
የአፋር ክልል ልዩ ሀይል አባል የሆነው ሁመድ አሊ የአፋር ክልልን ለመውረር የመጡ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎችን ሲፋለም ጥይት በመጨረሱ በታጠቀው ጊሌ ታንክ የማረከ ጀግና ወጣት ነው!

ህጻናት የታቀፉ ወላጆችን በግፍ የረሸነው አሸባሪው የህወሓት ቡድን ህጻን አማን እና ወንድሞቹን ያለወላጅ አስቀርቷል።
ህጻና አማን በእናትና አባቱ አስከሬን መካከል በደም ተነክሮ ነው የተገኘው። የእናቱን ሞት አይቷል። የወላጅ እናቱን አስከሬን ታቅፎ ተገኝቷል። ይህ የጭካኔ ጥግ ሂሳብ እናወራርዳለን በሚል የአሸባሪው ቡድን አመራሮች ተናግረው በአማራ ክልል ወረራ ከፈጸሙ በኋላ የፈጸሙት የሽብር ተግባር ነው።

“ኢትዮጵያዊያን እያለን አሸባሪው ህወሓት እንጂ አገር አትፈርስም”፦ ዘማቹ ረዳት ፕሮፌሰር
የሕልውና ዘመቻ ጥሪውን ተቀብለው በግንባር የሚገኙት ረዳት ፕሮፌሰር ጌትነት አልማው “እኛ ኢትዮጵያዊያን እያለን አሸባሪው ህወሓት እንጂ ኢትዮጵያ አትፈርስም፤ ይህም በተግባር እየታየ ነው” ሲሉ ተናገሩ።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ረዳት ፕሮፌሰር ጌትነት አልማው አሸባሪውን ህወሓት ለመደምሰስ የቀረበውን የክተት ጥሪ ተቀብለው በማይፀብሪ ግንባር ተሰልፈዋል።
“ለአገር ሉዓላዊነት መከበር ኢትዮጵያዊ ሁሉ መታገል አለበት” የሚሉት ረዳት ፕሮፌሰሩ፣ “በግንባሩ እየተፋለምኩ ያለሁት የአገሬን ሉዓላዊነት ለማስከበር ነው” ሲሉ ለኢዜአ ገልጸዋል።
በተሰለፉበት ግንባር የመከላከያ ሠራዊቱ፣ የፀጥታ ኃይሎች እና የአካባቢው ሕዝብ በጠላት ላይ ድል እየተቀዳጁ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
መላው ሕዝብ በድል አድራጊነት መንፈስ ለአገር ሉዓላዊነት እና አንድነት በመዋደቅ ለግለሰቦች ሥልጣን ሲል ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተነሣውን አሸባሪ ቡድን በያለበት መታገል እንዳለበት አመልክተዋል።
አሸባሪው ህወሓት ትምህርት ቤቶችን፣ የጤና ተቋማት፣ ቤተ-እምነቶችን እና የሕዝብ መገልገያ መሠረተ ልማቶችን እያወደመና እየዘረፈ የሚገኘው አሸባሪው ቡድን የሚነዛውን የሐሰት ወሬ መከተል እንደማያስፈልግ አስገንዝበዋል።
“የኢትዮጵያ ሕዝብ ድል እያደረገ እንደሆነ መታወቅ አለበት” ያሉት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤ ሁሉም ዜጋ ባለው አቅም በግንባር በመገኘትና ደጀን በመሆን ለአገሩ ነፃነት የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያደርግም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቡድኑ ምንም የማያውቁ ህፃናትን ለጦርነት እያሰለፈ ለሞት እየዳረጋቸው እንደሆነም አክለዋል። (ኢብኮ)
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
ወያኔ ማለት አረመኔ ማለት ነው። እንኳን ሃሽሽ እያጨሰና አፍልቶ እየተጋተ እንዲሁም የእንስሳ ክምችት ነው። ያለ እኛ ላሳር ይሉን የነበሩት እነዚህ ሙታኖች ሰውና ሃገር ይዘው መሞታቸው ብቻ ነው የሚያሳዝነው። ያለ ልቡ ከመንገድ ላይ በወያኔ ካድሬዎች እየተጠለፈ ለጦርነት የሚማገደው የትግራይ ወጣት ያሳዝናል። ወያኔ ግፈኛ ነው በቅርቡ በጦር ሜዳ የለቀመውን አስከሬን በገመድና በሌላም ነገር ተብትቦ ወንዝ ላይ በመልቀቅ ለዓለም ህዝብ የዘር ማጥፋት እየተፈጸመብን ነው በማለት በሱዳን በኩል ገብታ ሁኔታውን በዘገበችው ጭፍን የCNN ጋዘጠኛን ሪፓርት ለተመለከተ ወያኔ በእዝ ሰንሰለቱ እንዴት አድርጎ ሰውንና መንግስታትን እያታለለ እንደሆነ ማየት ይችላል። ጋዜጠኛዋ አንድ እውነትነት ያለው ነገር ብቻ ተናግራለች። የሙታን መርማሪ የሆኑ ሰዎች በነገሩኝ መሰረቱ ሰዎቹ ከሞቱ ቆይቷል በማለት አላዝናለች። ይህ ሁኔታ ወያኔ ሬሳ አከማችቶ በሚመቸው ጊዜ ሬሳውን እያሰረ እንደለቀቀ ማጠናከሪያ መረጃ ነው። ወያኔ በቁም ሰው ብቻ ሳይሆን በሟችም የሚነግድ እኩይ ፍጡር ነው። በራሳቸው የሴራ ግድያ የሞተውን ጄ/ ሃያሎምን ሆለታ ላይ የነበረውን የጦር ት/ቤት በስሙ ሰይመውታል። በባህርዳር ራሳቸው የገደሉትን ሙለዓለምን የሙሉዓለም አዳራሽ መታሰቢያ አቁመውለታል። ብዙ ማለት ይቻላል።
አሁን እንሆ በወሎ በጎንደርና በአፋር ወረራ እየፈጸመና እየተደበደበ ያለው ወያኔ ያለ እኛ ወንድ፤ ያለ እኛ የጦር አውቂ በማለት ራሱን አሳምኖ በአዲስ አበባ ዳግም ራሱን ሚኒሊክ ቤተመንግስት ለማስጠልል ያልሞከረው ሴራ የለም። ግን አልተሳካም። ጄ/ባጫ ደበሌ እንደተናገሩት “ውጊያው በመንግስትና በሌቦች መካከል ነው”። ወያኔ በራያና ቆቦ በሌሎችም የወሎ ቦታዎች የሰራው ግፍ ጭራሽ አያቀባብርም። ያው ገጣሚው እንዳለውን ነው።
የታሪክ ሃገር ናት የፍቅር ከተማ
ወሎ አይወለድም ፈሪና ገገማ
ወያኔ ገገማ ነው። የወሎን ህዝብ ያለ ልቡ ለማንበርከክ ያደረገው ሙከራ ከሽፏል። በአፋር በኩል በአፋር ጀግኖች ድባቅ ተመትቷል። ጠባብ፤ ሰነፍ፤ የማይዋጋ፤ የሃገር እና የህዝብ ጠላት እየተባለ በወያኔ ካድሬዎች ዘንተ ዓለም የሚፈረጀው የአማራ ህዝብም በቃኝ ከአሁን ወዲያ በማለት በልዪ ልዪ መንገድ ተደራጅቶ ወያኔን መልሶ አፍንጫውን ሲያደማው እያየን እየሰማን ነው። ለዚህ መሰለኝ ዘፋኙ እንዲህ ያለው።
ጠባብ ነው እያሉ ሲንቁ ሲንቁ
ነፍጠኛ ነው ብለው ሲንቁ ሲንቁ
ወንድ ነን ባዪቹ በወንዶች አለቁ
ትህነግ የአማራን ህዝብ ገና ከጅምሩ ጀምሮ የትግራይ ህዝብ ጠላት ነው በማለት ፈርጆ አማራው ከቀረው ወገኑ ጋር አብሮ እንዳይኖር በየቦታው እሳት እያቀጣጠለ እያጫረሰን እንደነበርና እንዳለ ልብ ያለው ያስተውላል። እነዚህ አሪዎሶች ከራሳቸው ሆድ እቃ ውጭ ስለ ሌላው ሰው ጉዳት ደንታ የላቸውም። የደነዘዙ በድኖች ናቸው። ዛሬ በአሜሪካ የተጠለሉት አቶ ስዬ አብርሃ፤ የድሮው አምባሳደር ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ያሉት ሾተላዎች በሩቅ ሆነው በዚህና በዚያ ነገር እየተበተቡ የትግራይን ህዝብ እያስጨረሱ ናቸው። የእነርሱ ልጆችና ቤተሰቦች ግን በአሜሪካ የተደላደለ ህይወትና ኑሮ ከኢትዮጵያ በዘረፉት ሃብት እየኖሩ ይገኛሉ። ብርሃነ ገ/ክርስቶስ በብራስል አምባሳደር ሆኖ ሲሰራ የፈጸመው ግፍ መፈጠርን የሚያስጠላ ነው። ያ የኢትዮጵያ ቆንስላ የተባለው ቦታ ከላይ እስከ ታች በወያኔ ሰዎች የተሞላ ነበር። በሰውር የምዝበራ ብልሃት ይህ ሰው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር እየወጣ በተሰጠው ገንዘብ አዲስ አበባ ላይ የእምነ በረድ ደረጃ ያለው የተንጣለለ ቤት ሰርቷል። በአሜሪካ ከፈታት ሚስቱ ጋር የተካፈለው እልፍ ገንዘብ ዛሬ ለእርሱና ለእርሷ መጦሪያ እየሆነ ነው። እናውቃለን ያንድ ዲፕሎማት ደሞዝ ምን ያህል እንደነበረና አሁንም እንደሆነ። እነዚህ ናቸው ታዲያ ለትግራይ ህዝብ ገለ መሌ የሚሉን። የሩቅ ጡሩንበኞች። ለራስ ብቻ ኗሪዎች። ዛሬ ማንም የማይበግረው የትግራይ ጦር እያሉ ሲያሞካሹት የነበሩት ድንጋይና ድላ በያዘ ፋኖ ሲማረክ ምን ይሰማቸው ይሆን። ግፍ ቁርጠኞችን ይፈጥራል። የሆነው እንደዛ ነው። ወደ 50 ዓመት ለሚጠጉ ዘመናት አማራን ያሰቃያው ወያኔ ዋጋውን እያገኘ ነው። እኔ የሚገርመኝ እንገነጠላለን ሲሉ ነው። አርጎት ነው። ከማህል ሃገር ከአፋር፤ ከአማራ ከኦሮሞ ባጠቃላይ ከጠቅላላው የሃገሪቱ ዳር ድንበር ተሟጣችሁ ውጡና የናፈቃችሁትን ሃገር ሁኑ። ማን ይለማመጣቹሃል። ሃገር አፍራሽ እንደሆናችሁ እኮ ህዝቡ ገና ድሮ ገብቶታል። አፍናችሁ ይዛቹሁ አላናግር ብላችሁት እንጂ። በእናቱና በአባቱ ሬስ መካከል ከሞት የተረፈው ያ ህጻን ገና አድጎ ይፋረዳቹሃል። እናንተ ወራዶች፤ ከሰው ተራ የወጣችሁ አውሬዎች። ለዓለም ህዝብ ተራብን፤ የዘር ማጥፋት ተፈጸመብን እያላችሁ ግፍ ፈጻሚዎች። ፈጣሪን የማትፈሩ ጣረሞቶች። ከምድረገጽ ያጥፋችሁ። በቃኝ!