• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አመትም ያላባራው ስቆቃ

September 12, 2013 09:32 am by Editor Leave a Comment

በግልም ቢሆን አዲሱን አመት በሰላም እና በደስታ መቀበሌ እውነት ነው! መስከረም ጠብቶ ብዙ ቀናት ሳንቆጥር ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚደርሰኝ የስደተኛ ወገን መከራ ግን ከአዲሱ አመት ዋዜማ ጀምሮ እስከ መባቻው አላባራም … አያንዳንዱን የወገን ስደት ሰቆቃ መከራ ጨክኘ ከመናገር ለመቆጥብ ያደረግኩት ትግል ላንዲት ቀን ቢሳካም ህሊናየ ግን እረፍት አላገኘም! በተለይ በአዲሱ አመት ዋዜማ “ብሪማን” ተብሎ በሚጠራው የጅዳው ትልቅ ማረሚያ ቤት የደረሰኝ መረጃ ያማል …

ያሳለፍነው ሮመዳን ወር እንደገባ ጅዳ ውስጥ የትዳር ጓደኛውን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ በአሳር በመከራ ከተያዘ በኋላ ዘብጥያ የወረደው አዕምሮውን የሳተ ኢትዮጵያዊ ከጤነኛ ታሳሪ ሃበሾች ጋር ነብሰ ገዳይ ከተራ ወንጀለኛ ጋር ደባልቀው በማሰራቸው ደም እንዲፈስ ምክንያት ሆኗል በማለት ታሳሪዎች እያነቡ ገልጸውልኛል። ይህ ነፍሰ ገዳይ ከአንድ ፍርዱን ጨርሶ በተወካይ ጉትጎታ እጦት ከእምስት ወራት በላይ  እስር ይንገላታ የነበረን በእስር ቤቱ ተደብቆ ሲጋራ የሚሸጥን ወጣት ኢትዮጵያዊን ታሳሪ “አንዲት ሲጋራ ለምን አልሰጠህኝም” በሚል ቂም በብረት ዘንግ አይኑን አፍስሶ የመደብደቡ ወንጀል ሊናገሩት የሚከብድ አሰቃቂ እንደነበር “ተደብዳቢው ከሞት አይተርፍም” ያሉኝ እማኝ ታሳሪዎች በሃዘን ገልጸውልኛል … በአዲሱ አመት ዋዜማ!

በአዲስ አመት መባቻ  ዛሬ ምሽት … ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ እና ፍትህ!

ሀገር ቤት የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ የርሃብ አድማ መምታት ዜና ከአሜሪካ ራዲዮ የግማሽ ሌሊት የሳተላይት ስርጭት እያዳመጥኩ በወጣቷ ጋዜጠኛ የእስር እንግልት ዙሪያ እንደ ዜጋ የሚሰማኝን ለማለት በሃሳብ ላይ ነኝ፣ ከኮምፒውተሬ ጋር ተፋጥጨ በሃሳብ ከርዕዮት አለሙ አልፊ ከእስክንድር ከውብሸት እና ከአንዷለም የእስር ፈተና ርቄ ፍትህን ፍለጋ ሄጃለሁ … “አሸባሪዎች!” አልኩ ለራሴ ውስጤ እየተቆጣ! ግን ዝም አልኩ … ጭጭ  … ዝም! ምን ይባላል!

ወጣቷ ጉብል ትፈታ ግን እላለሁ!

ከምሳ የተረፈችንን ራት አድርገን ከባለቤቴ ጋር እየቀማመስኩም ርዕዮትን አስታውሸ  ፍትህን ፍለጋ በሃሳብ ነጉጃለሁ … ምሽት ላይ አብረውኝ ሲጫዎቱ ያመሹትን ሁለት ታዳጊ ግረምሳ ልጆችን  በአመት በአል ተጠራርተን በአሉን ያደመቁ ዘምድ ጓደኛ ጎረቤቶችን አንዳፍታ ከነርዕዮት ጋር አዛምጀ ሳያቸው አመመኝ! በአውደ አመት ከልጅ ወላጅ ወዳጅ ዘመድ ተራርቀው የከረሙ እና እንዲከርሙ የተፈረደባቸው ወንድም እህቶች ጉዳይ በእርግጥም ያሳስባል ያማል! የሰረቀ፣ የገደለ በምህረት በሚፈታበት ሃገር የህዝብን በሶት በተናገረ መቀመቅ መውረድ አግባብ አይደለም ማለቱ በዘመኑ ባያዋጣም፣ ይቅርታ ምህረት ጠይቆ መነፈግ ልብ የሚሰብረውን ያህ ስብራት አጣሁለት! የእነ ርዕዮትን ስቃይ፣ እስራት! የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ! ሰላማዊ እርቅ ይበጀናል እላለሁ!

መንገድ ላይ ተጥላ የተገኘችው የኮንትራት ሰራተኛ …

ብዙ ርቄ ስጓዝ ስልኬ አቃጭሎ ከነጎድኩበት ሃሳብ ተመለስኩ … ከአንድ ወዳጀ የደረሰኝ የስልክ ጥሪ አዲሱን አመት ዳግም በአሳዛኝ መረጃ ቅበላ እንድጀምር አስገደደኝ፡፡ (እየተኮላተፈ አማርኛ የሚናገር ወዳጁ መንገድ ላይ አንዲት አትዮጵያዊት በአሰሪዎቿ ተጥላ እንዳገኘና ሃበሻ የሚያውቅ እሱን በመሆኑ እንዲረዳት መረጃ አቀብሎት ይህችን እህት እንዴት መርዳት እንደሚቻል “የተሻለ መረጃ ካለህ” ብሎ ሊያማክረኝ መደወሉን አጫወተኝ!  እኔም ከሁሉ አስቀድሞ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎችን እንዲያነጋግር በመምከር አድራሻ ጭምር አቀበልኩት እና በጉዳዩ ዙሪያ አማክሬው ስልኩን ዘጋን …

ወዳጀ በደረቁ ሌሊት መልሶ ደውሎ የደረሰበትን መረጃ አቀበለኝ … ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ደውሎ ቆንስል ሙንትሃን በማግኘት ችግሩን አስረድቶ መፍትሔ ጠየቀ። ከዚያም ቆንስል ሙንትሃ ልጅቱን ወደ ቆንሰሉ መጠለያ በመውሰድ ለመጠለያው ሃላፊ ለወ/ሮ አዜብ እንዲያስረክባት መክረውት ወደ ጅዳ ቆንሰል መጠለያ መሄዱን ገለጸልኝ፣  በቆንስላው ሲደርስ የተባሉት የመጠለያ ሃላፊም ሆኑ የሚመለከታቸው በቦታው አለማግኘቱን ወዳጀ በአግራሞትና በብስጭት የሆነውን ሁሉ ገልጾልኛል! ለመጠለያውን እና ለኮሚኒቲውን ጠባቂዎች ጉዳዩን በማስረዳት ይህች መንገድ ላይ ተጥላ ያገኟት እህት የቀሩትን  ከ140 የዘለቁ ተፈናቃዮች ለመቀላቀል ይቻላት ዘንድ የቆንስል ሃላፊዋን መልዕክትና ቃል ቢገልጹም ከጠባቂዎች ጋር መግባባት አልተቻለም!

ይህች ምስኪን እህት ለሃገር ምድሩ ባዳ በሆነችበት ሰማይ ስር መንገድ እንደመጣሏ ወገኖቿ የደረሱላት መሆኑ ቢያስደስትም ወደ መጠለያው ለመግባት ፈቃድ አለማግኘቷ ያበሳጨው መረጃውን ያቀበለኝ ወንድም እልህ እና ቁጭት እየተናነቀው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ስልክ ደውሎ እንዲህ ነበር ያለኝ “አቶ ነቢዩ ዘበኞች አትገባም አሉን፣ ወደ ጅዳው ቆንስል ሃላፊ አቶ ዘነበ ደወልን ስልካቸው ዝግ ነው! መልሰን ለቆንስል ሙንትሃ ደወልን፣ ቅድም ውሰዷት እና ለወ/ሮ አዜብ አስረክቧት ያሉኝ እመቤት ደጋግምን ብንደውልም ስልካቸውን አያነሱም፣ ምን ማድረግ ይቻላል? ግን … ወገናችን ይህን መከራ ላለማየት እህታችን ሜዳ ላይ አይተን እዳላየን በጭካኔ ጥለን መሄድ ነበረብን? …”  ብሎ ጠየቀ!  ብዙ ተነጋግረን ስልኩ ተዘጋ … አንደምንም  በግል አስጠግቶ አሳድሮ ነገ የሚሆነውን ለማድረግ ተስማምተን ከተሰነባበትን በኋላ መልሸ አሁንም የደረሰበትን ሁኔታ ለመረዳት ስደውልለት መልካም የምስራች አበሰረኝ ፣ እንዲህ ሲል “አዎ ተሳካ! የቆንስል ሃላፊዎች ስልካቸውን ማንሳት ባይችሉና የምናደርገው ጠፍቶን ብንንገላታም በፍቃድ ማግኘት ያልቻሉትን ወደ መጠለያ የማስጠጋት ሙከራ ሰው በሰው (በዋስጣ) ይህች አንጀት የምትበላ እህት ወደ ቆንስሉ መጠለያ ልትገባ ችላለች!” ብሎኛል!

በየሜዳው እየተጣሉ ያሉ የኮንትራት ሰራተኛ እህቶቻችን ከችግር ብዛት እስከ ማበድ ራሳቸውን እስከ ማጥፋት እንዳደረሳቸው እያየን ነው!  ሰብዕናው ቢገደን ገጽታችን እንዳያጠፉት እህቶቻችን ወደ መጠለያ በመሰብሰቡ ረገድ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ዛሬም ድምጻችን ሰምተው ሳይሆን ግፉአኑን ከደጃቸው ተመልክተው አንድ ቢሉን መልካም ነው!

የአዲሱ አመት የማለዳ ወግ  በመራራው ሮሮ ጀመርኩት … በአዲስ አመትም ያላባራው ሰቆቃ እና ልናገረው የከበደኝ ሮሮ! አልኩት … ልተንፍሰው በሚል ከብዙ ጥቂቱን ነካክቸ … ምን ላድርግ  ! የአረብ ሃገር ስደት  ኑሯችን እንዲያ ሆኗል!

እሰኪ ቸር ያሰማን!

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule