• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዳኛውማ “ደርግ” ነው

October 11, 2020 09:00 pm by Editor 2 Comments

የመጽሐፉ ርዕስ፡ “ዳኛው ማነው?” የብርሃነ መስቀል እና የታደለች ህይወት በኢሕአፓ የትግል ታሪክ 2012 ዓ.ም. እና የብርሃነመስቀል የእሥርቤት ቃል ምርመራ ሰኔ1971 ዓ.ም.

ሙሉውን የመጽሐፍ ግምገማ ለማንበብ

እዚህ ላይ ይጫኑ

“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature, Right Column Tagged With: birhanemeskel redda, dagnaw manew, derg, eprp, tadelech, ዳኛውማነው?

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 16, 2020 08:17 am at 8:17 am

    በኢትዮጵያ የፓለቲካ ታሪክ ውስጥ እንደ ኢህአፓ ያለ ሁለ አቀፍ ድርጅት ተፈጥሮ አያውቅም። በአላማ ጽናት፤ በጊዜው የርዬተ ዓለም ጥንካሬ ኢህአፓን የሚስተካከል ያኔም አልነበረም አሁንም አልተፈጠረም፡፡ ላመኑበት ሞትን በዝማሬ የተቀበሉ፤ ከሞቀ ቤታቸው ለሃገር በጎ ነገርን በማሰብ በረሃ ለበረሃ የተንከራተቱ እልፍ ናቸው፡፡ አይኔ ካየው ጥቂት ልበል፡፡ በአንድ ክፍል ተኝቼ እያለሁ የማያቋርጥ ተኩስ በከተማው ይሰማል፡፡ ውሾች ይጮሃሉ፤ ተኩሱም ጋብ ይልና እንደገና ይንጣጣል፡፡ በዚህ መካከል ድንገት በድምጽ ማጉያ “ይህ የኢህአሠ ሰራዊት ነው” የሚል ድምጽ ይሰማል። ወዲያውም ከተማውን ተቆጣጥረው እኔ ወደ አረፍኩበት ሆቴል በመግባት ፍተሻ አድርገው የሚገሉትንና የሚይዙትን ይዘው ወደ መጡበት ይመለሳሉ፡፡ ደርግ ከቀን በህዋላ በመድረስ ከጫማ ጠራጊ እስከ ገበሬ ሳይቀር ያገኘውን ሁሉ መግደልና ማሰሩ ትዝ ይለኛል፡፡ ሌላ ላክል ሁለት የኢህአፓ አባል ፍቅረኞች በደርግ ይያዙና ይታሰራሉ፡፡ ያው የስመ ምርመራው ካለቀ በህዋላ ከሌሎች ጋር አብረው እንዲገደሉ ይወሰናል፡፡ ጧት ቁርስ ልበላ ወደ ከተማ ስወጣ ተቃቅፈው የወደቁ የሁለት ሰዎች ሬሳ አየሁና ተጠግቼ ቆሞ የሚጠብቀውን የቀበሌ ዘበኛ እነማን ናቸው ስለው አይ አንተ ፍቅረኞች ናቸው፡፡ ገዳዪ ስፔሻል ፎርስ እንደነገረኝ አብረን ተቃቅፈን እንሙት ብለው በመጠየቃቸው ተፈቅዶላቸው በሆዳቸው ተቃቅፈው ተኝተው ይኸው ተገለው ወድቀዋል፡፡ እንደማስታወክ አረገኝና ልበላ ያሰብኩትን ቁርስ ረስቼ ወደ ቤት ተመለስኩ፡፡ የሚገርመው ሲተኮስባቸው ስጋቸውን አልፎ መሬቱ ሁሉ መቦዳደሱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የግፈኞች ሃገር ናት፡፡ የሚያስብላትንና የሚያሳስቧትን ለይታ አታውቅም፡፡ የሞተላት ሳይሆን የገደሏት ነው የሚጠቀሙቧት፡፡ ታዲያ ያኔ እንዲህ ነበር አሁን እንደዛ ነው እያሉ ከሞት ተራፊዎች መካከል በሃሳብ መቧቀሱ አላስፈላጊ ነው፡፡ ተጠያቂው ማን ነው ለሚለው መልሱ ቀላል ነው፡፡ ሁላችንም ነን፡፡ የሃገሪቱን ብርቅዬ ልጆች አፈር የከተተው ያ የፓለቲካ ፍትጊያ ለሻቢያና ለወያኔ በር ከፍቶ ሃገሪቱ ዛሬ በኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች እንድትናጥ ለማድረጉ ማነህ ባለሳምንት አስብሎ ሰንበቴ አያስደፋም፡፡ ጉዳዪ ግልጽ ነው። ሁሉም ሰው አጥፍቷል። ግማሹ ጠቋሚ፤ ሌላው ገዳይና አስገዳይ፤ ጭራሽ የለሁበትም የሚለው ሰው እንደበግ እየተጎተተ ሲታረድ ያኔም አይቷል አሁንም እያየ ነው፡፡ ስለዚህ እንደ ጲላጦስ እጅን ታጥቦ ከነገሩ የለሁበትም ማለት ግብዝነት እንጂ እውነትነት የለውም፡፡ ለሃገሪቱ መኮታኮት ከታህሳሱ ግርግር ጀመሮ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረሰ በጎሳና በቋንቋ አለያም በርዪተ ኣለም ጥሪ ተሰባስበው የተፋለሙና አሁንም በመፋለም ላይ ያሉ ሁሉ አስተዋጾ አድርገዋል፡፡ አንድ ነገር ግን አልገባኝም፡፡ የቀድሞዋ ታጋይ፤ የአሁኗ አምባሳደር እንዴት ነው ከወያኔ ጋር በሃሳብ ተጣጥመው አምባሳደር መሆን የበቁት? ለእኔ ኢህአፓና ወያኔ ማዶ ለማዶ የሚተያዪ ሜዳ ላይ የተፋለሙ ጭራሽ አስታራቂ ሃሳብ በመካከላቸው የጠፋ መሆኑን ብቻ ነው የማውቀው፡፡ ለዚህ ይሆን አበው “ለሞተ ይብላኝ” የሚሉት? እልፍ ቢከፈለኝ እኔ በወያኔ ስርአት አምባሳደር አልሆንም፡፡ መጽሃፉ መጻፉ ማለፊያ ነው። ግን ዳኛው ደርግ ብቻ ነበር ብሎ መቀበል ግን ተጨፈኑና ላሞኛችሁ እንደማለት ይቆጠራል፡፡ ቆንጭራም ሆነ ከዘራ፤ በጣትም ሆነ በወረቀት የጠቆሙ፤ በምላሳቸው ሰውን በውሸት የከሰሱ፤ ገራፊዎች፤ አፋኞች የቀይ ሽብርና የነጭ ሽብር ተሳታፊዎች፤ በየጎራው በካድሬ ስም ጠበንጃ አንግተው ህዝብን ያሰቃዪ፤ በመለዪ ለባሹ ውስጥ ወታደሩንና ሃገራቸውን ለወያኔና ለሻቢያ የሸጡ፤ በደርግ ጽ/ቤት ውስጥ ሚስጢር ሲያቀብሉ የኖሩ፤ ሰዎችን በሃሰት ከሰውና አስመስክረው ሚስቶቻቸውንና ሃብታቸውን የዘረፉ ዛሬ ቆመው እኛ አላጠፋንም እነዚያ ናቸው የሚሉ ሁሉ በድኖች ናቸው፡፡ የቁም ሙታኖች ሴራና ተንኮል ድምር ውጤት ነው ዛሬ ሃገሪቷ ፍርክርኳ እንዲወጣ ያደረጋት፡፡ የነገውንም በውል የሚያውቅ የለም፡፡ በቃኝ!

    Reply
  2. ዘረ-ያዕቖብ says

    October 22, 2020 09:46 am at 9:46 am

    Tesfa፣
    ያወሳሄው የቅርቡ ጊዜ ታሪካችን የሚየንገበግብና የሚያንሰፈስፍ ነው:: በመደምደምያህ ላይ ስለ ነገ ያወሳሄውን አስመልክቶ ግን፣ ዛሬ ነገን አርግዛ ትጓዛለች እንዲሉት ነውና፣ የዛሬ አስተሳሰባችንና ተግባራችን ነገን ይወስናል!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule