• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልደቱ አያሌውን ስድስት ነገሮች ሆነው ይሆናል በሉት

September 13, 2021 11:23 am by Editor Leave a Comment

አቶ ልደቱ አያሌው የፖለቲካ ህይወቱን አሀዱ ብሎ የጀመረው 1983ዓ.ም. ህወሃት/ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ የከተማዋን ወጣቶች የማደራጀት ስራ ላይ ከተሰማሩ ወጣቶች አንዱ ሆኖ ነው። በዚያ ወቅት ወጣቱ ልደቱ ለወያኔ መንግስት የመወገን ጫና በነበረበት የወጣት ማህበር ምስረታ ሂደት ንቁ ተዋናይ ነበረ። በመሆኑም የማህበሩ ሊቀመንበር የመሆን ፍላጎት እንደነበረው በወቅቱ አብረውት የነበሩ የመሰከሩት ነገር ነው። ነገር ግን በ1990 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በይፋ ሲመሰረት ወጣቱን በማደራጀት ምንም ተሳትፎ ያልነበረው የዳዊት ዮሃንስ (አፈጉባዔ የነበረ) ሚስት ወንድም የሆነው ወጣት ታጠቅ ካሳ ሊቀመንበር ሆኖ ተመረጠ።

ይሄኔ ነው እንግድህ የልደቱ የመጀመሪያው የፖለቲካ አቋም እጥፋት የተጀመረው። የታጠቅን በሊቀመንበርነት መመረጥ አሚን ብሎ መቀበል አልፈለገም። የተመሰረተው ማህበር ግን እንደታሰበው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ገለልተኛ እንደማይሆን እና ይልቁንም የኢህአዴግ የወጣት ክንፍ ሊባል የሚችል ነው። ያዛኔው ልደቱን ያበሳጨው ጉዳይ የወያኔ አገልጋይ ለመሆን አለመታመኑ ብቻ ነው። በመሆኑም ቀጥሎ የሄደው አዲስ ወደ ተመሰረተው የፕ/ር አስራት ወልደየስ ፓርቲ መአሕድ ነው። ልደቱ በይፋ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሆኖ ሲወጣ ኃላፊነቱን የጀመረው በተመሳሳይ የመአሕድ ወጣት ክንፍ አመራርነትን ሲቀላቀል ነው።

ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ጥሎ ወጥቶ እስከ አሁን ድረስ የሚመራውን የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን (ኢዴፓ) መሠረተ። ፓርቲው በታሪካዊው ምርጫ-97 ወቅት ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ የተባለውን ዋነኛ የተቃዋሚ ጎራ ከመሰረቱት አምስት ድርጅቶች አንዱ ነበር። በቅድመ-ምርጫ የክርክር መድረኮች ላይ አንደበተ-ርቱዕው ልደቱ አያሌው በተለየ ሁኔታ ጎልቶ ወጣ። ከአዲስ አበባ አልፎ የወጣቱ ፖለቲከኛ ስምና ዝና በመላ ኢትዮጵያ ገነነ።

ሆኖም ግን መጨረሻው እንደታሰበው ሳይሆን ቀርቶ የድህረ-ምርጫ ኩነቶች በህዝባዊ አመፅ እና የመንግስት የፀጥታ ኃይል በወሰዳቸው ዘግናኝ እርምጃዎች በውዝግብ የተሞላ ሆነ። ከዚህ ሂደት ጋር በተያያዘ የቅንጅት አመራር ከፍተኛ ጫና ውስጥ ገብቶ ተከፋፈለ። አብዛኛዎቹ የምርጫውን ውጤት ባለመቀበል ፓርላማ ላለመግባት ከህዝብ የተደረገባቸው ግፊት ተቀብለው አሻፈረን ሲሉ አቶ ልደቱ የቅንጅትን ማህተም ይዞ በተቃራኒዉ ቆሞ። ይሄን የቅንጅት አመራር አቋም ተከትሎ ፓርላማ አልገባም ያሉት ወደ ማረሚያ ቤት ሲላኩ አቶ ልደቱ ከተራው የድርጅቱ ተመራጮች ጋር ፓርላማ ገባ።

የቅንጅት መፍረስ እስከ አሁን አነጋጋሪ እና የአቶ ልደቱን የፖለቲካ ስብዕና የቀበረ ሆኖ በማለፉ ሁኔታውን ለኢትዮጵያ ህዝብ ካላስረዳሁ በማለት ዛሬም ላይ ታች ሲል ይታያል። ቅንጅቱን በመበተኑ የማን ሚና የጎላ ነበር? ለሚለው ጥያቄ ህዝብ በአገኘው መረጃ ልክ ብያኔ ሰጥቶበት ያለፈው ምናልባትም በሀገራችን ታሪክ ከፍተኛ የህዝብ ትኩረት አግኝቶ የነበረ ክስተት ነው። ቢሆንም ልደቱ እስከ ዓለም ፍጻሜ የእርሱን “እውነት” ለማወቅ የምንጨነቅ የሚመስለው ለምንድን ነው? መጻሕፍት ጽፎ፣ መቶ መግለጫ ሰጥቶ ወዘተ እውነቱን ያስረዳ ካልመሰለው እስኪ ምናልባት እነዚህ ስድስት ነገሮች ሆነው ይሆናል በሉት።

ይሆናል 1፤ ምናልባት የምታስረዳው “እውነት” የለ ይሆናል፤ ወይም ከሌላ አንጻር ቆመው ሲያዩት የሚጠቅም ታሪክ እና እውነት አይደለም ይሆናል። እርግጠኝነትህን ተጠራጠረው።

ይሆናል 2፤ “እውነቱ” ባንተ ብቃት/ቁመና ሊገለጽ፣ ሊሰበክ የማይችል ሆኖ ይሆናል። እስቲ ሌሎች ይህንን እውነት እንዲያስረዱት ተውላቸው። መለኮታዊ ተልእኮ ተሰጥቶህ እንኳን ቢሆን ለላከህ አካል “አልቻልኩም፣ አልሰሙኝም” ብለህ ንገረው። ነቢያት አድርገውታል።

ይሆናል 3፤ እንዲሰሙህና እንዲለወጡ የምትፈልጋቸው ሰዎች ያንተን “እውነት” ለመስማት ወይም/እና ለመቀበል አይፈልጉ ወይም አልበቁ ይሆናል። ተዋቸው። ግዴታ አታድርግባቸው። ያንተን እውነት ማወቅም ሆነ መቀበል አንተ የምታስበውን ያህል ጠቃሚ ላይሆን ይችላል። አይደለምም።

ይሆናል 4፤ ሕይወትህን ወይም ትርጉሟን በአንድ ያንተ እውነት ላይ ብቻ አንጠልጥለሃት፣ እረፍት ነስቶህ ይሆናል። የፖለቲካም ሆነ ሌላ ሕይወትህን (ወይም ትርጉሙን) ከዚህ ከምትለው እውነት/ትርክት ለማፋታት ሞክር። ሌላው ቀርቶ፣ የፖለቲካ ሕይወትንም ጭምር ከዚህ ከምትለው “እውነት” ውጭ እንደ አዲስ ልትገነባ ትችላለህ፤ ከፈለግህ። እውነት የምትለው ጉዳይ/ትርክት እስረኛ አትሁን። ራስህን ፍታ።

ይሆናል 5፤ ፖለቲካ ጨዋታ መሆኑን ረስተኸው ይሆናል። በማንኛውም ጨዋታ መብለጥ፣ መበለጥ ያለ ነው። አንድ ግጥሚያ በፍትሕ በርትእ ይዳኝም አይዳኝም አጠቃላይ ጨዋታው ይቀጥላል። ያለፈውን ግጥሚያ ወደኋላ ተመልሶ መቀየር አይቻልም። ስላለፈው ግጥሚያ ስሕተቶች ያልካቸውን ለማስረዳት ሞክረሃል። ከዚያ በላይ ማድረግ አትችልም። ጨዋታው ካንተ የግል ውጤትና ስሜት ይበልጣልና መቀጠሉ አይቀርም። ወደ ጨዋታው ተመለስ፤ ወይም ጨዋታ ቀይር፤ ወይም ጨዋታ ተው።

ይሆናል 6፤ ስፖርተኛ ሆነህ ከተጎዳህ ቢያንስ ሕመምህ እስኪድን ጉዳት ካደረሰብህ ጨዋታ ማረፍ አለብህ። አንተ ከፖለቲካ በቂ እረፍት ሳትወስድ እየተመላለስክ ሕመምህ እንዳይሽር አድርገኸው ይሆናል። ካስቻለህ በቂ እረፍት አድርግ። ካላስቻለህ፣ ለቅሶህን አቁመህ፣ ወደምትወደውና ወደምትችለው የፓርቲ ፖለቲካ በቀጥታ ግባ። አለዚያም ከፓርቲ ፖለቲካ ውጭ ባለ መድረክ ለምሳሌ ትንተና ወደ መስጠት፥ ወደ ማጥናት ወዘተ ዙር። በአንድ ነጠላ ጉዳይ ላይ ጊዜህን፣ ስሜትህን እና አቅምህን አታባክን።

ነገሩ እንዲህ ነው።

(ይህን አስተያየቴን የሆነ ባንተ ላይ የተሸረበ ሴራ አካል አድርገህ እንደማታየው ተስፋ አደርጋለሁ። ያው ተስፋ ነው።)

መስፍን ነጋሽ፤ 10 Oct 2018 የተፃፈ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: lidetu ayalew, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule