• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች

April 1, 2021 01:04 am by Editor Leave a Comment

በምዕራብ ወለጋ ዞን በርካታ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ።

ግድያው የተፈጸመው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል እያለ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ “እኛ የፖለቲካ ሰዎች አይደለንም፤ ገበሬዎች ነን ፤ መንግስት ለምን አይደርስልንም?” ብለዋል።

በኦሮሚ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ፣ ትናንትና
ምሽት 3 ሰዓት ላይ በርካታ ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን የአካባቢ ነዋሪዎች
የተናገሩት። ነዋሪዎቹ ፤ አሁን ላይ አስክሬኖች በየቦታው ተጥለው መገኘታቸውን ገልጸው ቁጥሩ ምን ያህል ነው የሚለውን ለመግለጽ አስቸጋሪ እንደሆነ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

ሕጻናትና ሴቶች አሁን ላይ ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ ጫካዎች መግባታቸውን
የገለጹት አስተያየት ሰጭዎቹ፤ መንግስት የማይደርስላቸው ከሆነ አሁንም ሌላ
ግድያ ሊኖር እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የፌዴራል የጸጥታ ኃይሎች በቦታው አለመድረሳቸውን የገለጹት
ነዋሪዎቹ፤ አስክሬኖች የተጣሉበት ቦታ ጋሪ የማይገባበት በመሆኑ ለማንሳት
መቸገራቸውን ተናግረዋል።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉት እነዚህ ነዋሪዎች “እኛ የፖለቲካ ሰዎች
አይደለንም፤ ገበሬዎች ነን ፤ መንግስት ለምን አይደርስልንም?” ሲሉ ይጠይቃሉ።
በደረባ (በከብት ማደለቢያና መጠበቂያ ቦታ) ላይ ብቻ 20 አስክሬኖች መገኘታቸውን ያነሱት ነዋሪዎቹ አሁንም ከፍተኛ የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው
ነው የገለጹት።

አሁን ላይ በአካባቢው በርካታ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል አባላት እንዳሉ የገለጹት
ነዋሪዎቹ፤ “መከላከያ ወይም ፌዴራል ፖሊስ ካልገባ ልዩ ኃይሉ ከሞት
ያስጥለናል ብለን አናስብም ” ብለዋል።

በስልካቸው ፎቶና ተንቀሳቃሽ ምስል አንስተው እንዳይልኩ ስልካቸውን
መቀማታቸውን የገለጹት የቦኒ ቀበሌ ነዋሪዎች፤ አሁን የያዙት ስልክ ተለዋጭ እና የቤተሰባቸውን መሆኑን ገልጸዋል።

ግድያ የተፈጸመባቸው ዜጎች አማራ በመሆናቸው ብቻ መሆኑንም ነው አል ዐይን አማርኛ ያስታወቁት። የኦሮሚያ ክልል መንግስት በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ፣ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን አረጋግጧል። (አል ዐይን አማርኛ)

በምእራብ ወለጋ ንፁሀን ላይ ግድያ መፈጸሙን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ

በምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ጋምቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ፣ ንፁሀን ላይ ግድያ መፈጸሙን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በጥቃቱም የሞቱት 16 ወንዶች እና 12 ሴቶች ህይወት ተቀጥፏል ሲሉ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል።

ከሟቾች በተጨማሪም 12 ሰዎችም ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል።

የክልሉ ፖሊስ በአካባቢው ደርሶ አካባቢውን ለማረጋጋት በደረገው ጥረት  ሶስት የኦነግ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል።

የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ከምሽቱ ሶሰት ሰአት ላይ ከ50 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎችን ሰብስቦ ጭፍጨፋ ፈፅሟል ሲሉ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል። 

ባለፈው አንድ አመት በኦነግ ሸኔ ላይ በተወሰደም እርምጃ 1 ሺህ 947 አባላቱ የተገደሉ ሲሆን 489 አባላቱ ደግሞ መማረካቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ተናግረዋል። (ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, SHINE

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule