• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አመትም ያላባራው ስቆቃ

September 12, 2013 09:32 am by Editor Leave a Comment

በግልም ቢሆን አዲሱን አመት በሰላም እና በደስታ መቀበሌ እውነት ነው! መስከረም ጠብቶ ብዙ ቀናት ሳንቆጥር ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚደርሰኝ የስደተኛ ወገን መከራ ግን ከአዲሱ አመት ዋዜማ ጀምሮ እስከ መባቻው አላባራም … አያንዳንዱን የወገን ስደት ሰቆቃ መከራ ጨክኘ ከመናገር ለመቆጥብ ያደረግኩት ትግል ላንዲት ቀን ቢሳካም ህሊናየ ግን እረፍት አላገኘም! በተለይ በአዲሱ አመት ዋዜማ “ብሪማን” ተብሎ በሚጠራው የጅዳው ትልቅ ማረሚያ ቤት የደረሰኝ መረጃ ያማል …

ያሳለፍነው ሮመዳን ወር እንደገባ ጅዳ ውስጥ የትዳር ጓደኛውን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ በአሳር በመከራ ከተያዘ በኋላ ዘብጥያ የወረደው አዕምሮውን የሳተ ኢትዮጵያዊ ከጤነኛ ታሳሪ ሃበሾች ጋር ነብሰ ገዳይ ከተራ ወንጀለኛ ጋር ደባልቀው በማሰራቸው ደም እንዲፈስ ምክንያት ሆኗል በማለት ታሳሪዎች እያነቡ ገልጸውልኛል። ይህ ነፍሰ ገዳይ ከአንድ ፍርዱን ጨርሶ በተወካይ ጉትጎታ እጦት ከእምስት ወራት በላይ  እስር ይንገላታ የነበረን በእስር ቤቱ ተደብቆ ሲጋራ የሚሸጥን ወጣት ኢትዮጵያዊን ታሳሪ “አንዲት ሲጋራ ለምን አልሰጠህኝም” በሚል ቂም በብረት ዘንግ አይኑን አፍስሶ የመደብደቡ ወንጀል ሊናገሩት የሚከብድ አሰቃቂ እንደነበር “ተደብዳቢው ከሞት አይተርፍም” ያሉኝ እማኝ ታሳሪዎች በሃዘን ገልጸውልኛል … በአዲሱ አመት ዋዜማ!

በአዲስ አመት መባቻ  ዛሬ ምሽት … ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ እና ፍትህ!

ሀገር ቤት የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ የርሃብ አድማ መምታት ዜና ከአሜሪካ ራዲዮ የግማሽ ሌሊት የሳተላይት ስርጭት እያዳመጥኩ በወጣቷ ጋዜጠኛ የእስር እንግልት ዙሪያ እንደ ዜጋ የሚሰማኝን ለማለት በሃሳብ ላይ ነኝ፣ ከኮምፒውተሬ ጋር ተፋጥጨ በሃሳብ ከርዕዮት አለሙ አልፊ ከእስክንድር ከውብሸት እና ከአንዷለም የእስር ፈተና ርቄ ፍትህን ፍለጋ ሄጃለሁ … “አሸባሪዎች!” አልኩ ለራሴ ውስጤ እየተቆጣ! ግን ዝም አልኩ … ጭጭ  … ዝም! ምን ይባላል!

ወጣቷ ጉብል ትፈታ ግን እላለሁ!

ከምሳ የተረፈችንን ራት አድርገን ከባለቤቴ ጋር እየቀማመስኩም ርዕዮትን አስታውሸ  ፍትህን ፍለጋ በሃሳብ ነጉጃለሁ … ምሽት ላይ አብረውኝ ሲጫዎቱ ያመሹትን ሁለት ታዳጊ ግረምሳ ልጆችን  በአመት በአል ተጠራርተን በአሉን ያደመቁ ዘምድ ጓደኛ ጎረቤቶችን አንዳፍታ ከነርዕዮት ጋር አዛምጀ ሳያቸው አመመኝ! በአውደ አመት ከልጅ ወላጅ ወዳጅ ዘመድ ተራርቀው የከረሙ እና እንዲከርሙ የተፈረደባቸው ወንድም እህቶች ጉዳይ በእርግጥም ያሳስባል ያማል! የሰረቀ፣ የገደለ በምህረት በሚፈታበት ሃገር የህዝብን በሶት በተናገረ መቀመቅ መውረድ አግባብ አይደለም ማለቱ በዘመኑ ባያዋጣም፣ ይቅርታ ምህረት ጠይቆ መነፈግ ልብ የሚሰብረውን ያህ ስብራት አጣሁለት! የእነ ርዕዮትን ስቃይ፣ እስራት! የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ! ሰላማዊ እርቅ ይበጀናል እላለሁ!

መንገድ ላይ ተጥላ የተገኘችው የኮንትራት ሰራተኛ …

ብዙ ርቄ ስጓዝ ስልኬ አቃጭሎ ከነጎድኩበት ሃሳብ ተመለስኩ … ከአንድ ወዳጀ የደረሰኝ የስልክ ጥሪ አዲሱን አመት ዳግም በአሳዛኝ መረጃ ቅበላ እንድጀምር አስገደደኝ፡፡ (እየተኮላተፈ አማርኛ የሚናገር ወዳጁ መንገድ ላይ አንዲት አትዮጵያዊት በአሰሪዎቿ ተጥላ እንዳገኘና ሃበሻ የሚያውቅ እሱን በመሆኑ እንዲረዳት መረጃ አቀብሎት ይህችን እህት እንዴት መርዳት እንደሚቻል “የተሻለ መረጃ ካለህ” ብሎ ሊያማክረኝ መደወሉን አጫወተኝ!  እኔም ከሁሉ አስቀድሞ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎችን እንዲያነጋግር በመምከር አድራሻ ጭምር አቀበልኩት እና በጉዳዩ ዙሪያ አማክሬው ስልኩን ዘጋን …

ወዳጀ በደረቁ ሌሊት መልሶ ደውሎ የደረሰበትን መረጃ አቀበለኝ … ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ደውሎ ቆንስል ሙንትሃን በማግኘት ችግሩን አስረድቶ መፍትሔ ጠየቀ። ከዚያም ቆንስል ሙንትሃ ልጅቱን ወደ ቆንሰሉ መጠለያ በመውሰድ ለመጠለያው ሃላፊ ለወ/ሮ አዜብ እንዲያስረክባት መክረውት ወደ ጅዳ ቆንሰል መጠለያ መሄዱን ገለጸልኝ፣  በቆንስላው ሲደርስ የተባሉት የመጠለያ ሃላፊም ሆኑ የሚመለከታቸው በቦታው አለማግኘቱን ወዳጀ በአግራሞትና በብስጭት የሆነውን ሁሉ ገልጾልኛል! ለመጠለያውን እና ለኮሚኒቲውን ጠባቂዎች ጉዳዩን በማስረዳት ይህች መንገድ ላይ ተጥላ ያገኟት እህት የቀሩትን  ከ140 የዘለቁ ተፈናቃዮች ለመቀላቀል ይቻላት ዘንድ የቆንስል ሃላፊዋን መልዕክትና ቃል ቢገልጹም ከጠባቂዎች ጋር መግባባት አልተቻለም!

ይህች ምስኪን እህት ለሃገር ምድሩ ባዳ በሆነችበት ሰማይ ስር መንገድ እንደመጣሏ ወገኖቿ የደረሱላት መሆኑ ቢያስደስትም ወደ መጠለያው ለመግባት ፈቃድ አለማግኘቷ ያበሳጨው መረጃውን ያቀበለኝ ወንድም እልህ እና ቁጭት እየተናነቀው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ስልክ ደውሎ እንዲህ ነበር ያለኝ “አቶ ነቢዩ ዘበኞች አትገባም አሉን፣ ወደ ጅዳው ቆንስል ሃላፊ አቶ ዘነበ ደወልን ስልካቸው ዝግ ነው! መልሰን ለቆንስል ሙንትሃ ደወልን፣ ቅድም ውሰዷት እና ለወ/ሮ አዜብ አስረክቧት ያሉኝ እመቤት ደጋግምን ብንደውልም ስልካቸውን አያነሱም፣ ምን ማድረግ ይቻላል? ግን … ወገናችን ይህን መከራ ላለማየት እህታችን ሜዳ ላይ አይተን እዳላየን በጭካኔ ጥለን መሄድ ነበረብን? …”  ብሎ ጠየቀ!  ብዙ ተነጋግረን ስልኩ ተዘጋ … አንደምንም  በግል አስጠግቶ አሳድሮ ነገ የሚሆነውን ለማድረግ ተስማምተን ከተሰነባበትን በኋላ መልሸ አሁንም የደረሰበትን ሁኔታ ለመረዳት ስደውልለት መልካም የምስራች አበሰረኝ ፣ እንዲህ ሲል “አዎ ተሳካ! የቆንስል ሃላፊዎች ስልካቸውን ማንሳት ባይችሉና የምናደርገው ጠፍቶን ብንንገላታም በፍቃድ ማግኘት ያልቻሉትን ወደ መጠለያ የማስጠጋት ሙከራ ሰው በሰው (በዋስጣ) ይህች አንጀት የምትበላ እህት ወደ ቆንስሉ መጠለያ ልትገባ ችላለች!” ብሎኛል!

በየሜዳው እየተጣሉ ያሉ የኮንትራት ሰራተኛ እህቶቻችን ከችግር ብዛት እስከ ማበድ ራሳቸውን እስከ ማጥፋት እንዳደረሳቸው እያየን ነው!  ሰብዕናው ቢገደን ገጽታችን እንዳያጠፉት እህቶቻችን ወደ መጠለያ በመሰብሰቡ ረገድ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ዛሬም ድምጻችን ሰምተው ሳይሆን ግፉአኑን ከደጃቸው ተመልክተው አንድ ቢሉን መልካም ነው!

የአዲሱ አመት የማለዳ ወግ  በመራራው ሮሮ ጀመርኩት … በአዲስ አመትም ያላባራው ሰቆቃ እና ልናገረው የከበደኝ ሮሮ! አልኩት … ልተንፍሰው በሚል ከብዙ ጥቂቱን ነካክቸ … ምን ላድርግ  ! የአረብ ሃገር ስደት  ኑሯችን እንዲያ ሆኗል!

እሰኪ ቸር ያሰማን!

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule