• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠላትን በዱላ በመምታት ጀብዱ የፈጸሙ አባትና ልጅ

September 24, 2021 10:10 am by Editor Leave a Comment

አርሶ አደር ፈንታዬ አበረ ተወልደው ያደጉት በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ቀበሌ 32 ነው። እንደአካባቢያቸው ማኅበረሰብ ሁሉ እሳቸውም በደግነታቸው፣ በታታሪነታቸውና በጀግንነታቸው ይታወቃሉ። በግብርና ሥራም ቢሆን የተዋጣላቸው አርሶ አደር ናቸው። በእንግድነት ለመጣባቸውም አልጋቸውን ይለቃሉ፣ የሚበላ የሚጠጣ ቤት ያፈራውን ሁሉ ያቀርባሉ።

ዛሬ ግን ወደ አርሶ አደሩ ቀዬ ብቅ ያለው ተናፋቂ እንግዳ አይደለም፣ ወይም አረምን በማረም አርሶ አደሩን ለመርዳት የመጣ አይደለም፣ ቀማኛ፣ ወራሪ፣ አሸባሪ እና ዘራፊ ቡድን እንጂ። አርሶ አደሩ ለዚህ ወራሪ እንደ እንግዳ ተቀባይነታቸው አላስተናገዱትም ከልጃቸው ጋር በመሆን የጀግንነት ክንዳቸውን አቀመሱት እንጅ። እሳቸውም ሆነ ልጃቸው የመተኮስ ልምዱ ቢኖራቸውም የጦር መሳሪያ ግን የላቸውም። የነበራቸው ጀግንነትና ልበ ሙሉነት ነበር። ከልጃቸው ጌጡ ፈንታዬ ጋር በመሆን ጠላት ወደ እነሱ ሲመጣ ተመለከቱ።

እንደለመደው ጠላት ሊዘርፍና ሊያጠፋቸው መሆኑን ቀድመው የተረዱት ጀግናው አባት፣ ልጃቸው በያዘው ዱላ የጠላትን አንገት እንዲመታው በአይናቸው ጥቅሻ ትዕዛዝ ይሰጡታል። ወጣት ጌጡ “የአባቴን የዓይን ጥቅሻ ትዕዛዝ ተቀብዬ በያዝኩት ዱላ ብርቱ ክንዴን የጠላት ጭንቅላት ላይ አሳረፍኩበት” ብሏል። አንገቱ ላይ የተመታው ጠላትም የወረደበትን ውርጂብኝ መቋቋም ስለተሳነው እስከወዲያኛው አሸለበ።

ወጣት ጌጡም አሁን የጠላትን ክላሽ ታጠቀ። የያዘውን ዱላ አመስግኖ በማስቀመጥ በማረከው ክላሽ ከአካባቢው ወጣቶች ጋር በመሆን አካባቢውን ከጠላት እየጠበቀ መሆኑን ተናግሯል።

የልጃቸው የቁጣ ክንድ ስኬታማ መሆኑን የተመለከቱት አባቱ እሳቸውም ሊያጠፋቸው የመጣውን ሌላ ጠላት ተናንቁት፣ ልክ እንደ ጀግናው ልጃቸው በያዙት ዱላ ቀጠቀጡት፣ ጠላትም የወረደበትን ምት መቋቋም ስለተሳነው የያዘውን ክላሽ ጥሎ ፈረጠጠ። “ሮጠ ብዬ አልማርኩትም አነጣጥሬ በራሱ ክላሽ ማጅራቱን ብዬ ገደልኩት” ብለዋል። በፈጸሙት ታላቅ ጀብድ ኩራትና የላቀ ሞራል የተሰማቸው አባትና ልጅ የጠላትን ትጥቅ መረከብ ችለዋል። ጠላት አጥፊነቱ እና ቀማኛነቱ ቢከፋም በሚደርስበት ዱላ በተለያየ አካባቢ የያዘውን ትጥቅ ለነዋሪዎቹ እያስታጠቀ እየፈረጠጠ እንደሆነ ነው ጀግኖቹ የተናገሩት።

ተደራጅተው የቆዩ የቀበሌዋ ነዋሪዎች ከአረመኔው ቡድን ራሳቸውን ለመከላከል በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል። “ጠላትን መሸሽ ለእሱ ጉልበት መስጠት ነው” ያሉት አርሶ አደር ፈንታዬ ጠላትን ለመቅበር ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

“ሽሮ፣ በርበሬና ሊጥ ፍለጋ እንደውሻ ሲዞሩ እዚያው ተቀብረው እንዲቀሩ እናደርጋለን” ብለዋል። በዚሁ ጀብድ በተፈጸመበት ቀን ተደራጅተው የነበሩ የአካባቢው አርሶ አደሮችም 11 ሰርገው የገቡ የአሸባሪውን ቡድን አባላት እንደደመሰሷቸው አርሶ አደር ፈንታዬ ተናግረዋል። ሰረገው የገቡ ጠላቶች ሁሉ ማለቃቸውን ነው የተናገሩት።

“የእኔና የልጄን ጀብዱ ያዩ የቀበሌያችን ወጣቶች ሁሉ እናንተ የሄዳችሁበትን መንገድ በመከተል የጠላትን አንገት እናስደፋለን በማለት ከጎናችን ተሰልፈዋል” ብለዋል። በሁሉም አካባቢ የሚኖሩ አርሶ አደሮች ራሳቸውን ከጠላት ወረራ በመመከት የጀግንነት ታሪካቸውን ሊደግሙ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

የጀግኖቹ ጎረቤት የሆኑት አርሶ አደር አዳነ አራጌ የቀበሌያቸው ጀግኖች በዱላ መትተው ጠላት የያዘውን መሳሪያ መረከባቸውን መስክረዋል። የ32 ቀበሌ ነዋሪዎች ተደራጅተው በጠላት ላይ በከፈቱት ጥቃት ጠላት የያዘውን ቁሳቁስ ባለበት ትቶ እንዲሸሽ እንዳደረጉ ተናግረዋል። “ጠላት አርሶ አደሮችን ለማታለል ሽማግሌ ቢልክም ሥራው የማታለል መሆኑን ስለምናውቅ ጠንክረን እየታገልነው ነው” ብለዋል።

አሸባሪው ቡድን በቀበሌያችን ከቆየ የበለጠ ውድመትና ግድያ ስለሚፈጽም ከወዲሁ ጠንክረን እየታገልነው ነው ብለዋል። (አሚኮ: ቡሩክ ተሾመ – ከፍላቂት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column Tagged With: feat, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule