• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሳውዲ እስር ቤት ሦስት ኢትዮጵያውያን መሞታቸውን አምነስቲ ይፋ አደረገ

October 2, 2020 02:48 pm by Editor Leave a Comment

በሳዑዲ አረቢያ እስር ቤት ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ስደተኞች አያያዝ በተመለከተ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባካሄደው ምርመራ አዳዲስና አሰቃቂ ዝርዝር መረጃ ማግኘቱን አስታወቀ።

ድርጅቱ እንዳለው በዚህም ሳቢያ የስደተኞቹ ህይወት አደጋ ላይ መሆኑን አመልክቶ ሦስት ኢትዮጵያዊያን መሞታቸውን በእስር ቤቶቹ ካሉ ስደተኞች ማረጋገጡን ስለሁኔታው ባወጣው መግለጫ ጠቅሰወል።

የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቱ ጨምሮም የሳዑዲ መንግሥት ስደተኞቹ ያሉበት አደገኛ ሁኔታ እንዲያሻሽል እንዲሁም ነጻ እንዲወጡ የጠየቀ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም የስደተኞቹ አያያዝ እንዲስተካከል ግፊት እንዲያደርግና ፈቃደኛ የሆኑትም ወደአገራቸው እንዲመለሱ የሚደረግበትን መንገድ እንዲፈልግ ጠይቋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በስደተኛ ማቆያ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ጉዳይ ሪፖርቶች ከመውጣታቸው ቀደም ብሎ ጀምሮ እየተከታተለ እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ የሆኑት ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ ለቢቢሲ ገልጸው፤ በተጨማሪም ያሉበትን አሳሳቢ ሁኔታ የሚገልጹ ሪፖርቶች በሚወጡ ጊዜም ጉዳዩን ለሳዑዲ ባለስልጣናት በማሳወቅ ደኅንነታቸው እንዲጠበቅ ከመጠየቅ ተቆጥበው እንደማያውቁ ተናግረዋል።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል እንዳለው ከባለፈው ዓመት ጀምሮ የየመን አማጺያን በሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊን ስደተኞችን፣ ከየመን አስወጥተው በማባረራቸው ወደ ሳዑዲ አረቢያ ገብተው ለሕይወት አስጊ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ገልጿል።

አምነስቲ ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን እንደተናገሩት ለሁለት ሆነው በሰንሰለት መታሰር፣ በታሰሩበት ክፍል ውስጥ እንዲጸዳዱ መደረግ፣ ለ24 ሰዓታት በተጨናነቀ ክፍል ውስጥ እንዲሆኑ ማድረግን ጨምሮ በሳዑዲ እስር ቤቶች ውስጥ የመከራ ሕይወትን እየመሩ ነው።

የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቱ ከተለያዩ ታሳሪዎች ያገኘውን መረጃ መሰረት በማድረግ እንዳመለከተው በእስር ቤቱ ውስጥ የሦስት ሰዎች ሕይወት አልፏል። በተጨማሪም በገለልተኛ ሁኔታ ለማረጋገጥ አልቻልኩም ያላቸው ቢያንስ የአራት ኢትዮጵያውያንን ሞት መስማቱን አመልክቷል።

በእስር ቤቱ ውስጥ ባለ በሽታ፣ የምግብና ውሃ ችግር እንዲሁም የህክምና አገልግሎት አለመኖር ለሞት የሚዳረጉትን ሰዎች ቁጥር ከፍ ሊያደርገው እንደሚችል ሪፖርቱ ጠቅሷል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Social

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule