• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዳኛውማ “ደርግ” ነው

October 11, 2020 09:00 pm by Editor 2 Comments

የመጽሐፉ ርዕስ፡ “ዳኛው ማነው?” የብርሃነ መስቀል እና የታደለች ህይወት በኢሕአፓ የትግል ታሪክ 2012 ዓ.ም. እና የብርሃነመስቀል የእሥርቤት ቃል ምርመራ ሰኔ1971 ዓ.ም.

ሙሉውን የመጽሐፍ ግምገማ ለማንበብ

እዚህ ላይ ይጫኑ

“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature, Right Column Tagged With: birhanemeskel redda, dagnaw manew, derg, eprp, tadelech, ዳኛውማነው?

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 16, 2020 08:17 am at 8:17 am

    በኢትዮጵያ የፓለቲካ ታሪክ ውስጥ እንደ ኢህአፓ ያለ ሁለ አቀፍ ድርጅት ተፈጥሮ አያውቅም። በአላማ ጽናት፤ በጊዜው የርዬተ ዓለም ጥንካሬ ኢህአፓን የሚስተካከል ያኔም አልነበረም አሁንም አልተፈጠረም፡፡ ላመኑበት ሞትን በዝማሬ የተቀበሉ፤ ከሞቀ ቤታቸው ለሃገር በጎ ነገርን በማሰብ በረሃ ለበረሃ የተንከራተቱ እልፍ ናቸው፡፡ አይኔ ካየው ጥቂት ልበል፡፡ በአንድ ክፍል ተኝቼ እያለሁ የማያቋርጥ ተኩስ በከተማው ይሰማል፡፡ ውሾች ይጮሃሉ፤ ተኩሱም ጋብ ይልና እንደገና ይንጣጣል፡፡ በዚህ መካከል ድንገት በድምጽ ማጉያ “ይህ የኢህአሠ ሰራዊት ነው” የሚል ድምጽ ይሰማል። ወዲያውም ከተማውን ተቆጣጥረው እኔ ወደ አረፍኩበት ሆቴል በመግባት ፍተሻ አድርገው የሚገሉትንና የሚይዙትን ይዘው ወደ መጡበት ይመለሳሉ፡፡ ደርግ ከቀን በህዋላ በመድረስ ከጫማ ጠራጊ እስከ ገበሬ ሳይቀር ያገኘውን ሁሉ መግደልና ማሰሩ ትዝ ይለኛል፡፡ ሌላ ላክል ሁለት የኢህአፓ አባል ፍቅረኞች በደርግ ይያዙና ይታሰራሉ፡፡ ያው የስመ ምርመራው ካለቀ በህዋላ ከሌሎች ጋር አብረው እንዲገደሉ ይወሰናል፡፡ ጧት ቁርስ ልበላ ወደ ከተማ ስወጣ ተቃቅፈው የወደቁ የሁለት ሰዎች ሬሳ አየሁና ተጠግቼ ቆሞ የሚጠብቀውን የቀበሌ ዘበኛ እነማን ናቸው ስለው አይ አንተ ፍቅረኞች ናቸው፡፡ ገዳዪ ስፔሻል ፎርስ እንደነገረኝ አብረን ተቃቅፈን እንሙት ብለው በመጠየቃቸው ተፈቅዶላቸው በሆዳቸው ተቃቅፈው ተኝተው ይኸው ተገለው ወድቀዋል፡፡ እንደማስታወክ አረገኝና ልበላ ያሰብኩትን ቁርስ ረስቼ ወደ ቤት ተመለስኩ፡፡ የሚገርመው ሲተኮስባቸው ስጋቸውን አልፎ መሬቱ ሁሉ መቦዳደሱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የግፈኞች ሃገር ናት፡፡ የሚያስብላትንና የሚያሳስቧትን ለይታ አታውቅም፡፡ የሞተላት ሳይሆን የገደሏት ነው የሚጠቀሙቧት፡፡ ታዲያ ያኔ እንዲህ ነበር አሁን እንደዛ ነው እያሉ ከሞት ተራፊዎች መካከል በሃሳብ መቧቀሱ አላስፈላጊ ነው፡፡ ተጠያቂው ማን ነው ለሚለው መልሱ ቀላል ነው፡፡ ሁላችንም ነን፡፡ የሃገሪቱን ብርቅዬ ልጆች አፈር የከተተው ያ የፓለቲካ ፍትጊያ ለሻቢያና ለወያኔ በር ከፍቶ ሃገሪቱ ዛሬ በኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች እንድትናጥ ለማድረጉ ማነህ ባለሳምንት አስብሎ ሰንበቴ አያስደፋም፡፡ ጉዳዪ ግልጽ ነው። ሁሉም ሰው አጥፍቷል። ግማሹ ጠቋሚ፤ ሌላው ገዳይና አስገዳይ፤ ጭራሽ የለሁበትም የሚለው ሰው እንደበግ እየተጎተተ ሲታረድ ያኔም አይቷል አሁንም እያየ ነው፡፡ ስለዚህ እንደ ጲላጦስ እጅን ታጥቦ ከነገሩ የለሁበትም ማለት ግብዝነት እንጂ እውነትነት የለውም፡፡ ለሃገሪቱ መኮታኮት ከታህሳሱ ግርግር ጀመሮ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረሰ በጎሳና በቋንቋ አለያም በርዪተ ኣለም ጥሪ ተሰባስበው የተፋለሙና አሁንም በመፋለም ላይ ያሉ ሁሉ አስተዋጾ አድርገዋል፡፡ አንድ ነገር ግን አልገባኝም፡፡ የቀድሞዋ ታጋይ፤ የአሁኗ አምባሳደር እንዴት ነው ከወያኔ ጋር በሃሳብ ተጣጥመው አምባሳደር መሆን የበቁት? ለእኔ ኢህአፓና ወያኔ ማዶ ለማዶ የሚተያዪ ሜዳ ላይ የተፋለሙ ጭራሽ አስታራቂ ሃሳብ በመካከላቸው የጠፋ መሆኑን ብቻ ነው የማውቀው፡፡ ለዚህ ይሆን አበው “ለሞተ ይብላኝ” የሚሉት? እልፍ ቢከፈለኝ እኔ በወያኔ ስርአት አምባሳደር አልሆንም፡፡ መጽሃፉ መጻፉ ማለፊያ ነው። ግን ዳኛው ደርግ ብቻ ነበር ብሎ መቀበል ግን ተጨፈኑና ላሞኛችሁ እንደማለት ይቆጠራል፡፡ ቆንጭራም ሆነ ከዘራ፤ በጣትም ሆነ በወረቀት የጠቆሙ፤ በምላሳቸው ሰውን በውሸት የከሰሱ፤ ገራፊዎች፤ አፋኞች የቀይ ሽብርና የነጭ ሽብር ተሳታፊዎች፤ በየጎራው በካድሬ ስም ጠበንጃ አንግተው ህዝብን ያሰቃዪ፤ በመለዪ ለባሹ ውስጥ ወታደሩንና ሃገራቸውን ለወያኔና ለሻቢያ የሸጡ፤ በደርግ ጽ/ቤት ውስጥ ሚስጢር ሲያቀብሉ የኖሩ፤ ሰዎችን በሃሰት ከሰውና አስመስክረው ሚስቶቻቸውንና ሃብታቸውን የዘረፉ ዛሬ ቆመው እኛ አላጠፋንም እነዚያ ናቸው የሚሉ ሁሉ በድኖች ናቸው፡፡ የቁም ሙታኖች ሴራና ተንኮል ድምር ውጤት ነው ዛሬ ሃገሪቷ ፍርክርኳ እንዲወጣ ያደረጋት፡፡ የነገውንም በውል የሚያውቅ የለም፡፡ በቃኝ!

    Reply
  2. ዘረ-ያዕቖብ says

    October 22, 2020 09:46 am at 9:46 am

    Tesfa፣
    ያወሳሄው የቅርቡ ጊዜ ታሪካችን የሚየንገበግብና የሚያንሰፈስፍ ነው:: በመደምደምያህ ላይ ስለ ነገ ያወሳሄውን አስመልክቶ ግን፣ ዛሬ ነገን አርግዛ ትጓዛለች እንዲሉት ነውና፣ የዛሬ አስተሳሰባችንና ተግባራችን ነገን ይወስናል!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule