• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደቡብ የህወሓት ኅልውና እያከተመ ነው

June 25, 2018 11:12 am by Editor Leave a Comment

ለኢህአዴግ ሊቀመንበርነትና ለጠቅላይ ሚኒስትርነት የህወሓት እጩ በመሆን የቀረበውና በህወሓት ሙሉ ድምጽ የተሰጠው ሽፈራው ሽጉጤ ከደቡብ ሕዝብ ሊቀመንበርነቱ ለቀቀ።

ሽፈራው ሽጉጤ ራሱ እንደተናገረው ከሆነ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ቢልም አፍቃሪ ህወሓት የሆኑና እርሱ በኢህአዴግ ሊቀመንበርነት እንዲመረጥ የፕሮፓጋንዳ ሥራ ሲሠሩ የነበሩ ሰውየው “ተገፍቶ ነው” የወጣው በማለት አቅጣጫ የማስቀየር ሙከራ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

በቅርቡ በሃዋሳ በደረሰው ግጭት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የሚመለከታቸው አመራሮች በግጭቱ ውስጥ ተሳታፊ ቢሆኑም ባይሆኑም ይህ ዓይነቱ ግጭት እየተፈጠረ በኃላፊነት መቀጠል እንደሌለባቸውና ከሥልጣናቸው በፈቃዳቸው መልቀቅ እንዳለባቸው ሃሳብ ሰጥተው ነበር። ይህንንም ተከትሎ ከወላይታ ዞን አራት አመራሮች በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን መልቀቃቸውን በደብዳቤ ማሳወቃቸው ይታወሳል።

በዚሁ የሃዋሳ ግጭትና ያንን ተከትሎ በተፈጸመው ግድያ ሽፈራው ሽጉጤ ተጠያቂ እንደሚሆንና ሕዝቡም “አይወክለንም” በማለት ድምጹን ሲያሰማ መቆየቱን በቪኦኤና በሌሎች የሚዲያ ውጤቶች መዘገቡ ይታወቃል።

በበርካታ ወንጀሎች በተለይም በደቡብ ክልል ይኖሩ የነበሩ አማሮችን ከቀያቸው እንዲለቁ በማስገደድ ግፍ እንደፈጸመ በተደጋጋሚ የሚነገርበት ሽፈራው ከፓርቲው ሊቀመንበርነቱ መነሳት ቀጥሎ ከሚኒስትርነቱም እንደሚለቅ በስፋት ይነገራል። በደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በነበረበት ዘመን ፈጽሞታል ከሚባለው ወንጀሎች ጋር በህወሓት አጋርነቱ በሌሎች ሤራዎችም ይጠረጠራል። በዚህ ላይ አስተያየታቸውን የሚሰጡ እንደሚሉት በቀጣይ ወደ ፍርድ ከሚመጡ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት ሽፈራው ሽጉጤ ቀዳሚው ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አላቸው።

ከኦህዴድንና ብአዴን መክዳት ጋር በተያያዘ ህወሓት አለኝ የሚለው ቀሪው አጋዡ ደኢህዴን እንደሆነ የሚነገር ሲሆን ይህንንም አጠናክሮ የያዘለት ሽፈራው ሽጉጤ ነበር። ከሚመራው የደቡብ ሕዝብ ጥቅም ይልቅ የህወሓት ጉዳይ ይበልጡኑ የሚያሳስበው ሽፈራው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን በህወሓት በኩል ከፍተኛ ጫና ሲደረግ ነበር፤ ህወሓትም ሙሉ ድምጽ ሰጥታው ነበር።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ ከሰበሰበው አስተያየት መካከል “አብሬው ሠርቻለሁ” የሚሉ አስተያየት ሰጪ በማኅበራዊ ድረገጽ እንደጻፉት “ሽፈራው ማለት በጣም ደካማ፣ ከዕውቀት የጸዳ፣ ግብረገብነት የሌለው፣ አእምሮው የሞተ ሰው ነው፤ ከዚህ በፊት የኢህአዴግ ሊቀመንበር ሆኖ ለመመረጥ እጩ ሆኖ መቅረቡን ስሰማ ታምሜ ነበር፤ የኢህአዴግ ፖለቲካ ባይሆን ኖሮ፤ ሽፈራው ሚኒስትር መሆን አይደለም የሚኒስቴሩ መሥሪያቤት ጥበቃ የመሆን ብቃት የሌለው ሰው መሆኑን እመሰክራለሁ” ብለዋል።

ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ያስፈነጠረው መለስ ዜናዊ፤ የኢህአዴግን ዓላማ እስካስፈጸመ ድረስ መሃይምም ቢሆን በሚኒስትርነት እንሾማለን በማለት ይነዳው ለነበረው ፓርላማ መናገሩ ይታወሳል።

የሽፈራውን ሥልጣን መልቀቅ ተከትሎ በተመሳሳይ የህወሓት ሹመኞች ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ የሚጠበቅ ሲሆን በተለይ ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመግደል ከተሞከረው ጋር በተያያዘ ከ“ቀን ጅቦቹ” መካከል ለፍርድ የሚቀርቡ እንደሚኖሩ ይጠበቃል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: abiy, eprdf, Full Width Top, Middle Column, resignation, shiferaw, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule