• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሠራተኛውን ማን አቃጠለው?

October 14, 2015 07:29 pm by Editor 2 Comments

የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) ከጥቂት ቀናት በፊት በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ ኤሊ ውሃ ከተማ ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም ስለተፈጸመው ግድያ መረጃ ልከውልናል፡፡

ከመረጃ አቀባያችን ጋር በተደጋጋሚ በተላላክነውና ባቀረብነው በርካታ ጥያቄዎች መሠረት ያገኘነው መረጃ ይህንን ይመስላል፡-

እጅግ ዘግናኝ የሚባለው ግድያ የተፈጸመው ከላይ በተጠቀሰው ሥፍራ በሚገኘው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት እየተባለ በሚጠራው ግቢ ውስጥ ነው፡፡ የእማኝ ዘጋቢው በራሳቸው አገላለጽ እንዲህ ዘግበውታል፡- (የላኩልን የእንግሊዝኛ ፊደላትን በመጠቀም ሲሆን ወዳማርኛው እንዲህ መልሰነዋል)

“ወንጀሉ የተፈጸመው ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ በኤሊውሃ ከተማ ግቢ ተብሎ በሚጠራው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት ውስጥ ነው፡፡ የተቃጠለው ልጅ ወልዱ ይባላል፡፡ በ(ፕሮጀክቱ) የላቦራቶሪ ሠራተኛ ነበር፡፡ ሟች ወጣት ወልዱ በላቦራቶሪ ክላስ ውስጥ ቤንዚን እየቀዳ ነበር፡፡ ብዛት ያላቸው የቤንዚን ጄሪካኖች ነበሩ፤ አለቃው ቻይናዊ ይመጣና ሲጋራ ወደ ቤንዚኑ ይወረውራል፤ ከዚያ በኋላ ምን እንደተከሰተ ግልጽ ነው፤ ሙሉ ቤቱ ነደደ፡፡ ቻይናዊው እየሮጠ ወጥቶ ቤቱን አውጭ ዘጋው፤ በቃ ወጣት ወልዱ አይሞቱ ሞት ሞተ፤ እርር፣ ክስል ብሎ በቁሙ ዓይኑ እያየ አንዳች እርዳታ ሳያገኝ ተቃጥሎ ሞተ፡፡ ከዚህ በኋላ ሬሳውን ይዘው ምርመራ ቤተሰብ ፍለጋ እያሉ ለ4 ቀን ካንከራተቱት በኋላ መልሰው እዚያው ኤሊ ውሃ ከተማ ቤተሰቦች በሌሉበት ተቀበረ፤ ወንጀሉን የፈጸመው ቻይናዊ ግን እስካሁን ለፍርድ አልቀረበም፡፡ ምክንያቱም የወረዳው መንግሥት ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡”

ይህ ከደረሰን በኋላ የእማኝ ዘጋቢውን ተጨማሪ ዝርዝር ለማግኘት ጥያቄዎችን አንስተን ነበር፡፡ በጥያቄያችን መሠረትም የሟችን የተቃጠለ ምስልና ከመሞቱ በፊት ያለውን ምስሉን የሚያሳይ ሁለት ፎቶዎች ልከውልናል፡፡ የተቃጠለው ሬሣ እጅግ ዘግናኝ ከመሆኑ ባሻገር ማንነቱ ጠፍቶ ለመለየት በሚያስቸግርበት ሁኔታ ከሌላ ወገን ማረጋገጥ የሚቻል ባለመሆኑ ከሁሉ በላይ ግን መሞቱ በቤተሰቡ ዘንድ የታወቀ ባለመሆኑ ይፋ ከማድረግ ተቆጥበናል፡፡ ሆኖም አሁንም ይህ መረጃ አቀባዩ በራሳቸው አነሳሽነት የላኩት የእማኝ ዘገባ በመሆኑ ላቀረብናቸው ተጨማሪ ጥያቄዎች የላኩት ምላሽ በአጭሩ ይህንን ይመስላል፡-

“ወጣት ወልዱ የተባለው ሟች የአፋር አፈር (soil) ላቦራቶሪ ሠራተኛ ነው፡፡ ለላቦራቶሪ ሥራ የሚጠቀምበትን ማሽን የሚያንቀሳቅስው ቤንዚን በመጠቀም ነው፤ እሱን በዚህ ሥራ የተሰማሩ ባለሙያዎች የበለጠ ማብራሪያ መጠየቅ ይቻላል፤ እናም ለዚህ ሥራ የሚጠቀምበት የሚበቃውን ያህል ለመቅዳት በቤንዚን ክፍል ውስጥ እያለ ነው ይህ አረመኔ ቻይናዊ ወደሱ መጥቶ ወደ ውስጥ በመግባት ሲያጨስ የነበረውን ሲጋራ በመወርወር አደጋው የተፈጠረው፡፡ የቤተሰቡን ጉዳይ እስካሁን ለማወቅ አልተቻለም፤ የትግራይ ክልል ተወላጅ እንደሆነ ብቻ ነው የሚታወቀው፡፡ እናም ሬሣውን እስከ መቀሌ ከተማ ድረስ ወስደው ለማጣራት ሙከራ አድርገናል ነው የሚሉት ግቢው ውስጥ የሚገኙ የፌዴራል ፖሊሶች፡፡ ግን መሞቱን ለማሳወቅ ያደረጉት እንቅስቃሴ በጣም አነስተኛ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ከቻይናዎች አንድ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃ ሲጠፋቸው (ፖሊሶቹ) አሳድደው አዲስ አበባ ውስጥ ሊያዝ ችሏል፤ እና ይህንንም ጉዳይ ቢያስቡበት ቤተሰቦቹ ማግኘት ይችላሉ ብዬ እገምታለሁ፡፡”

ወንጀሉን የፈጸመው አለቃው ስም ማን እንደሆነ የእማኝ ዘጋቢው ሲናገሩ በራሳቸው አገላለጽ “wenjelun yefetsemew aleqaw yehoneaw Mr Waan yetebale chinawi neaw” (“ወንጀሉን የፈጸመው አለቃው ሆነው ሚስተር ዋን የተባለ ቻይናዊ ነው፡፡”) በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ይህ የእማኝ ዘጋቢው መረጃ ሲሆን ጎልጉል በሥፍራው ዘጋቢ ስለሌለው በቦታው የሚገኙትን ባለሥልጣናት በግምባር ለማነጋገር አልቻለም፡፡ ሆኖም ግን ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተውን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ምላሽ እንዲሰጥ ሞክረን ስልኩ ሳይነሳ በመቅረቱ መረጃ ለማግኘት አልተቻለም።

ሞተ የተባለውን ወጣት የሚያውቁ ቤተሰቦችም ሆኑ የቅርብ ወዳጆች በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ እንዲሰጡ እንጠይቃለን፡፡ እንደሚዲያ እኛ ከእማኝ ዘጋቢ ያገኘነውን አቅርበናል፤ ዜናው የመረጃ አቀባዩ ነው፤ ሆኖም ግን በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሠሩ ድርጅቶች እና የሕዝብ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሁኔታውን ማጣራትና ዳር ማድረስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ አሠሪ የተባለው መሥሪያቤትም ይህንን የመመርመርና የተባለው ቻይናዊ ወንጀለኛ ከሆነ ለፍርድ የማቅረብ ከፍተኛ ኃላፊነት አለበት፡፡ “ዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን” የዜጎችንም ህይወት የሚመለከት ይመስለናል፡፡

ጎልጉል የእማኝ ሪፖርተሮች ያሉት ሲሆን በነዚሁ ምንጮቹ አማካይነት መረጃ ለህዝብ ሲያቀርብ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ለዚህም ነው “ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ ነው” የምንለው፡፡ ይህ ዜና ክዘግናኝነቱ ባሻገር ከጀርባው ልዩ ሚስጥር እንደሚኖረው ስለሚታመን ዜናው የሚመለከታችሁ ወገኖች ምላሽም ይሁን ማስተባበያ እንዲሰጡ እንማጸናለን።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Opinions, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Abe says

    October 18, 2015 06:31 pm at 6:31 pm

    This is so shocking and terrifying news beyond one’s human absorb and imagination to live with. Never such type of crime committed in Ethiopia before except by the then Fascist Italy during its Colonial Invasion Attempt in 1935-1940. Are the Chinese our modern day colonizers and have the right to decide on our living and life beyond their economic involvement? Its great shame to our country, people, and above all, to our “Government”. How can a bilateral relationship with China continues while this type of atrocity is going on our citizens? What is the value of so called “Development” while you are exposing your people to such horrendous acts and dreadful situations.
    After all, the Chinese are not investing nor providing relief or development aid to Ethiopia. They are simply loaners of their surplus with steep interest rate and labour contract (hiring their citizens) attached to it.
    We have to rise, stand up , fight and speak louder for our rights (at least for our natural rights). We need to make and force our leaders to be accountable and responsible. Otherwise, we keep on living in such abominable situation and lead undignified life and death. We also lose our country slowly to “Chinese Imperialism”to use the words of Alberto Acosta, former Ecuador Energy Minister.

    Reply
  2. Belhu says

    November 29, 2015 07:39 pm at 7:39 pm

    በቤንሻንጉል ክልል በሐሰት የትምሕርት ማስረጃ በመያዝ (በተለየ ከሰሜን ኢትዮጲያ የመጡ) URRAP በሚባል የገጠር መንገድ ስራ ፕሮጀክቶች በመደራጀት ኢንጅነር በመባል ሚሊዮኖችን እየዘረፉ ይገኛሉ:: መረጃውን ለሚመለከተው አድርሱልን::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule