• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዳኛውማ “ደርግ” ነው

October 11, 2020 09:00 pm by Editor 2 Comments

የመጽሐፉ ርዕስ፡ “ዳኛው ማነው?” የብርሃነ መስቀል እና የታደለች ህይወት በኢሕአፓ የትግል ታሪክ 2012 ዓ.ም. እና የብርሃነመስቀል የእሥርቤት ቃል ምርመራ ሰኔ1971 ዓ.ም.

ሙሉውን የመጽሐፍ ግምገማ ለማንበብ

እዚህ ላይ ይጫኑ

“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature, Right Column Tagged With: birhanemeskel redda, dagnaw manew, derg, eprp, tadelech, ዳኛውማነው?

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 16, 2020 08:17 am at 8:17 am

    በኢትዮጵያ የፓለቲካ ታሪክ ውስጥ እንደ ኢህአፓ ያለ ሁለ አቀፍ ድርጅት ተፈጥሮ አያውቅም። በአላማ ጽናት፤ በጊዜው የርዬተ ዓለም ጥንካሬ ኢህአፓን የሚስተካከል ያኔም አልነበረም አሁንም አልተፈጠረም፡፡ ላመኑበት ሞትን በዝማሬ የተቀበሉ፤ ከሞቀ ቤታቸው ለሃገር በጎ ነገርን በማሰብ በረሃ ለበረሃ የተንከራተቱ እልፍ ናቸው፡፡ አይኔ ካየው ጥቂት ልበል፡፡ በአንድ ክፍል ተኝቼ እያለሁ የማያቋርጥ ተኩስ በከተማው ይሰማል፡፡ ውሾች ይጮሃሉ፤ ተኩሱም ጋብ ይልና እንደገና ይንጣጣል፡፡ በዚህ መካከል ድንገት በድምጽ ማጉያ “ይህ የኢህአሠ ሰራዊት ነው” የሚል ድምጽ ይሰማል። ወዲያውም ከተማውን ተቆጣጥረው እኔ ወደ አረፍኩበት ሆቴል በመግባት ፍተሻ አድርገው የሚገሉትንና የሚይዙትን ይዘው ወደ መጡበት ይመለሳሉ፡፡ ደርግ ከቀን በህዋላ በመድረስ ከጫማ ጠራጊ እስከ ገበሬ ሳይቀር ያገኘውን ሁሉ መግደልና ማሰሩ ትዝ ይለኛል፡፡ ሌላ ላክል ሁለት የኢህአፓ አባል ፍቅረኞች በደርግ ይያዙና ይታሰራሉ፡፡ ያው የስመ ምርመራው ካለቀ በህዋላ ከሌሎች ጋር አብረው እንዲገደሉ ይወሰናል፡፡ ጧት ቁርስ ልበላ ወደ ከተማ ስወጣ ተቃቅፈው የወደቁ የሁለት ሰዎች ሬሳ አየሁና ተጠግቼ ቆሞ የሚጠብቀውን የቀበሌ ዘበኛ እነማን ናቸው ስለው አይ አንተ ፍቅረኞች ናቸው፡፡ ገዳዪ ስፔሻል ፎርስ እንደነገረኝ አብረን ተቃቅፈን እንሙት ብለው በመጠየቃቸው ተፈቅዶላቸው በሆዳቸው ተቃቅፈው ተኝተው ይኸው ተገለው ወድቀዋል፡፡ እንደማስታወክ አረገኝና ልበላ ያሰብኩትን ቁርስ ረስቼ ወደ ቤት ተመለስኩ፡፡ የሚገርመው ሲተኮስባቸው ስጋቸውን አልፎ መሬቱ ሁሉ መቦዳደሱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የግፈኞች ሃገር ናት፡፡ የሚያስብላትንና የሚያሳስቧትን ለይታ አታውቅም፡፡ የሞተላት ሳይሆን የገደሏት ነው የሚጠቀሙቧት፡፡ ታዲያ ያኔ እንዲህ ነበር አሁን እንደዛ ነው እያሉ ከሞት ተራፊዎች መካከል በሃሳብ መቧቀሱ አላስፈላጊ ነው፡፡ ተጠያቂው ማን ነው ለሚለው መልሱ ቀላል ነው፡፡ ሁላችንም ነን፡፡ የሃገሪቱን ብርቅዬ ልጆች አፈር የከተተው ያ የፓለቲካ ፍትጊያ ለሻቢያና ለወያኔ በር ከፍቶ ሃገሪቱ ዛሬ በኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች እንድትናጥ ለማድረጉ ማነህ ባለሳምንት አስብሎ ሰንበቴ አያስደፋም፡፡ ጉዳዪ ግልጽ ነው። ሁሉም ሰው አጥፍቷል። ግማሹ ጠቋሚ፤ ሌላው ገዳይና አስገዳይ፤ ጭራሽ የለሁበትም የሚለው ሰው እንደበግ እየተጎተተ ሲታረድ ያኔም አይቷል አሁንም እያየ ነው፡፡ ስለዚህ እንደ ጲላጦስ እጅን ታጥቦ ከነገሩ የለሁበትም ማለት ግብዝነት እንጂ እውነትነት የለውም፡፡ ለሃገሪቱ መኮታኮት ከታህሳሱ ግርግር ጀመሮ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረሰ በጎሳና በቋንቋ አለያም በርዪተ ኣለም ጥሪ ተሰባስበው የተፋለሙና አሁንም በመፋለም ላይ ያሉ ሁሉ አስተዋጾ አድርገዋል፡፡ አንድ ነገር ግን አልገባኝም፡፡ የቀድሞዋ ታጋይ፤ የአሁኗ አምባሳደር እንዴት ነው ከወያኔ ጋር በሃሳብ ተጣጥመው አምባሳደር መሆን የበቁት? ለእኔ ኢህአፓና ወያኔ ማዶ ለማዶ የሚተያዪ ሜዳ ላይ የተፋለሙ ጭራሽ አስታራቂ ሃሳብ በመካከላቸው የጠፋ መሆኑን ብቻ ነው የማውቀው፡፡ ለዚህ ይሆን አበው “ለሞተ ይብላኝ” የሚሉት? እልፍ ቢከፈለኝ እኔ በወያኔ ስርአት አምባሳደር አልሆንም፡፡ መጽሃፉ መጻፉ ማለፊያ ነው። ግን ዳኛው ደርግ ብቻ ነበር ብሎ መቀበል ግን ተጨፈኑና ላሞኛችሁ እንደማለት ይቆጠራል፡፡ ቆንጭራም ሆነ ከዘራ፤ በጣትም ሆነ በወረቀት የጠቆሙ፤ በምላሳቸው ሰውን በውሸት የከሰሱ፤ ገራፊዎች፤ አፋኞች የቀይ ሽብርና የነጭ ሽብር ተሳታፊዎች፤ በየጎራው በካድሬ ስም ጠበንጃ አንግተው ህዝብን ያሰቃዪ፤ በመለዪ ለባሹ ውስጥ ወታደሩንና ሃገራቸውን ለወያኔና ለሻቢያ የሸጡ፤ በደርግ ጽ/ቤት ውስጥ ሚስጢር ሲያቀብሉ የኖሩ፤ ሰዎችን በሃሰት ከሰውና አስመስክረው ሚስቶቻቸውንና ሃብታቸውን የዘረፉ ዛሬ ቆመው እኛ አላጠፋንም እነዚያ ናቸው የሚሉ ሁሉ በድኖች ናቸው፡፡ የቁም ሙታኖች ሴራና ተንኮል ድምር ውጤት ነው ዛሬ ሃገሪቷ ፍርክርኳ እንዲወጣ ያደረጋት፡፡ የነገውንም በውል የሚያውቅ የለም፡፡ በቃኝ!

    Reply
  2. ዘረ-ያዕቖብ says

    October 22, 2020 09:46 am at 9:46 am

    Tesfa፣
    ያወሳሄው የቅርቡ ጊዜ ታሪካችን የሚየንገበግብና የሚያንሰፈስፍ ነው:: በመደምደምያህ ላይ ስለ ነገ ያወሳሄውን አስመልክቶ ግን፣ ዛሬ ነገን አርግዛ ትጓዛለች እንዲሉት ነውና፣ የዛሬ አስተሳሰባችንና ተግባራችን ነገን ይወስናል!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am
  • በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ March 15, 2021 09:04 am
  • በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ March 15, 2021 08:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule