• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሰላምን ከጦርነት፣ መፍረስን ካለመፍረስ የሚለይ ቀይ መስመር የለም!

November 14, 2019 09:37 pm by Editor Leave a Comment

በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር)

“እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” አለ፣ አንድ ታዋቂ የየመን ጋዜጠኛ፤ በአንድ ቃለመጠይቁ ላይ። ነገሮች የረዥም፣ ተከታታይ ሂደት ውጤት ወይም መጨረሻ ናቸው፤ የድንገቴ ክስተት አይደሉም። ጦርነት ያለመግባባትና የቅራኔ ሂደት ውጤት ነው። ሞት ከጤንነት ጀምሮ፣ እየጠነከረ የሚሄድ ህመም ሒደት ውጤት ነው። በሥርዓትና ደንብ የቆመ ሀገር መፍረስም እንዲሁ የረዥም ጊዜ፣ ተከታታይ ከሥርዓትና ደንብ ማፈንገጥ ሒደት ውጤት ነው።

የሀገር መሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች . . . ሁላችንም፣ “ኢትዮጵያ አትፈርስም” እያልን እንጮሀለን። ከጩኸቱ ጀርባ የቻሉትን እያደረጉ ያሉት ግን የሀይማኖት አባቶች ብቻ ናቸው፤ ዕንባቸውን ሽቅብ ወደ ፈጣሪ መንበር እየረጩ የመንፈስ ልጆቻቸውን ይለምናሉ፤ ምእመኑን በጸሎትና በጾም ያተጋሉ። ፖለቲከኞች እዚህ ግባ የሚባል አቅም የላቸውም፤ አብዛኞቹ ያላቸውን ትንሽ አቅም ፓርቲያቸውን በምርጫ ቦርድ አስመዝግበው፣ በመጪው ምርጫ መሳተፍ ይችሉ ዘንድ እየተጠቀሙበት ነው። የሀገርንና የዜጎችን ጉልበትና ሀላፊነት ጠቅልሎ የተሸከመው መንግሥት፣ በየአካባቢው ለሚታየው የዜጎችን ህይወትና ንብረት፣ እንዲሁም በሰላም ወጥቶ የመግባት ተግዳሮት ለመቆጣጠርና “አትፈርስም!” የሚላት ሀገር እንዳትፈርስ ለማድረግ የሚያስችል እርምጃ እየወሰደ አይደለም፤ እየተከተለ ያለው አዲስ መንገድ እንደ ሰበካና ልመና እየተወሰደ ነው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ሰበካና ልመና የሚሰማ ቢሆን ኖሮ፣ በአለም የሚኖሩ ጻድቃኖች ነፍስ ወደ ሰማይ አትሰደድም ነበር፤ ሀገራችን የጻድቃኖች ማረፊያ ምድራዊ ገነት በሆነች ነበር። አይሰማም!

ሁላችንም አንድ ልብ ያላልነው ጉዳይ አለ። ይኸውም፣ በፈረሰ ሀገር ውስጥ የተፈፀመና እኛ ሀገር ያልተፈፀመ የሰብአዊ መብት በደል ምን አለ? ሞት! በየአይነቱ፣ በሚዘገንን መንገድ ተፈፀሟል፤ ዝርፊያ! ባንኮች ጭምር ተዘርፈዋል፤ ሀብታሞች ሰርተው ያፈሩትን፣ ድሆች ጾም አድረው የቋጠሩትን አይናቸው እያየ ተዘርፈዋል። ማፈናቀል! የዚህ ተጠቂዎች በሚሊየን እስከመቆጠር ደርሰው ነበር፤ አሁንም በሺዎች ይቆጠራሉ። የሀይማኖት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች ተቃጥለዋል፤ . . . ምን ያልተደረገ ቀረ!?

መፍረስን እየተለማመድነው ነው። ስናስባቸው ያቅለሸልሹንና ያስመልሱን፣ እንቅልፍ ለቀናት ይነሱን የነበሩ አስነዋሪ ተግባራት፣ እንደየልብ ባልንጀራ በየቀኑ የምናገኛቸው ተግባራት እየሆኑ፣ እየተለማመድናቸው ነው። አሁን እንደ ሀገር ከመፍረስ ጋር ያለን ርቀት የቁጥርና የድግግሞሽ ጉዳይ ብቻ ነው። ለመሆኑ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ስንት ሲሆን ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? ስንት የሀይማኖት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ሲቃጠሉ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? መንገድ ተዘግቶ ስንት ቀን ሰዎች በወጡበት ሲያድሩ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? ስንት ዩኒቨርሲቲዎች የግጭት ማዕከል ሆነው ሲዘጉ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? . . . በአጠቃላይ ስንት ክልል፣ ስንት ከተማ፣ ስንት መንደር፣ ስንት ጎጆ ነው የሀገር መፍረስ ማረጋገጫ!? ለዚህ ነው የመናዊው ጋዜጠኛ፣ “እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” ያለው።

መንግሥት ህግና ሥርዓትን ማስከበር እንዳለበት የሚያምን ከሆነ፣ ጊዜው አሁን ነው። የኢህአዴግ ውህደት በጎ ተስፋ ቢሆንም፣ ትልቅ ችግር ይዞ እንደሚመጣ ምልክቱ እየታየ ነው፤ የኢህአዴግ ውህደት በአዳራሽ ውስጥ፣ በሥራ አስፈጻሚዎች ውይይት ሳይሆን፣ ከአዳራሹ ውጪ ባለው ሰላም፣ የህግና የሥርዓት መከበር ነው እውን ሊሆን የሚችለው።

ህግ፣ መንግሥት መንበረ ሥልጣኑን ሲቀበል የሚረከበው ሀገርና ዜጋን ማስተዳደሪያ መሣሪያ ነው። መንግሥት ከዜጎች ጋር የተቆራኘበት ገመድ ነው – ህግ። ህግን የማያስከብር መንግሥት ዜጎችን ከጥቃት ሊከላከል አይችልም። ህግን ካላስከበረ፣ ዜጎቹ ከመንግስት ይልቅ ህግ በሚጥሰው፣ ግፍ በሚፈጽመው ላይ ለመተማመን ይገደዳሉ (አብዛኛውን ጊዜ እምነት ከፍርሀት እንደሚመነጭ ልብ ይሏል)። . . . መንግሥት ህግን ማስከበር አለበት። ለዚህ ደግሞ ጊዜው አሁን ነው።

(ፎቶ፤ የሰንዓ አሮጌ ከተማ በቦምብ ጥቃት ከፈራረሰ በኋላ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: jawar massacre, Right Column - Primary Sidebar, sanaa, tplf, yemen

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule