• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች

April 1, 2021 01:04 am by Editor Leave a Comment

በምዕራብ ወለጋ ዞን በርካታ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ።

ግድያው የተፈጸመው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል እያለ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ “እኛ የፖለቲካ ሰዎች አይደለንም፤ ገበሬዎች ነን ፤ መንግስት ለምን አይደርስልንም?” ብለዋል።

በኦሮሚ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ፣ ትናንትና
ምሽት 3 ሰዓት ላይ በርካታ ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን የአካባቢ ነዋሪዎች
የተናገሩት። ነዋሪዎቹ ፤ አሁን ላይ አስክሬኖች በየቦታው ተጥለው መገኘታቸውን ገልጸው ቁጥሩ ምን ያህል ነው የሚለውን ለመግለጽ አስቸጋሪ እንደሆነ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

ሕጻናትና ሴቶች አሁን ላይ ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ ጫካዎች መግባታቸውን
የገለጹት አስተያየት ሰጭዎቹ፤ መንግስት የማይደርስላቸው ከሆነ አሁንም ሌላ
ግድያ ሊኖር እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የፌዴራል የጸጥታ ኃይሎች በቦታው አለመድረሳቸውን የገለጹት
ነዋሪዎቹ፤ አስክሬኖች የተጣሉበት ቦታ ጋሪ የማይገባበት በመሆኑ ለማንሳት
መቸገራቸውን ተናግረዋል።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉት እነዚህ ነዋሪዎች “እኛ የፖለቲካ ሰዎች
አይደለንም፤ ገበሬዎች ነን ፤ መንግስት ለምን አይደርስልንም?” ሲሉ ይጠይቃሉ።
በደረባ (በከብት ማደለቢያና መጠበቂያ ቦታ) ላይ ብቻ 20 አስክሬኖች መገኘታቸውን ያነሱት ነዋሪዎቹ አሁንም ከፍተኛ የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው
ነው የገለጹት።

አሁን ላይ በአካባቢው በርካታ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል አባላት እንዳሉ የገለጹት
ነዋሪዎቹ፤ “መከላከያ ወይም ፌዴራል ፖሊስ ካልገባ ልዩ ኃይሉ ከሞት
ያስጥለናል ብለን አናስብም ” ብለዋል።

በስልካቸው ፎቶና ተንቀሳቃሽ ምስል አንስተው እንዳይልኩ ስልካቸውን
መቀማታቸውን የገለጹት የቦኒ ቀበሌ ነዋሪዎች፤ አሁን የያዙት ስልክ ተለዋጭ እና የቤተሰባቸውን መሆኑን ገልጸዋል።

ግድያ የተፈጸመባቸው ዜጎች አማራ በመሆናቸው ብቻ መሆኑንም ነው አል ዐይን አማርኛ ያስታወቁት። የኦሮሚያ ክልል መንግስት በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ፣ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጧል። (አል ዐይን አማርኛ)

በምእራብ ወለጋ ንፁሀን ላይ ግድያ መፈጸሙን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ

በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ፣ ንፁሀን ላይ ግድያ መፈጸሙን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በጥቃቱም የሞቱት 16 ወንዶች እና 12 ሴቶች ህይወት ተቀጥፏል ሲሉ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል።

ከሟቾች በተጨማሪም 12 ሰዎችም ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል።

የክልሉ ፖሊስ በአካባቢው ደርሶ አካባቢውን ለማረጋጋት በደረገው ጥረት  ሶስት የኦነግ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል።

የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ከምሽቱ ሶሰት ሰአት ላይ ከ50 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎችን ሰብስቦ ጭፍጨፋ ፈፅሟል ሲሉ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። 

ባለፈው አንድ አመት በኦነግ ሸኔ ላይ በተወሰደም እርምጃ 1 ሺህ 947 አባላቱ የተገደሉ ሲሆን 489 አባላቱ ደግሞ መማረካቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ተናግረዋል። (ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, SHINE

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule