስራ በጥሞና ለመመልከት ሞክረናል። ሌሎች ሚዲያዎችንና ብሎጎችንም ዳሰናል። የራሳችን ደካማ ጎን ስንፈትሽ እግረ መንገዳችንን ዙሪያችንን ስንቃኝ የሚዲያ ተሃድሶ (ሪፎርም) አስፈላጊ እንደሆነ ተረድተናል። አምነናል። "መቼ" ለሚለው ጥያቄ ምላሹ ዛሬ፣ አሁን፣ አሁኑኑ የሚል ነው። ድክመታችን ስንጀምር በዘረጋናቸው … [Read more...] about የ፩ኛ ዓመት መልዕክት – የሚዲያ ተሃድሶ ግድ ነው!!