• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይትን መስዋዕት የሚያደርጉ የ”አማራ ነጻ አውጪዎች”

January 31, 2024 01:06 pm by Editor Leave a Comment

ከትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) ጋር አብሮ “የጠብ መንጃ ትግሉን ማጧጧፍ” በሚል ከውሳኔ የደረሱ ክፋይ የ”አማራ ነጻ አውጪ” ኃይሎች መኖራቸው ተሰማ። ለስምምነቱ ትሕነግ ምዕራብ ትግራይ የሚለውንና አሁን “ነጻ ወጥቷል” የሚባለውን ወልቃይት ተላልፎ እንዲሰጥ ፈቃደኝነት ያለበት እንደሆነ ተመልክቷል።

ራሳቸውን በተለያዩ አካባቢያዊና አደረጃጀት ከሰየሙት መካከል አሁን አንድ ለመሆን እየሠሩ እንደሆነ የሚነገርላቸው በዝናቡ የሚመራው የጎጃም ዕዝና የዘመነ ካሴ ኃይል ነው ይህን ስምምነት ለማድረግ እየሠራ እንደሆነ የተሰማው።

“ጊዜው አሁን ነው፤ ይህንን ጊዜ ልንጠቀምበት ይገባል” በሚል በገሃድ ወልቃይትን ዳግም በኃይል ለመያዝ ደብረጽዮን በቅርቡ መናገሩ ይታወሳል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከሕዝብ ጋር በተለያዩ ከተሞች ውይይት ያደረገው ጌታቸው ረዳም “እኛ ሥራችንን መሥራት ባለመቻላችን ነው እናንተ ተፈናቅላችሁ የምትሰቃዩት” ብሎ በትግራይ መናገሩ አይዘነጋም።

ዜናውን ለአዲስ አበባ የጎልጉል ዘጋቢ ያቀበሉ “ፋኖና ትሕነግ ልዩነታቸውን አስወግደው በአንድነት ብልጽግናን ማስወገድ አለባቸው” በሚል በውጭ አገር ባሉ አመራሮች አማካይነት ንግግር እንደነበር ያስታውሳሉ። ሙከራው ተግባራዊ ሊሆን ያልቻበትን መሠረታዊ ጉዳዮች ያስረዳሉ።

በአማራ ክልል ውስጥ ያለው የጠብመንጃ እንቅስቃሴ በኤርትራ የሚደገፍ መሆኑ ሻዕቢያ ከትሕነግ ጋር የሚፈጠር ማንኛውንም ጥምረት አለመፍቀዱና ወልቃይትን ከትሕነግ በላይ ሻዕቢያ ስለሚፈልገው፣ ከፋኖ ውስጥም ሆነ ከአማራ ልዩ ኃይል ከወጡት ውስጥ የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የሚያቀርቡ ስላሉ ንግግሩ ከምኞት አለመዝለሉን በዋናነት ይገልጻሉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ነው አዲሱ የማበር ዜና ሾልኮ የወጣው። ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ያገገመው ትሕነግ መንግሥትን በድርቅ፣ በተለያዩ ወንጀሎች፣ እንዲሁም በሰላማዊ ሰልፎች ጫና በማሳደር፣ ከአሜሪካ የምስራቅ አፍሪቃ አምባሳደር ሃመር ጋር ተከታታይ ግንኙነት እያደረገ ባለበት ወቅት ነው።

ዩኤስ ኤይድ (USAID) “የዕርዳታ ስንዴ ተሰርቋል” በሚል ያቋረጠውን እርዳታ ሲጀመር “ብቻዬን ልሥራ፣ አጠገቤ ድርሽ አትበሉ” ማለቱንና መንግሥት ይህ ዓለም ላይ በየትኛውም አገር የማይሠራበት አሠራር ኢትዮጵያ ላይ ብቻ ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሰሞኑንን በሁለት ከፍል ባሰራጩት የሥልጠና ቪዲዮ ላይ ማስታወቃቸውንም የዜናው ምንጭ ጉዳዩን እንደሚያጠነክረው ገልጸዋል።  

በአማራ ስም በተለያዩ የአካባቢና የአደረጃጀት ስም የሚጠሩት ነፍጥ አንጋቢዎች መከፋፈላቸው በኢትዮ360 ሳይቀር በይፋ እየተገለጸ ባለበት፣ እስከንድር ነጋ ከጎጃም ወደ ሸዋ እንዲሸሽ መደረጉ ከተሰማና በጎንደርና አካባቢው አሉ የሚባሉ አደረጃጀቶች አቋም ጠርቶ ባልወጣበት፣ በሸዋ ያለው ትግል በዕርስ በርስ ግጭት ላይ መሆኑንን ከስፍራው ታዛቢዎች ይፋ እያደረጉ፣ በደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ እና የእርሱ አለቃ የነበረው መከታው ማሞ ኃይሎች መካከል የነበረው አለመግባባት እያየለ ሄዶ በሰላ ድንጋይ አካባቢ ደም መፋሰሳቸው በተሰማበት ሰሞን፣ በወሎ ማዶ ደግሞ የመሪነት ማዕረግ ያስነሳው አለመግባባትና ከመንግሥት ጋር ስምምነት እያካሄዱ ያሉ ወገኖች መኖራቸውን ተከትሎ ነው የጎጃሙ ቡድን ከትሕነግ ጋር መነጋገር እንደጀመረ የተሰማው።   

ዜናውን ያሳበቁ እንደሚሉት ትሕነግ ዋና አጀንዳው ወልቃይት ነው። ወልቃይትን የማስመለስ አጀንዳው በየትኛውም ዘመን የሚታጠፍም አይደለም። ይህ ከሆነ ደግሞ ከትሕነግ ጋር ለማበር ወልቃይት ላይ ያለውን የትሕነግ አቋም መቀበል ወይም በተግባር “እንካችሁ” ማለት ግድ ነው።

ይህ ከትሕነግ ውልደት ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ጸንቶ የቆመው የወልቃይት ጉዳይ፣ “እንደፍጥርጥሩ” በሚል አብሮ ለመታገል ውሳኔ መነሻቸውን ጎጃም ያደረጉት ኃይሎች እየሠሩ ቢሆንም፣ ጉዳይ አማራውን ስለሚያስቆጣ እጅግ ሚስጢር ተደርጎ ተይዟል።

ቀደም ሲል ከኢትዮጵያ አሁን ከጀርመን የሚሰራጨው ኢትዮ ሚዲያ ፎረም የሚባለው የትሕነግ ልሳን ሰሞኑንን ባሰራጨው ዘገባ አውቆም ይሁን ሳያውቅ የአማራና የትህንግን ትግል የማቀናጀት ዕቅድ ቢኖርም፣ ሻዕቢያ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ወደተግባር የመሸጋገሩ ጉዳይ ለጊዜው እንደማይሆን በወፍ በረር ጠቆም አድርጎ ነበር።  

አሁን የድርድርና የሽምግልና ወሬ በሚናፈስበት ወቅት የሻለቃ ዳዊት የሚመራው ኃይልና ሀብታሙ አያሌው የሚመራው 360፣ አንዳርጋቸው ጽጌ የሚመራውና መሳይ መኮንን የከፈተው አንከር ሚዲያ በጋራ ለመሥራት ደፋ ቀና እያሉ እንደሆነ ነው።

ጉዳዩን የሚከታተሉ “ብዙ ጊዜ ተገዳድላችኋል፤ ለዜና ፍጆታ አይሆንም ብለን ይዘነው ነው” ሲል ሃብታሙ አያሌው ሰሞኑንን ዝናቡና ዘመነ ካሴ የሚመሩትን ኃይሎች መክሰሱ ራሱን ከነሱ የተለየ አዲስ ህብረት ጎጃምን ማዕከል አድርጎ መቋቋሙን ያረጋገጠ ሆኗል። ይህ ኃይል እስክንድርን ወደ ሸዋ ማባረሩ ይታወሳል።

ከኤርትራ አጀንዳና ፍላጎት አንጻር የሚቀኘው አንዳርጋቸው ጽጌ የሚመራው ኃይል፣ የጎጃሙን ኃይል ለመጠቅለል በርካታ ሙከራዎች አድርጎ እንደነበር የሚገልጹ እንዳሉት፣ በዝናቡ የሚመራዉ የጎጃም ዕዝ ፈቃደኛ አልሆነም። ከዚህ ሁሉ ፍትጊያ በኋላ አሁን እንደተሰማው ይህ የጎጃም ኃይል አዲስ ለጀመረው እንቅስቃሴ ይጠቅመው ዘንድ ምናላቸው ስማቸውን ከ360 በማስወጣት የሚዲያ ዘመቻ ለመጀመር ዝግጅቱን ጨርሷል።

ቀደም ሲል ጀምሮ የተወለደበት መንደሩን፣ የጎጃምና አካባቢውን መረጃ በማጠናከር የሚታወቀው ምናላቸው፣ “የጎጃም ፋኖ ዜና ለአንተ ብቻ ይሰጥሃል፣ መቋቋሚያ ገንዘብ ይለገስሃል፣ ጎፈንድሚ በስምህ ትከፍትና እዚያ በቂ ገንዘብ በመዋጮ ስም እንዲገባልህ ይደረጋል” በሚል አሜሪካ የሚኖሩ ባለአቅሞች ቃል እንደገቡለት ጎልጉል ጉዳዩን በቅርብ ከሚያውቁ ሰምቷል።

ከዚህ ቀደም ምናላቸው ኢሣትን ለቅቆ ከወጣ በኋላ በዘይት ነጋዴው ወርቁ አይተነው በኩል በየወሩ በኢትዮጵያ ብር ቋሚ ደመወዝ እየተከፈለው፣ በውጭ አገርም ድጋፍ እየተደረገለት የራሱን ግዮን ቲዩብ የተባለ ሚዲያ ከፍቶ እንደነበር አይዘነጋም። ኤርሚያ ለገሰ ከ360 በብሄር ምክንያት መባረሩን ጠቅሶ ሲለቅ ምናላቸው ወደ 360 መመለሱ አይዘነጋም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara region, debretsion, Eskinder Nega, getachew reda, operation dismantle tplf, tplf terrorist, wolkayit

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule