• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደቡብ የህወሓት ኅልውና እያከተመ ነው

June 25, 2018 11:12 am by Editor Leave a Comment

ለኢህአዴግ ሊቀመንበርነትና ለጠቅላይ ሚኒስትርነት የህወሓት እጩ በመሆን የቀረበውና በህወሓት ሙሉ ድምጽ የተሰጠው ሽፈራው ሽጉጤ ከደቡብ ሕዝብ ሊቀመንበርነቱ ለቀቀ።

ሽፈራው ሽጉጤ ራሱ እንደተናገረው ከሆነ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ቢልም አፍቃሪ ህወሓት የሆኑና እርሱ በኢህአዴግ ሊቀመንበርነት እንዲመረጥ የፕሮፓጋንዳ ሥራ ሲሠሩ የነበሩ ሰውየው “ተገፍቶ ነው” የወጣው በማለት አቅጣጫ የማስቀየር ሙከራ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

በቅርቡ በሃዋሳ በደረሰው ግጭት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የሚመለከታቸው አመራሮች በግጭቱ ውስጥ ተሳታፊ ቢሆኑም ባይሆኑም ይህ ዓይነቱ ግጭት እየተፈጠረ በኃላፊነት መቀጠል እንደሌለባቸውና ከሥልጣናቸው በፈቃዳቸው መልቀቅ እንዳለባቸው ሃሳብ ሰጥተው ነበር። ይህንንም ተከትሎ ከወላይታ ዞን አራት አመራሮች በፈቃዳቸው ሥልጣናቸውን መልቀቃቸውን በደብዳቤ ማሳወቃቸው ይታወሳል።

በዚሁ የሃዋሳ ግጭትና ያንን ተከትሎ በተፈጸመው ግድያ ሽፈራው ሽጉጤ ተጠያቂ እንደሚሆንና ሕዝቡም “አይወክለንም” በማለት ድምጹን ሲያሰማ መቆየቱን በቪኦኤና በሌሎች የሚዲያ ውጤቶች መዘገቡ ይታወቃል።

በበርካታ ወንጀሎች በተለይም በደቡብ ክልል ይኖሩ የነበሩ አማሮችን ከቀያቸው እንዲለቁ በማስገደድ ግፍ እንደፈጸመ በተደጋጋሚ የሚነገርበት ሽፈራው ከፓርቲው ሊቀመንበርነቱ መነሳት ቀጥሎ ከሚኒስትርነቱም እንደሚለቅ በስፋት ይነገራል። በደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በነበረበት ዘመን ፈጽሞታል ከሚባለው ወንጀሎች ጋር በህወሓት አጋርነቱ በሌሎች ሤራዎችም ይጠረጠራል። በዚህ ላይ አስተያየታቸውን የሚሰጡ እንደሚሉት በቀጣይ ወደ ፍርድ ከሚመጡ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት ሽፈራው ሽጉጤ ቀዳሚው ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አላቸው።

ከኦህዴድንና ብአዴን መክዳት ጋር በተያያዘ ህወሓት አለኝ የሚለው ቀሪው አጋዡ ደኢህዴን እንደሆነ የሚነገር ሲሆን ይህንንም አጠናክሮ የያዘለት ሽፈራው ሽጉጤ ነበር። ከሚመራው የደቡብ ሕዝብ ጥቅም ይልቅ የህወሓት ጉዳይ ይበልጡኑ የሚያሳስበው ሽፈራው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን በህወሓት በኩል ከፍተኛ ጫና ሲደረግ ነበር፤ ህወሓትም ሙሉ ድምጽ ሰጥታው ነበር።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ ከሰበሰበው አስተያየት መካከል “አብሬው ሠርቻለሁ” የሚሉ አስተያየት ሰጪ በማኅበራዊ ድረገጽ እንደጻፉት “ሽፈራው ማለት በጣም ደካማ፣ ከዕውቀት የጸዳ፣ ግብረገብነት የሌለው፣ አእምሮው የሞተ ሰው ነው፤ ከዚህ በፊት የኢህአዴግ ሊቀመንበር ሆኖ ለመመረጥ እጩ ሆኖ መቅረቡን ስሰማ ታምሜ ነበር፤ የኢህአዴግ ፖለቲካ ባይሆን ኖሮ፤ ሽፈራው ሚኒስትር መሆን አይደለም የሚኒስቴሩ መሥሪያቤት ጥበቃ የመሆን ብቃት የሌለው ሰው መሆኑን እመሰክራለሁ” ብለዋል።

ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ያስፈነጠረው መለስ ዜናዊ፤ የኢህአዴግን ዓላማ እስካስፈጸመ ድረስ መሃይምም ቢሆን በሚኒስትርነት እንሾማለን በማለት ይነዳው ለነበረው ፓርላማ መናገሩ ይታወሳል።

የሽፈራውን ሥልጣን መልቀቅ ተከትሎ በተመሳሳይ የህወሓት ሹመኞች ሥልጣናቸውን እንደሚለቁ የሚጠበቅ ሲሆን በተለይ ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመግደል ከተሞከረው ጋር በተያያዘ ከ“ቀን ጅቦቹ” መካከል ለፍርድ የሚቀርቡ እንደሚኖሩ ይጠበቃል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: abiy, eprdf, Full Width Top, Middle Column, resignation, shiferaw, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule