• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደቡብ የህወሓት ኅልውና እያከተመ ነው

June 25, 2018 11:12 am by Editor Leave a Comment

ለኢህአዴግ ሊቀመንበርነትና ለጠቅላይ ሚኒስትርነት የህወሓት እጩ በመሆን የቀረበውና በህወሓት ሙሉ ድምጽ የተሰጠው ሽፈራው ሽጉጤ ከደቡብ ሕዝብ ሊቀመንበርነቱ ለቀቀ።

ሽፈራው ሽጉጤ ራሱ እንደተናገረው ከሆነ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ቢልም አፍቃሪ ህወሓት የሆኑና እርሱ በኢህአዴግ ሊቀመንበርነት እንዲመረጥ የፕሮፓጋንዳ ሥራ ሲሠሩ የነበሩ ሰውየው “ተገፍቶ ነው” የወጣው በማለት አቅጣጫ የማስቀየር ሙከራ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

በቅርቡ በሃዋሳ በደረሰው ግጭት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የሚመለከታቸው አመራሮች በግጭቱ ውስጥ ተሳታፊ ቢሆኑም ባይሆኑም ይህ ዓይነቱ ግጭት እየተፈጠረ በኃላፊነት መቀጠል እንደሌለባቸውና ከሥልጣናቸው በፈቃዳቸው መልቀቅ እንዳለባቸው ሃሳብ ሰጥተው ነበር። ይህንንም ተከትሎ ከወላይታ ዞን አራት አመራሮች በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን መልቀቃቸውን በደብዳቤ ማሳወቃቸው ይታወሳል።

በዚሁ የሃዋሳ ግጭትና ያንን ተከትሎ በተፈጸመው ግድያ ሽፈራው ሽጉጤ ተጠያቂ እንደሚሆንና ሕዝቡም “አይወክለንም” በማለት ድምጹን ሲያሰማ መቆየቱን በቪኦኤና በሌሎች የሚዲያ ውጤቶች መዘገቡ ይታወቃል።

በበርካታ ወንጀሎች በተለይም በደቡብ ክልል ይኖሩ የነበሩ አማሮችን ከቀያቸው እንዲለቁ በማስገደድ ግፍ እንደፈጸመ በተደጋጋሚ የሚነገርበት ሽፈራው ከፓርቲው ሊቀመንበርነቱ መነሳት ቀጥሎ ከሚኒስትርነቱም እንደሚለቅ በስፋት ይነገራል። በደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በነበረበት ዘመን ፈጽሞታል ከሚባለው ወንጀሎች ጋር በህወሓት አጋርነቱ በሌሎች ሤራዎችም ይጠረጠራል። በዚህ ላይ አስተያየታቸውን የሚሰጡ እንደሚሉት በቀጣይ ወደ ፍርድ ከሚመጡ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት ሽፈራው ሽጉጤ ቀዳሚው ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አላቸው።

ከኦህዴድንና ብአዴን መክዳት ጋር በተያያዘ ህወሓት አለኝ የሚለው ቀሪው አጋዡ ደኢህዴን እንደሆነ የሚነገር ሲሆን ይህንንም አጠናክሮ የያዘለት ሽፈራው ሽጉጤ ነበር። ከሚመራው የደቡብ ሕዝብ ጥቅም ይልቅ የህወሓት ጉዳይ ይበልጡኑ የሚያሳስበው ሽፈራው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን በህወሓት በኩል ከፍተኛ ጫና ሲደረግ ነበር፤ ህወሓትም ሙሉ ድምጽ ሰጥታው ነበር።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ ከሰበሰበው አስተያየት መካከል “አብሬው ሠርቻለሁ” የሚሉ አስተያየት ሰጪ በማኅበራዊ ድረገጽ እንደጻፉት “ሽፈራው ማለት በጣም ደካማ፣ ከዕውቀት የጸዳ፣ ግብረገብነት የሌለው፣ አእምሮው የሞተ ሰው ነው፤ ከዚህ በፊት የኢህአዴግ ሊቀመንበር ሆኖ ለመመረጥ እጩ ሆኖ መቅረቡን ስሰማ ታምሜ ነበር፤ የኢህአዴግ ፖለቲካ ባይሆን ኖሮ፤ ሽፈራው ሚኒስትር መሆን አይደለም የሚኒስቴሩ መሥሪያቤት ጥበቃ የመሆን ብቃት የሌለው ሰው መሆኑን እመሰክራለሁ” ብለዋል።

ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ያስፈነጠረው መለስ ዜናዊ፤ የኢህአዴግን ዓላማ እስካስፈጸመ ድረስ መሃይምም ቢሆን በሚኒስትርነት እንሾማለን በማለት ይነዳው ለነበረው ፓርላማ መናገሩ ይታወሳል።

የሽፈራውን ሥልጣን መልቀቅ ተከትሎ በተመሳሳይ የህወሓት ሹመኞች ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ የሚጠበቅ ሲሆን በተለይ ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመግደል ከተሞከረው ጋር በተያያዘ ከ“ቀን ጅቦቹ” መካከል ለፍርድ የሚቀርቡ እንደሚኖሩ ይጠበቃል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: abiy, eprdf, Full Width Top, Middle Column, resignation, shiferaw, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule