• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሰላምን ከጦርነት፣ መፍረስን ካለመፍረስ የሚለይ ቀይ መስመር የለም!

November 14, 2019 09:37 pm by Editor Leave a Comment

በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር)

“እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” አለ፣ አንድ ታዋቂ የየመን ጋዜጠኛ፤ በአንድ ቃለመጠይቁ ላይ። ነገሮች የረዥም፣ ተከታታይ ሂደት ውጤት ወይም መጨረሻ ናቸው፤ የድንገቴ ክስተት አይደሉም። ጦርነት ያለመግባባትና የቅራኔ ሂደት ውጤት ነው። ሞት ከጤንነት ጀምሮ፣ እየጠነከረ የሚሄድ ህመም ሒደት ውጤት ነው። በሥርዓትና ደንብ የቆመ ሀገር መፍረስም እንዲሁ የረዥም ጊዜ፣ ተከታታይ ከሥርዓትና ደንብ ማፈንገጥ ሒደት ውጤት ነው።

የሀገር መሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች . . . ሁላችንም፣ “ኢትዮጵያ አትፈርስም” እያልን እንጮሀለን። ከጩኸቱ ጀርባ የቻሉትን እያደረጉ ያሉት ግን የሀይማኖት አባቶች ብቻ ናቸው፤ ዕንባቸውን ሽቅብ ወደ ፈጣሪ መንበር እየረጩ የመንፈስ ልጆቻቸውን ይለምናሉ፤ ምእመኑን በጸሎትና በጾም ያተጋሉ። ፖለቲከኞች እዚህ ግባ የሚባል አቅም የላቸውም፤ አብዛኞቹ ያላቸውን ትንሽ አቅም ፓርቲያቸውን በምርጫ ቦርድ አስመዝግበው፣ በመጪው ምርጫ መሳተፍ ይችሉ ዘንድ እየተጠቀሙበት ነው። የሀገርንና የዜጎችን ጉልበትና ሀላፊነት ጠቅልሎ የተሸከመው መንግሥት፣ በየአካባቢው ለሚታየው የዜጎችን ህይወትና ንብረት፣ እንዲሁም በሰላም ወጥቶ የመግባት ተግዳሮት ለመቆጣጠርና “አትፈርስም!” የሚላት ሀገር እንዳትፈርስ ለማድረግ የሚያስችል እርምጃ እየወሰደ አይደለም፤ እየተከተለ ያለው አዲስ መንገድ እንደ ሰበካና ልመና እየተወሰደ ነው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ሰበካና ልመና የሚሰማ ቢሆን ኖሮ፣ በአለም የሚኖሩ ጻድቃኖች ነፍስ ወደ ሰማይ አትሰደድም ነበር፤ ሀገራችን የጻድቃኖች ማረፊያ ምድራዊ ገነት በሆነች ነበር። አይሰማም!

ሁላችንም አንድ ልብ ያላልነው ጉዳይ አለ። ይኸውም፣ በፈረሰ ሀገር ውስጥ የተፈፀመና እኛ ሀገር ያልተፈፀመ የሰብአዊ መብት በደል ምን አለ? ሞት! በየአይነቱ፣ በሚዘገንን መንገድ ተፈፀሟል፤ ዝርፊያ! ባንኮች ጭምር ተዘርፈዋል፤ ሀብታሞች ሰርተው ያፈሩትን፣ ድሆች ጾም አድረው የቋጠሩትን አይናቸው እያየ ተዘርፈዋል። ማፈናቀል! የዚህ ተጠቂዎች በሚሊየን እስከመቆጠር ደርሰው ነበር፤ አሁንም በሺዎች ይቆጠራሉ። የሀይማኖት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች ተቃጥለዋል፤ . . . ምን ያልተደረገ ቀረ!?

መፍረስን እየተለማመድነው ነው። ስናስባቸው ያቅለሸልሹንና ያስመልሱን፣ እንቅልፍ ለቀናት ይነሱን የነበሩ አስነዋሪ ተግባራት፣ እንደየልብ ባልንጀራ በየቀኑ የምናገኛቸው ተግባራት እየሆኑ፣ እየተለማመድናቸው ነው። አሁን እንደ ሀገር ከመፍረስ ጋር ያለን ርቀት የቁጥርና የድግግሞሽ ጉዳይ ብቻ ነው። ለመሆኑ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ስንት ሲሆን ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? ስንት የሀይማኖት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ሲቃጠሉ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? መንገድ ተዘግቶ ስንት ቀን ሰዎች በወጡበት ሲያድሩ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? ስንት ዩኒቨርሲቲዎች የግጭት ማዕከል ሆነው ሲዘጉ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? . . . በአጠቃላይ ስንት ክልል፣ ስንት ከተማ፣ ስንት መንደር፣ ስንት ጎጆ ነው የሀገር መፍረስ ማረጋገጫ!? ለዚህ ነው የመናዊው ጋዜጠኛ፣ “እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” ያለው።

መንግሥት ህግና ሥርዓትን ማስከበር እንዳለበት የሚያምን ከሆነ፣ ጊዜው አሁን ነው። የኢህአዴግ ውህደት በጎ ተስፋ ቢሆንም፣ ትልቅ ችግር ይዞ እንደሚመጣ ምልክቱ እየታየ ነው፤ የኢህአዴግ ውህደት በአዳራሽ ውስጥ፣ በሥራ አስፈጻሚዎች ውይይት ሳይሆን፣ ከአዳራሹ ውጪ ባለው ሰላም፣ የህግና የሥርዓት መከበር ነው እውን ሊሆን የሚችለው።

ህግ፣ መንግሥት መንበረ ሥልጣኑን ሲቀበል የሚረከበው ሀገርና ዜጋን ማስተዳደሪያ መሣሪያ ነው። መንግሥት ከዜጎች ጋር የተቆራኘበት ገመድ ነው – ህግ። ህግን የማያስከብር መንግሥት ዜጎችን ከጥቃት ሊከላከል አይችልም። ህግን ካላስከበረ፣ ዜጎቹ ከመንግስት ይልቅ ህግ በሚጥሰው፣ ግፍ በሚፈጽመው ላይ ለመተማመን ይገደዳሉ (አብዛኛውን ጊዜ እምነት ከፍርሀት እንደሚመነጭ ልብ ይሏል)። . . . መንግሥት ህግን ማስከበር አለበት። ለዚህ ደግሞ ጊዜው አሁን ነው።

(ፎቶ፤ የሰንዓ አሮጌ ከተማ በቦምብ ጥቃት ከፈራረሰ በኋላ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: jawar massacre, Right Column - Primary Sidebar, sanaa, tplf, yemen

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule