ማሳሰቢያ፦ በቀርቡ በወጣችው ጦማር ላይ “እንዲህ ያለ ፓትርያርክ አይተን አናውቅም” በሚል ርእስ እንገናኝ ብዬ በመሰናበቴ በዚህ ርእስ የሚቀርበውን አንባቢ እንደሚጠብቅ የታወቀ ነው። ይሁን እንጅ ያለፈው እሁድ ደብረ ዘይት የሚታሰብበት ቀን ስለነበረ፤ ይህች ጦማር የያዘችው መልእክት በከንሳስ ደብረ ሳህል መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቀረበ። ትምህርቱን የተካፈሉት ምእመናን በዓለም ዙሪያ ላለው ሁሉ ህዝብ ይድረስ” የሚል ሀሳብ ስላመነጩ “እንዲህ ያለ ፓትርያርክ አይተን አናውቅም” በሚል ርእስ የተዘጋጀውን ጦማር አዘግይቼ ይህችን ጦማር አስቀደምኩ። “እንዲህ ያለ ፓትርያርክ አይተን አናውቅም” በሚለው ርእስ የተዘጋጀው ጦማር ይቀጥላል። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ደብረ ዘይትና አባ ማትያስ
Opinions
የኔ ሃሳብ
ዘር ማጥራትን ያህል ወንጀል ፈጽሞ ይቅርታ መጠየቅ ፌዝ ካልሆነ ድራማ ነው!
በፌዴራል ስም የተሸፈኑ ህውሃት/ኢህአዴጎች እና በአቶ መለስ ራዕይ የተጠመቁ የክልል ፖለቲከኞች በኢትዮጵያ የዘር ማጥራት (Ethnic Cleansing) ወንጀል ስለመፈጸማቸው መዘገብ ከጀመረ ውሎ አድሯል። ይኽ ዜና በኢትዮጵያ ወዳጆች ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ዜጎች ዘንድ ስጋት ፈጥሯል። ኢትዮጵያ እንድትበተን የሚፈልጉ ግን አፍና እጃቸውን አስተባብረው ኢትዮጵያ የምትባል አገር ከመንገዳቸው ላይ ተወግዳ ህልማቸው ወደሆኑት የቃል-ኪዳን አገሮቻቸው (Promised-land) ለመድረስ የጀመሩትን ጉዞ ፍጥነት እና ግልጽነት ሳያመቻቸው ዝቅ ሲያመቻቸው ደግሞ ከፍ ያደርጋሉ እንጂ አያቆሙም። የህውሃት ሕገ መንግስት (አንቀጽ 39) ግፉ በርቱ ይላል። ስለዚህ የቤንሻንጉል ጉምዝ አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ናስር ቀደም ብሎ በቪኦኤ አማርኛ ፕሮግራም ሲጠየቅ አፉን ሞልቶ ሞቅ ባለ ስሜት አማርኛ ተናጋሪውን … [Read more...] about ዘር ማጥራትን ያህል ወንጀል ፈጽሞ ይቅርታ መጠየቅ ፌዝ ካልሆነ ድራማ ነው!
ፈሪ ህዝብ አድርባይ እንጂ የልማት ሰራዊት መሆን አይችልም
የኢትዮጵያ እዝብ በተፈጥሮው ፈሪ ህዝብ ነው ብዬ አላምንም፡ ነገር ግን ለብዙ ዘመናት የተለዋወጡ ገዚዎች በፈጠሩበት ተጵህኖ በፍራቻ ድባብ ውስጥ እንዲኖር አድርጎታል ብዬ አስባለው እስከ አሁን ድረስ። የአገሩን ዳር ድንበር ና ነጳነት በአጋጣሚ ሳይሆን በደሙ ጠብቆ የኖረን ህዝብ ፈሪ ነው ብሎ ማሰብ እብደት ነው። ነገር ግን በውስጥ ገዚዎች መካከል የተደረጉ ግጭቶች ያደረሱበት ጉዳት ፡ (የቅርቦቹን እንኳን ብንወስድ የቀይ ሽብርና 1997ቱ ምርጫ ግጭቶች) ፣ ኢፍታዊነት ፣ የፖለቲካ ፣ ፍትህ ና ሰብሃዊ መብት ግንዛቤ ችግር በፍራቻ ድባብ ና በግል እስካልነኩኝ አያገባኝም በሚል ጠባብ የአህምሮ እስር ቤት ውስጥ እንዲኖር አድርጎታል። በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያዊ ማለት መብቱ ሲጣስ እሺ፣ ሲፈናቀል እሺ ፣ ንብረቱ ሲቀማ እሺ ፣ ፍትህ ሲዛባ እሺ ፡ሲታሰር እሺ ፣ ሰለ ፍትህ ፣ … [Read more...] about ፈሪ ህዝብ አድርባይ እንጂ የልማት ሰራዊት መሆን አይችልም
የዓሣ ግማቱ ከአናቱ!!
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ! አሜን። ወንድሞች ሆይ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው ኃጢያተኛውን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን የኃጢያትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ። የያዕቆብ መ.5፤19-10። እግዚአብሔር በዘመናት መካከል ለሕዝቡ በባሪያዎቹ እየተናገረ፤ ሕዝቡን ከመከራ እና ከመተላለፋቸው እየመለሰ፤ ወደ ክብሩ መንግስት እያፈለሰ፤ ዓለም ከፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ አሁን እኛ እስከደረስንበት ጊዜ ድረስ ወንጌል ወደ እኛ ደርሷል። ወደፊትም ዓለምን ከመኖር ወደ አለመኖር እስከሚያመጣት ድረት ይኸ ሁኔታ ይቀጥላል። ስለሆነም ሕዝቡ ባለማወቅ ጨለማ ውስጥ ሲተራመስ ፤ ሕዝቡን በጨለማ ውስጥ የማይተው አምላክ በወደደው ጊዜና ስዓት ነገሮችን ከተሰወሩበት ግርዶሽ ውስጥ ወዶ ይገልጣል። ዛሬም ቃሉንም ሆነ ህጉን ካለማወቃችን የተነሳ … [Read more...] about የዓሣ ግማቱ ከአናቱ!!
Developmental Neo-Patrimonialism
Beware! “Our Allies – The West, The Occident” are designing A New Ideology for Africa. It has been launched as a research project way back in 2011 and is now coming forward, with a claim to be the panacea of poverty in the African Continent! The Big catechism is “DEVELOPMENTAL” but the real backdrop is “Patrimonial”, the new face of promoting racism and perpetual ethnic conflicts to get in touch to the resources of our continent! Ethiopia is promoted as the Prototype for the new face of racist … [Read more...] about Developmental Neo-Patrimonialism
የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ
በአሁኑ ሰዓት በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን መፈናቀል በመቃውም በኦስሎ ከተማ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠርቷል፡፡ በአካባቢው የምትገኙ ሁሉ በሰልፉ ላይ እንድትገኙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን ያቀርባሉ፡፡ መረጃውን ከምስሉ ላይ ይመልከቱ፡፡ … [Read more...] about የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ
World Bank Must End its Support for Human Rights Abuses in Ethiopia
ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ ጎልጉል “ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል” ዓለም ባንክ ርምጃ ለመውሰድ ጫፍ ደርሷል በሚል እና ኢህአዴግ በ600 ሚሊዮን ዶላር አጣብቂኝ ውስጥ ገባ!! ብያኔው ከጸና ኪሣራው በቢሊዮን ዶላር ሊደርስም ይችላል! በሚል ርዕስ ሰፋ ያለ ዘገባ ማቅረባችን ይታወቃል፡፡ የዓለም ባንክ እስካሁን ውሳኔውን ይፋ በማድረግ ለኢትዮጵያ የሚሠጠውን ዕርዳታና ብድር ምርመራ እንዲደረግበት አለማስጀመሩ የብዙዎች ጥያቄ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ኢህአዴግ ከዓለም ባንክ የሚሠጠውን ዕርዳታ ለፖለቲካ ተግባር ማዋሉ የመርማሪው ቡድን ቦታው ድረስ በመሄድ ምርመራ አድርጎ ያረጋገጠ ቢሆንም ከየአቅጣጫው እየተሰነዘሩ ያሉት ተጸዕኖዎችም በከፍተኛ ሁኔታ እየተጠናከሩ መጥተዋል፡፡ የዚህ ጦማር ዋንኛ ዓላማም በዚሁ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ A multi-billion dollar aid program … [Read more...] about World Bank Must End its Support for Human Rights Abuses in Ethiopia
ሰላማዊ ትግል እና የመለስ ራዕይ ዘር-የማጥራት ወንጀል ስለመሆኑ
ከጉራፈርዳ እና ከቤንሻንጉል-ጉምዝ የተሰሙት ድምጾች ዘር የማጥራት (Ethnic Cleansing) ወንጀል በኢትዮጵያ ህጋዊ መሆን መጀመራቸውን አስታወቁ። እነዚህ ድምጾች የኢትዮጵያ ፌዲራል መንግስት እና የክልል መንግስቶች ኢትዮጵያን ለመበተን ውስጥ ውስጡን የነበራቸውን የአሳብ እና የተግባር ስምምነት ገሃድ በማውጣት የኢትዮጵያ አንድነት አደገኛ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ግልጽ አደረጉ። የኢትዮጵያ አንድነት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ለሚመኙ አገር ወዳዶች በሙሉ እንቅልፍ የሚነሳ መልዕክት አስተላልፈዋል ከጉራፈርዳ እና ከቤንሻንጉል-ጉምዝ የተሰሙት ድምጾች ። የኢትዮጵያችን ጉዳይ ያገባናል ለሚሉ አገር ወዳድ ዜጎች በሙሉ የኢትዮጵያ ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት እስከሚሆን ድረስ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የተደቀነውን አደጋ ለመከላከል ያልተቋረጠ በድስፕሊን የታነጸ ሰላማዊ ትግል ማድረግ … [Read more...] about ሰላማዊ ትግል እና የመለስ ራዕይ ዘር-የማጥራት ወንጀል ስለመሆኑ
SMNE’s Press release
Oromo Democratic Front (ODF) Declares Commitment to Work with Others towards a Democratic, Multi-national Ethiopia: Is this the Same “New Ethiopia” We in the SMNE Envision? On March 30, 2013, I had the privilege of watching history in progress while attending the first meeting of the newly formed Oromo Democratic Front (ODF) as an observer. Those involved included most of the founding leaders of the Oromo Liberation Front (OLF). As they announced their new vision, direction and organization … [Read more...] about SMNE’s Press release
የ እስክንድር ወንጀሉ መምከሩና ኣቅጣጫ ማሳየቱ ብቻ ነው
ኣንድ ጊዜ ኣባባ ተስፋየ ከዚያ ከሚያምርባቸው የ ልጆች ክፍለ ጊዜ ዝግጅታቸው ጠፉብኝና ኸረ የት ገቡ? ብየ ኣንዱን ጠየኩ። “ኣልሰማህም እንዴ ?” በፍጹም ምን ሆኑ? ደንገጥ ብየ እንደገና ጠየኩ። ያ ሰው እየሳቀ “ባለፈው ጊዜ ኣዲሱ ኣመት የሰላምና የእርቅ ያድርግልን ብለው በመናገራቸው የመንግስት ሰዎች ማን ሲጣላ ኣዩ? ብለው ኣባረሩዋቸው እኮ!” ሲለኝ ለደቂቃዎች እንደዚያ የሳቅኩበት ጊዜ ትዝ ኣይለኝም። የሁለታችንም ሳቅ ካለቀ በሁዋላ እውነተኛው ስሜት ሲመጣ ደሞ ያስለቅሳችሁዋል። ነገሩ እውነት መሆን ኣለመሆኑን ኣጥብቄ ኣልጠየኩም፣ ለነገሩ ከዚያ ቀን በሁዋላም ከብዙ ሰው ይህንኑ ሰማሁ። ነገሩ በትክክል ሆነም ኣልሆነም ያ ሁሉ ሰው መንግስት እንደዚያ ሊያደርግ ይችላል ብሎ ማሰቡ ራሱ ነገሩ መሆኑን ኣለያም ሊሆን መቻሉን ያሳያል። በዚያች ኣገር ምን የማይሆን ኣለና። በዚህ ስደነቅ … [Read more...] about የ እስክንድር ወንጀሉ መምከሩና ኣቅጣጫ ማሳየቱ ብቻ ነው









