• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እየተስተዋለ – ለኢትዮ 360 ተንታኞች!

January 21, 2020 06:23 am by Editor Leave a Comment

አምስተርዳም (በቪቫ ምኒልክ)

ለዛሬው ጽሁፌ መነሻ የሆነኝ በኢትዮ 360 በሰሞኑ የኢትዮጵያን መከላከያና ደህንነት ክፍል አስመልክቶ የቀረበው ውይይት እጅግ ስለ አስደነገጠኝ ነው።

ከውይይት ጭብጥ እንደተረዳሁትም ከመከላከያና የደህንነት መስሪያቤት ከፍተኛ አመራሮች በደረሰን መረጃ መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አገራችንን ለአረቦች አሳልፎ በመስጠት የእስልምና ሐገራት አባል ለማድረግ እየሰራ ነው የሚልና የምእራብ እዝን ወደ ወለጋ ያዛወረው የኦሮሞን ልዩ ሃይል ለማደራጀት እንዲመቸው ነዉ የሚል በጥላቻ ላይ ብቻ የተመሰረተው ክሳችሁን መሉ ለሙሉ የምቃውምበትን ነጥብ ከዚህ በታች በአጭሩ ዘርዝር አድርጌ ለማስተላለፍ እሞክራለሁ።

የውይይት ሃሳባችሁ መነሻ ያደረጋችሁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ከሰይፉ ጋር ያደረጉት ዉይይት ላይ ስለ አረብ አገራት ለኢትዮጵያ በሚሰጡት የገንዘብ ድጋፍ አስከትሎ የሰጡት አስተያየትን ቀደም ብለን መረጃው በእጃችን (በEthio 360) መግባቱን በመረዳታቸው ለመከላከል ያቀዱት መንገድ ነዉ የሚል ነጥብ አንስታችኋል። በዚህ ጉዳይ ለኔ ግልፅ ሆኖ የታየኝ በገና በዓል ምክንያት ረዳት ለሌላቸው አዛውንትና ህፃናት በአደረጉት የምሳ ግብዣ ላይ እነዚህ አዛውንትና ህፃናት በቋሚነት ህብረተሰብ ግንዛቤ አግኝቶ ድጋፍ እንዲያደርግ ሚድያው ከፍተኛውን ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ ብለው ስለገመቱ፤ ከነዚህ ውስጥ አንዱ የሆነውን ጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁንን ጋበዙ። ጋዜጠኛው ካነሳው ጥያቄ ተመርኩዞ የሰጡት መልስ ከሳቸውም በፊት አረቦቹ ከኢህአዲግ ጋር ተቀራርበው ይሰሩ እንደነበር ገልጸዋል። ሌላው ቀርቶ የብሔራዊ ደህንነት ቢሮ (ህንፃ) ግንባታን የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውንና በሳቸው አመራር ግዜም ይበልጥ መቀራረብና መግባባት እንዳላቸው ተናግረዋል። ይህንንም ግንኙነት የነሱን ፍላጎት በጠበቀና እኔም የሃገሬን ብሔራዊ መብት በማይነካ ደረጃ እየጠበቁ እንደሚያጠናክሩት በግልፅ አስረድተዋል።

ኢትዮ 360 ግን እነሱ የሚሰማቸውን ብሔራዊ ስሜት ያህል ሀገሪቱን የሚመሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማይሰማቸው ናቸው ብሎ በድፍረት መናገራችሁ ለምን ዓላማ ልትጠቀሙበት እንድፈለጋችሁ በግልፅ ሊገባኝ ባይችልም አጀንዳው ወያኔ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ከሚያቀርበው ክስ ጋር ተቀራራቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ።

ወያኔ ወደ ሥልጣን ለመመለስ ብዙ ቀውስ እየፈጠረ በሚገኝበት ሰዓት ላይ የመጨረሻ አጀንዳው አድርጎ ሊጠቅምበት የሚፈልገው ጉዳይ የመከላከያና የደህንነት ክፍሉን ለመበታተን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ላይ ወድቋል በሚል የጀመረውን ቅስቀሳ በሚደግፍ መልኩ እናንተ የምታደርጉት ተደጋጋሚ ዘገባዎችና ውይይቶች ከወያኔ ባልተናነሰ ደረጃ በየቀኑ በጠቅላይ ሚንስትሩ ላይ የምታደርጉት ከመስመር የወጣ ትችትና ዘለፋ ሚዲያችሁ ነፃና ገለልተኛ ነው ብዬ ለማመን እቸገራለሁ።

ከሃገሬ በብዙ ሺህ ማይል የራኩና ከሃገሬም ከወጣሁ ሩብ ክፍለ ዘመን ያስቆጠርኩ እንደ መሆኔ አፌን ሞልቼ በትውልድ እናት ሃገሬ ውስጥ በየቀኑ ስለሚካሄደው ሁኔታ በቂ መረጃ አለኝ ብዬ ባላምንም አሁን በሃገራችን የሚካሄደውን ለማወቅ ግን ዘመኑ የደረሰበት የመረጃ ፍሰት መረጃን ለማግኝትም ሆነ እውነተኛውን አጣርቶ ለማወቅ ብዙ አስቸጋሪ ሆኖ አላገኘሁትም ስለዚህ ነው ኢትዮ 360 የተሳሳተ መረጃ ከማስተላለፍ ልትቆጠቡ ይገባል የምለው።

ከውይይታችሁ ዉስጥ እንደተደመጠው የምዕራብ እዝን ወደ ወለጋ የወሰደው የኦሮሚያ ልዩ ሃይልን ለማጠናከርና የኢትዮጵያ መከላከያ ለማዳከም ነዉ የሚል ክስ አቅርባችኋል። የኢትዮጵያ መከላከያ የምድር ጦር እደረጃጀት በእዝ የተከፋፈልና አስፋፈሩም በግልፅ የሚታወቅ መሆኑም ለማንም ማወቅ ለሚፈልግ አስቸጋሪ ያለመሆኑ እየታወቀና የምእራብ እዝ ወደ ወለጋ ለግዳጅ መንቀሳቀስ በየቀኑ በየሚዲያው በግልፅ እየተነገረ፣ እናንተ ለምን ትርጉም ልትሰጡት እንደፈለጋችሁ ለኔ አልገባኝም?

ወያኔ ላለፉት ሃያ ሰባት አመት ኢትዮጵያ አገራችንን ምን አይነት አዘቅት ዉስጥ ከቷት እንደሄደና የመቶ ዓመት የቤት ሥራ ሰጥቻችዃለሁ ብሎ እየተመፃደቀ በሚገኝበት በአሁኑ ሰአት፣ ወያኔ በአደራጀው የአፓርታይድ የዘር አከላለልና አንዱ በእንዱ ላይ እንዲነሳሳ በረጨው የጥላቻ ፖለቲካ በተለያየ የሃገራችን ቦታዎች ዜጎች የመኖርና ወጥቶ የመግባት ዋስትና አጥተው ህይወት እንደ ቅጠል እየረገፈ በየቦታው እየተፈናቀሉ በምንሰማበት ሁኔታ ይህን ችግር ለማስወገድ የሚቻለውን ሁሉ በማደረግ ላይ የሚገኘውን መንግሥት ብዙ ማጣጣልና እንዲዳከም ብሎም እንዲወድቅ ከወያኔና ዘረኛ ከሆኑ ሃይሎች ጋር በግልም ሆነ በተዘዋዋሪ መተባበር ኢትዮጵያን እንደማፍረስ ይቆጠራል።

ካቀረባችሁት ከፍተኛ ክስ ዋናው ሊሰመርበት የሚገባው ተወዳጁ የኢትዮጵያ መከላከያ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ሰዓረ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሃገሪቱን ደህንነትና መከላከያ ተቋም በውጭ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት አስደፍረዋል በሚል በመቃወሙ ከቦታው ሊነሳ ጥያቄ አቅርቦ እንደነበረ ወይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሊያነሱት ነበር በመሀል ተገደለ። ከግድያው ጀርባም የሳቸው እጅ አለበት የሚል ጥርጣሬ እንዳላችሁ፤ አሁንም ይህንን ጣልቃ ገብነት የሚቃወሙት ከፍተኛ ጀኔራል መኮንንኖች ይህው ግድያ እንዳይደርስባችው ስጋት እንዳላችሁ የገለፃችሁበት መንገድ ምንም አይነት የማጣራትና የመመርመር በተጨባጭ ማስረጃ ላይ የተመረኮዘ የጋዜጠኝነት ሥራ ሳትሰሩ በነፍሰ ገዳይነት መፈረጅ እናንተን በግልፅ የወያኔ መንገድ ተባባሪ ናችሁ ለማለት ያስችላል ።

እውነታው ግን እኔ እንደተረዳሁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ከሚደነቁበት ዋንኛው ነጥብ በአብላጫው በወያኔ ትግራይ የበላይነት የተያዘውን የመከላከያና የደህንነት ተቋም በፍጥነት ማሻሻያ (Reform) ማድረጋቸው ነው። ለዚህም ተግባር ተባባሪ ከነበሩት ውስጥ በግንባር የሚጠቀሱት ጀነራል ሰአረ መኮንን ሲሆኑ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የለውጥ እንቅስቃሴ አጋርና ለኢትዮጵያ ህዝብ ታማኝ በመሆን ህይወታቸው እስካለፈ ድረስ በሃቅ አግልግለዋል። እኝህን የመሰለ ታማኝ ጀነራላቸውን ነው ዓብይ እውን አስገደለው የምትሉን?

በኔ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ሃገሬቱን ላለፉት ሁለት አመታት መምራት ከጀመሩበት ግዜ እስካሁን ብዙ ሊመስገኑም ሊወቀሱበት የሚችል ብዙ ዝርዝር ሁኔታዎች ቢኖሩም አሁን ምርጫ ሊቃረብ ጥቂት ወራት ሲቀረው ይህን ሁሉ አፍራሽና ሚዛናዊነት የጎደለው ፕሮፓጋንዳ ማድረግ ለሐገራችንና ለህዝባችን ምን ጥቅም እንድ ሚሰጥ ፍርዱን ለአንባቤና አድማጭ እየተውኩ፣ ሃገሬ መቼ ይሆን በሙያው የተካነ አድሎአዊ ያልሆን ለአንድ በድን ወይም ብሔር ያልወገነ በጋዜጠኝነት ሙያና ስነ ምግባር ያለው ጀግና ጋዜጠኛ የሚወጣላት እያልኩ ላለፉት ፪ ዓመታት ከመቼውም ግዜ በበለጠ ዝምታ የመረጥኩበት ሁኔታ ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመን በስደት የትግል ሕይወቴ ብዙ ነገር ያሳየኝና ያስተማርኝ ቢሆንም እንዳለፉት ፪ ዓመታት እጅግ የሚገርምና አይን ያወጣ እናውቅልሃለን ባይ የበዛብት ግዜ ላይ በመድረሴ ዝም ብሎ ማዳመጥ የተሻለ መሆኑን በማመኔን ነበር።

እጅግ የምወዳትና ከፍተኛ የአካል መስዋእትነት የከፈልኩባት እናት ሐገሬ ዛሬ ባለችበት ከፍተኛ ስጋትና ተስፋ ውስጥ ከእግዚአብሔር በታች የሐገሬን ህዝብ ብቸኛ ዋስትና በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ጠቅላይ አዛዥነት የሚመራው የሃገር መከላከያና የድህንነት ሃይል ብቻ ነው ብዬ እኔ አምናለሁ። ቢያንስ ትክክለኛ ምርጫ ተካሂዶ በህዝብ ድምፅ የሚመረጥ መንግሥት ሃላፊነትን እስኪረከብ ድረስ ትእግስት ይኑረን እያልኩ ለዛሬው ሃሳቤን በዚሁ አጠቃልላለሁ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: Ethio 360, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule