• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠላትን በዱላ በመምታት ጀብዱ የፈጸሙ አባትና ልጅ

September 24, 2021 10:10 am by Editor Leave a Comment

አርሶ አደር ፈንታዬ አበረ ተወልደው ያደጉት በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ቀበሌ 32 ነው። እንደአካባቢያቸው ማኅበረሰብ ሁሉ እሳቸውም በደግነታቸው፣ በታታሪነታቸውና በጀግንነታቸው ይታወቃሉ። በግብርና ሥራም ቢሆን የተዋጣላቸው አርሶ አደር ናቸው። በእንግድነት ለመጣባቸውም አልጋቸውን ይለቃሉ፣ የሚበላ የሚጠጣ ቤት ያፈራውን ሁሉ ያቀርባሉ።

ዛሬ ግን ወደ አርሶ አደሩ ቀዬ ብቅ ያለው ተናፋቂ እንግዳ አይደለም፣ ወይም አረምን በማረም አርሶ አደሩን ለመርዳት የመጣ አይደለም፣ ቀማኛ፣ ወራሪ፣ አሸባሪ እና ዘራፊ ቡድን እንጂ። አርሶ አደሩ ለዚህ ወራሪ እንደ እንግዳ ተቀባይነታቸው አላስተናገዱትም ከልጃቸው ጋር በመሆን የጀግንነት ክንዳቸውን አቀመሱት እንጅ። እሳቸውም ሆነ ልጃቸው የመተኮስ ልምዱ ቢኖራቸውም የጦር መሳሪያ ግን የላቸውም። የነበራቸው ጀግንነትና ልበ ሙሉነት ነበር። ከልጃቸው ጌጡ ፈንታዬ ጋር በመሆን ጠላት ወደ እነሱ ሲመጣ ተመለከቱ።

እንደለመደው ጠላት ሊዘርፍና ሊያጠፋቸው መሆኑን ቀድመው የተረዱት ጀግናው አባት፣ ልጃቸው በያዘው ዱላ የጠላትን አንገት እንዲመታው በአይናቸው ጥቅሻ ትዕዛዝ ይሰጡታል። ወጣት ጌጡ “የአባቴን የዓይን ጥቅሻ ትዕዛዝ ተቀብዬ በያዝኩት ዱላ ብርቱ ክንዴን የጠላት ጭንቅላት ላይ አሳረፍኩበት” ብሏል። አንገቱ ላይ የተመታው ጠላትም የወረደበትን ውርጂብኝ መቋቋም ስለተሳነው እስከወዲያኛው አሸለበ።

ወጣት ጌጡም አሁን የጠላትን ክላሽ ታጠቀ። የያዘውን ዱላ አመስግኖ በማስቀመጥ በማረከው ክላሽ ከአካባቢው ወጣቶች ጋር በመሆን አካባቢውን ከጠላት እየጠበቀ መሆኑን ተናግሯል።

የልጃቸው የቁጣ ክንድ ስኬታማ መሆኑን የተመለከቱት አባቱ እሳቸውም ሊያጠፋቸው የመጣውን ሌላ ጠላት ተናንቁት፣ ልክ እንደ ጀግናው ልጃቸው በያዙት ዱላ ቀጠቀጡት፣ ጠላትም የወረደበትን ምት መቋቋም ስለተሳነው የያዘውን ክላሽ ጥሎ ፈረጠጠ። “ሮጠ ብዬ አልማርኩትም አነጣጥሬ በራሱ ክላሽ ማጅራቱን ብዬ ገደልኩት” ብለዋል። በፈጸሙት ታላቅ ጀብድ ኩራትና የላቀ ሞራል የተሰማቸው አባትና ልጅ የጠላትን ትጥቅ መረከብ ችለዋል። ጠላት አጥፊነቱ እና ቀማኛነቱ ቢከፋም በሚደርስበት ዱላ በተለያየ አካባቢ የያዘውን ትጥቅ ለነዋሪዎቹ እያስታጠቀ እየፈረጠጠ እንደሆነ ነው ጀግኖቹ የተናገሩት።

ተደራጅተው የቆዩ የቀበሌዋ ነዋሪዎች ከአረመኔው ቡድን ራሳቸውን ለመከላከል በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል። “ጠላትን መሸሽ ለእሱ ጉልበት መስጠት ነው” ያሉት አርሶ አደር ፈንታዬ ጠላትን ለመቅበር ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

“ሽሮ፣ በርበሬና ሊጥ ፍለጋ እንደውሻ ሲዞሩ እዚያው ተቀብረው እንዲቀሩ እናደርጋለን” ብለዋል። በዚሁ ጀብድ በተፈጸመበት ቀን ተደራጅተው የነበሩ የአካባቢው አርሶ አደሮችም 11 ሰርገው የገቡ የአሸባሪውን ቡድን አባላት እንደደመሰሷቸው አርሶ አደር ፈንታዬ ተናግረዋል። ሰረገው የገቡ ጠላቶች ሁሉ ማለቃቸውን ነው የተናገሩት።

“የእኔና የልጄን ጀብዱ ያዩ የቀበሌያችን ወጣቶች ሁሉ እናንተ የሄዳችሁበትን መንገድ በመከተል የጠላትን አንገት እናስደፋለን በማለት ከጎናችን ተሰልፈዋል” ብለዋል። በሁሉም አካባቢ የሚኖሩ አርሶ አደሮች ራሳቸውን ከጠላት ወረራ በመመከት የጀግንነት ታሪካቸውን ሊደግሙ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

የጀግኖቹ ጎረቤት የሆኑት አርሶ አደር አዳነ አራጌ የቀበሌያቸው ጀግኖች በዱላ መትተው ጠላት የያዘውን መሳሪያ መረከባቸውን መስክረዋል። የ32 ቀበሌ ነዋሪዎች ተደራጅተው በጠላት ላይ በከፈቱት ጥቃት ጠላት የያዘውን ቁሳቁስ ባለበት ትቶ እንዲሸሽ እንዳደረጉ ተናግረዋል። “ጠላት አርሶ አደሮችን ለማታለል ሽማግሌ ቢልክም ሥራው የማታለል መሆኑን ስለምናውቅ ጠንክረን እየታገልነው ነው” ብለዋል።

አሸባሪው ቡድን በቀበሌያችን ከቆየ የበለጠ ውድመትና ግድያ ስለሚፈጽም ከወዲሁ ጠንክረን እየታገልነው ነው ብለዋል። (አሚኮ: ቡሩክ ተሾመ – ከፍላቂት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column Tagged With: feat, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule