• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሰላምን ከጦርነት፣ መፍረስን ካለመፍረስ የሚለይ ቀይ መስመር የለም!

November 14, 2019 09:37 pm by Editor Leave a Comment

በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር)

“እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” አለ፣ አንድ ታዋቂ የየመን ጋዜጠኛ፤ በአንድ ቃለመጠይቁ ላይ። ነገሮች የረዥም፣ ተከታታይ ሂደት ውጤት ወይም መጨረሻ ናቸው፤ የድንገቴ ክስተት አይደሉም። ጦርነት ያለመግባባትና የቅራኔ ሂደት ውጤት ነው። ሞት ከጤንነት ጀምሮ፣ እየጠነከረ የሚሄድ ህመም ሒደት ውጤት ነው። በሥርዓትና ደንብ የቆመ ሀገር መፍረስም እንዲሁ የረዥም ጊዜ፣ ተከታታይ ከሥርዓትና ደንብ ማፈንገጥ ሒደት ውጤት ነው።

የሀገር መሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች . . . ሁላችንም፣ “ኢትዮጵያ አትፈርስም” እያልን እንጮሀለን። ከጩኸቱ ጀርባ የቻሉትን እያደረጉ ያሉት ግን የሀይማኖት አባቶች ብቻ ናቸው፤ ዕንባቸውን ሽቅብ ወደ ፈጣሪ መንበር እየረጩ የመንፈስ ልጆቻቸውን ይለምናሉ፤ ምእመኑን በጸሎትና በጾም ያተጋሉ። ፖለቲከኞች እዚህ ግባ የሚባል አቅም የላቸውም፤ አብዛኞቹ ያላቸውን ትንሽ አቅም ፓርቲያቸውን በምርጫ ቦርድ አስመዝግበው፣ በመጪው ምርጫ መሳተፍ ይችሉ ዘንድ እየተጠቀሙበት ነው። የሀገርንና የዜጎችን ጉልበትና ሀላፊነት ጠቅልሎ የተሸከመው መንግሥት፣ በየአካባቢው ለሚታየው የዜጎችን ህይወትና ንብረት፣ እንዲሁም በሰላም ወጥቶ የመግባት ተግዳሮት ለመቆጣጠርና “አትፈርስም!” የሚላት ሀገር እንዳትፈርስ ለማድረግ የሚያስችል እርምጃ እየወሰደ አይደለም፤ እየተከተለ ያለው አዲስ መንገድ እንደ ሰበካና ልመና እየተወሰደ ነው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ሰበካና ልመና የሚሰማ ቢሆን ኖሮ፣ በአለም የሚኖሩ ጻድቃኖች ነፍስ ወደ ሰማይ አትሰደድም ነበር፤ ሀገራችን የጻድቃኖች ማረፊያ ምድራዊ ገነት በሆነች ነበር። አይሰማም!

ሁላችንም አንድ ልብ ያላልነው ጉዳይ አለ። ይኸውም፣ በፈረሰ ሀገር ውስጥ የተፈፀመና እኛ ሀገር ያልተፈፀመ የሰብአዊ መብት በደል ምን አለ? ሞት! በየአይነቱ፣ በሚዘገንን መንገድ ተፈፀሟል፤ ዝርፊያ! ባንኮች ጭምር ተዘርፈዋል፤ ሀብታሞች ሰርተው ያፈሩትን፣ ድሆች ጾም አድረው የቋጠሩትን አይናቸው እያየ ተዘርፈዋል። ማፈናቀል! የዚህ ተጠቂዎች በሚሊየን እስከመቆጠር ደርሰው ነበር፤ አሁንም በሺዎች ይቆጠራሉ። የሀይማኖት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች ተቃጥለዋል፤ . . . ምን ያልተደረገ ቀረ!?

መፍረስን እየተለማመድነው ነው። ስናስባቸው ያቅለሸልሹንና ያስመልሱን፣ እንቅልፍ ለቀናት ይነሱን የነበሩ አስነዋሪ ተግባራት፣ እንደየልብ ባልንጀራ በየቀኑ የምናገኛቸው ተግባራት እየሆኑ፣ እየተለማመድናቸው ነው። አሁን እንደ ሀገር ከመፍረስ ጋር ያለን ርቀት የቁጥርና የድግግሞሽ ጉዳይ ብቻ ነው። ለመሆኑ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ስንት ሲሆን ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? ስንት የሀይማኖት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ሲቃጠሉ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? መንገድ ተዘግቶ ስንት ቀን ሰዎች በወጡበት ሲያድሩ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? ስንት ዩኒቨርሲቲዎች የግጭት ማዕከል ሆነው ሲዘጉ ነው ሀገር ፈረሰች የሚባለው? . . . በአጠቃላይ ስንት ክልል፣ ስንት ከተማ፣ ስንት መንደር፣ ስንት ጎጆ ነው የሀገር መፍረስ ማረጋገጫ!? ለዚህ ነው የመናዊው ጋዜጠኛ፣ “እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” ያለው።

መንግሥት ህግና ሥርዓትን ማስከበር እንዳለበት የሚያምን ከሆነ፣ ጊዜው አሁን ነው። የኢህአዴግ ውህደት በጎ ተስፋ ቢሆንም፣ ትልቅ ችግር ይዞ እንደሚመጣ ምልክቱ እየታየ ነው፤ የኢህአዴግ ውህደት በአዳራሽ ውስጥ፣ በሥራ አስፈጻሚዎች ውይይት ሳይሆን፣ ከአዳራሹ ውጪ ባለው ሰላም፣ የህግና የሥርዓት መከበር ነው እውን ሊሆን የሚችለው።

ህግ፣ መንግሥት መንበረ ሥልጣኑን ሲቀበል የሚረከበው ሀገርና ዜጋን ማስተዳደሪያ መሣሪያ ነው። መንግሥት ከዜጎች ጋር የተቆራኘበት ገመድ ነው – ህግ። ህግን የማያስከብር መንግሥት ዜጎችን ከጥቃት ሊከላከል አይችልም። ህግን ካላስከበረ፣ ዜጎቹ ከመንግስት ይልቅ ህግ በሚጥሰው፣ ግፍ በሚፈጽመው ላይ ለመተማመን ይገደዳሉ (አብዛኛውን ጊዜ እምነት ከፍርሀት እንደሚመነጭ ልብ ይሏል)። . . . መንግሥት ህግን ማስከበር አለበት። ለዚህ ደግሞ ጊዜው አሁን ነው።

(ፎቶ፤ የሰንዓ አሮጌ ከተማ በቦምብ ጥቃት ከፈራረሰ በኋላ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: jawar massacre, Right Column - Primary Sidebar, sanaa, tplf, yemen

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule