• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዳኛውማ “ደርግ” ነው

October 11, 2020 09:00 pm by Editor 2 Comments

የመጽሐፉ ርዕስ፡ “ዳኛው ማነው?” የብርሃነ መስቀል እና የታደለች ህይወት በኢሕአፓ የትግል ታሪክ 2012 ዓ.ም. እና የብርሃነመስቀል የእሥርቤት ቃል ምርመራ ሰኔ1971 ዓ.ም.

ሙሉውን የመጽሐፍ ግምገማ ለማንበብ

እዚህ ላይ ይጫኑ

“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature, Right Column Tagged With: birhanemeskel redda, dagnaw manew, derg, eprp, tadelech, ዳኛውማነው?

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 16, 2020 08:17 am at 8:17 am

    በኢትዮጵያ የፓለቲካ ታሪክ ውስጥ እንደ ኢህአፓ ያለ ሁለ አቀፍ ድርጅት ተፈጥሮ አያውቅም። በአላማ ጽናት፤ በጊዜው የርዬተ ዓለም ጥንካሬ ኢህአፓን የሚስተካከል ያኔም አልነበረም አሁንም አልተፈጠረም፡፡ ላመኑበት ሞትን በዝማሬ የተቀበሉ፤ ከሞቀ ቤታቸው ለሃገር በጎ ነገርን በማሰብ በረሃ ለበረሃ የተንከራተቱ እልፍ ናቸው፡፡ አይኔ ካየው ጥቂት ልበል፡፡ በአንድ ክፍል ተኝቼ እያለሁ የማያቋርጥ ተኩስ በከተማው ይሰማል፡፡ ውሾች ይጮሃሉ፤ ተኩሱም ጋብ ይልና እንደገና ይንጣጣል፡፡ በዚህ መካከል ድንገት በድምጽ ማጉያ “ይህ የኢህአሠ ሰራዊት ነው” የሚል ድምጽ ይሰማል። ወዲያውም ከተማውን ተቆጣጥረው እኔ ወደ አረፍኩበት ሆቴል በመግባት ፍተሻ አድርገው የሚገሉትንና የሚይዙትን ይዘው ወደ መጡበት ይመለሳሉ፡፡ ደርግ ከቀን በህዋላ በመድረስ ከጫማ ጠራጊ እስከ ገበሬ ሳይቀር ያገኘውን ሁሉ መግደልና ማሰሩ ትዝ ይለኛል፡፡ ሌላ ላክል ሁለት የኢህአፓ አባል ፍቅረኞች በደርግ ይያዙና ይታሰራሉ፡፡ ያው የስመ ምርመራው ካለቀ በህዋላ ከሌሎች ጋር አብረው እንዲገደሉ ይወሰናል፡፡ ጧት ቁርስ ልበላ ወደ ከተማ ስወጣ ተቃቅፈው የወደቁ የሁለት ሰዎች ሬሳ አየሁና ተጠግቼ ቆሞ የሚጠብቀውን የቀበሌ ዘበኛ እነማን ናቸው ስለው አይ አንተ ፍቅረኞች ናቸው፡፡ ገዳዪ ስፔሻል ፎርስ እንደነገረኝ አብረን ተቃቅፈን እንሙት ብለው በመጠየቃቸው ተፈቅዶላቸው በሆዳቸው ተቃቅፈው ተኝተው ይኸው ተገለው ወድቀዋል፡፡ እንደማስታወክ አረገኝና ልበላ ያሰብኩትን ቁርስ ረስቼ ወደ ቤት ተመለስኩ፡፡ የሚገርመው ሲተኮስባቸው ስጋቸውን አልፎ መሬቱ ሁሉ መቦዳደሱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የግፈኞች ሃገር ናት፡፡ የሚያስብላትንና የሚያሳስቧትን ለይታ አታውቅም፡፡ የሞተላት ሳይሆን የገደሏት ነው የሚጠቀሙቧት፡፡ ታዲያ ያኔ እንዲህ ነበር አሁን እንደዛ ነው እያሉ ከሞት ተራፊዎች መካከል በሃሳብ መቧቀሱ አላስፈላጊ ነው፡፡ ተጠያቂው ማን ነው ለሚለው መልሱ ቀላል ነው፡፡ ሁላችንም ነን፡፡ የሃገሪቱን ብርቅዬ ልጆች አፈር የከተተው ያ የፓለቲካ ፍትጊያ ለሻቢያና ለወያኔ በር ከፍቶ ሃገሪቱ ዛሬ በኦሮሞ ጠባብ ብሄርተኞች እንድትናጥ ለማድረጉ ማነህ ባለሳምንት አስብሎ ሰንበቴ አያስደፋም፡፡ ጉዳዪ ግልጽ ነው። ሁሉም ሰው አጥፍቷል። ግማሹ ጠቋሚ፤ ሌላው ገዳይና አስገዳይ፤ ጭራሽ የለሁበትም የሚለው ሰው እንደበግ እየተጎተተ ሲታረድ ያኔም አይቷል አሁንም እያየ ነው፡፡ ስለዚህ እንደ ጲላጦስ እጅን ታጥቦ ከነገሩ የለሁበትም ማለት ግብዝነት እንጂ እውነትነት የለውም፡፡ ለሃገሪቱ መኮታኮት ከታህሳሱ ግርግር ጀመሮ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረሰ በጎሳና በቋንቋ አለያም በርዪተ ኣለም ጥሪ ተሰባስበው የተፋለሙና አሁንም በመፋለም ላይ ያሉ ሁሉ አስተዋጾ አድርገዋል፡፡ አንድ ነገር ግን አልገባኝም፡፡ የቀድሞዋ ታጋይ፤ የአሁኗ አምባሳደር እንዴት ነው ከወያኔ ጋር በሃሳብ ተጣጥመው አምባሳደር መሆን የበቁት? ለእኔ ኢህአፓና ወያኔ ማዶ ለማዶ የሚተያዪ ሜዳ ላይ የተፋለሙ ጭራሽ አስታራቂ ሃሳብ በመካከላቸው የጠፋ መሆኑን ብቻ ነው የማውቀው፡፡ ለዚህ ይሆን አበው “ለሞተ ይብላኝ” የሚሉት? እልፍ ቢከፈለኝ እኔ በወያኔ ስርአት አምባሳደር አልሆንም፡፡ መጽሃፉ መጻፉ ማለፊያ ነው። ግን ዳኛው ደርግ ብቻ ነበር ብሎ መቀበል ግን ተጨፈኑና ላሞኛችሁ እንደማለት ይቆጠራል፡፡ ቆንጭራም ሆነ ከዘራ፤ በጣትም ሆነ በወረቀት የጠቆሙ፤ በምላሳቸው ሰውን በውሸት የከሰሱ፤ ገራፊዎች፤ አፋኞች የቀይ ሽብርና የነጭ ሽብር ተሳታፊዎች፤ በየጎራው በካድሬ ስም ጠበንጃ አንግተው ህዝብን ያሰቃዪ፤ በመለዪ ለባሹ ውስጥ ወታደሩንና ሃገራቸውን ለወያኔና ለሻቢያ የሸጡ፤ በደርግ ጽ/ቤት ውስጥ ሚስጢር ሲያቀብሉ የኖሩ፤ ሰዎችን በሃሰት ከሰውና አስመስክረው ሚስቶቻቸውንና ሃብታቸውን የዘረፉ ዛሬ ቆመው እኛ አላጠፋንም እነዚያ ናቸው የሚሉ ሁሉ በድኖች ናቸው፡፡ የቁም ሙታኖች ሴራና ተንኮል ድምር ውጤት ነው ዛሬ ሃገሪቷ ፍርክርኳ እንዲወጣ ያደረጋት፡፡ የነገውንም በውል የሚያውቅ የለም፡፡ በቃኝ!

    Reply
  2. ዘረ-ያዕቖብ says

    October 22, 2020 09:46 am at 9:46 am

    Tesfa፣
    ያወሳሄው የቅርቡ ጊዜ ታሪካችን የሚየንገበግብና የሚያንሰፈስፍ ነው:: በመደምደምያህ ላይ ስለ ነገ ያወሳሄውን አስመልክቶ ግን፣ ዛሬ ነገን አርግዛ ትጓዛለች እንዲሉት ነውና፣ የዛሬ አስተሳሰባችንና ተግባራችን ነገን ይወስናል!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule