• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልደቱ አያሌውን ስድስት ነገሮች ሆነው ይሆናል በሉት

September 13, 2021 11:23 am by Editor Leave a Comment

አቶ ልደቱ አያሌው የፖለቲካ ህይወቱን አሀዱ ብሎ የጀመረው 1983ዓ.ም. ህወሃት/ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ የከተማዋን ወጣቶች የማደራጀት ስራ ላይ ከተሰማሩ ወጣቶች አንዱ ሆኖ ነው። በዚያ ወቅት ወጣቱ ልደቱ ለወያኔ መንግስት የመወገን ጫና በነበረበት የወጣት ማህበር ምስረታ ሂደት ንቁ ተዋናይ ነበረ። በመሆኑም የማህበሩ ሊቀመንበር የመሆን ፍላጎት እንደነበረው በወቅቱ አብረውት የነበሩ የመሰከሩት ነገር ነው። ነገር ግን በ1990 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በይፋ ሲመሰረት ወጣቱን በማደራጀት ምንም ተሳትፎ ያልነበረው የዳዊት ዮሃንስ (አፈጉባዔ የነበረ) ሚስት ወንድም የሆነው ወጣት ታጠቅ ካሳ ሊቀመንበር ሆኖ ተመረጠ።

ይሄኔ ነው እንግድህ የልደቱ የመጀመሪያው የፖለቲካ አቋም እጥፋት የተጀመረው። የታጠቅን በሊቀመንበርነት መመረጥ አሚን ብሎ መቀበል አልፈለገም። የተመሰረተው ማህበር ግን እንደታሰበው ከፖለቲካ ፓርቲዎች ገለልተኛ እንደማይሆን እና ይልቁንም የኢህአዴግ የወጣት ክንፍ ሊባል የሚችል ነው። ያዛኔው ልደቱን ያበሳጨው ጉዳይ የወያኔ አገልጋይ ለመሆን አለመታመኑ ብቻ ነው። በመሆኑም ቀጥሎ የሄደው አዲስ ወደ ተመሰረተው የፕ/ር አስራት ወልደየስ ፓርቲ መአሕድ ነው። ልደቱ በይፋ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሆኖ ሲወጣ ኃላፊነቱን የጀመረው በተመሳሳይ የመአሕድ ወጣት ክንፍ አመራርነትን ሲቀላቀል ነው።

ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ጥሎ ወጥቶ እስከ አሁን ድረስ የሚመራውን የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን (ኢዴፓ) መሠረተ። ፓርቲው በታሪካዊው ምርጫ-97 ወቅት ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ የተባለውን ዋነኛ የተቃዋሚ ጎራ ከመሰረቱት አምስት ድርጅቶች አንዱ ነበር። በቅድመ-ምርጫ የክርክር መድረኮች ላይ አንደበተ-ርቱዕው ልደቱ አያሌው በተለየ ሁኔታ ጎልቶ ወጣ። ከአዲስ አበባ አልፎ የወጣቱ ፖለቲከኛ ስምና ዝና በመላ ኢትዮጵያ ገነነ።

ሆኖም ግን መጨረሻው እንደታሰበው ሳይሆን ቀርቶ የድህረ-ምርጫ ኩነቶች በህዝባዊ አመፅ እና የመንግስት የፀጥታ ኃይል በወሰዳቸው ዘግናኝ እርምጃዎች በውዝግብ የተሞላ ሆነ። ከዚህ ሂደት ጋር በተያያዘ የቅንጅት አመራር ከፍተኛ ጫና ውስጥ ገብቶ ተከፋፈለ። አብዛኛዎቹ የምርጫውን ውጤት ባለመቀበል ፓርላማ ላለመግባት ከህዝብ የተደረገባቸው ግፊት ተቀብለው አሻፈረን ሲሉ አቶ ልደቱ የቅንጅትን ማህተም ይዞ በተቃራኒዉ ቆሞ። ይሄን የቅንጅት አመራር አቋም ተከትሎ ፓርላማ አልገባም ያሉት ወደ ማረሚያ ቤት ሲላኩ አቶ ልደቱ ከተራው የድርጅቱ ተመራጮች ጋር ፓርላማ ገባ።

የቅንጅት መፍረስ እስከ አሁን አነጋጋሪ እና የአቶ ልደቱን የፖለቲካ ስብዕና የቀበረ ሆኖ በማለፉ ሁኔታውን ለኢትዮጵያ ህዝብ ካላስረዳሁ በማለት ዛሬም ላይ ታች ሲል ይታያል። ቅንጅቱን በመበተኑ የማን ሚና የጎላ ነበር? ለሚለው ጥያቄ ህዝብ በአገኘው መረጃ ልክ ብያኔ ሰጥቶበት ያለፈው ምናልባትም በሀገራችን ታሪክ ከፍተኛ የህዝብ ትኩረት አግኝቶ የነበረ ክስተት ነው። ቢሆንም ልደቱ እስከ ዓለም ፍጻሜ የእርሱን “እውነት” ለማወቅ የምንጨነቅ የሚመስለው ለምንድን ነው? መጻሕፍት ጽፎ፣ መቶ መግለጫ ሰጥቶ ወዘተ እውነቱን ያስረዳ ካልመሰለው እስኪ ምናልባት እነዚህ ስድስት ነገሮች ሆነው ይሆናል በሉት።

ይሆናል 1፤ ምናልባት የምታስረዳው “እውነት” የለ ይሆናል፤ ወይም ከሌላ አንጻር ቆመው ሲያዩት የሚጠቅም ታሪክ እና እውነት አይደለም ይሆናል። እርግጠኝነትህን ተጠራጠረው።

ይሆናል 2፤ “እውነቱ” ባንተ ብቃት/ቁመና ሊገለጽ፣ ሊሰበክ የማይችል ሆኖ ይሆናል። እስቲ ሌሎች ይህንን እውነት እንዲያስረዱት ተውላቸው። መለኮታዊ ተልእኮ ተሰጥቶህ እንኳን ቢሆን ለላከህ አካል “አልቻልኩም፣ አልሰሙኝም” ብለህ ንገረው። ነቢያት አድርገውታል።

ይሆናል 3፤ እንዲሰሙህና እንዲለወጡ የምትፈልጋቸው ሰዎች ያንተን “እውነት” ለመስማት ወይም/እና ለመቀበል አይፈልጉ ወይም አልበቁ ይሆናል። ተዋቸው። ግዴታ አታድርግባቸው። ያንተን እውነት ማወቅም ሆነ መቀበል አንተ የምታስበውን ያህል ጠቃሚ ላይሆን ይችላል። አይደለምም።

ይሆናል 4፤ ሕይወትህን ወይም ትርጉሟን በአንድ ያንተ እውነት ላይ ብቻ አንጠልጥለሃት፣ እረፍት ነስቶህ ይሆናል። የፖለቲካም ሆነ ሌላ ሕይወትህን (ወይም ትርጉሙን) ከዚህ ከምትለው እውነት/ትርክት ለማፋታት ሞክር። ሌላው ቀርቶ፣ የፖለቲካ ሕይወትንም ጭምር ከዚህ ከምትለው “እውነት” ውጭ እንደ አዲስ ልትገነባ ትችላለህ፤ ከፈለግህ። እውነት የምትለው ጉዳይ/ትርክት እስረኛ አትሁን። ራስህን ፍታ።

ይሆናል 5፤ ፖለቲካ ጨዋታ መሆኑን ረስተኸው ይሆናል። በማንኛውም ጨዋታ መብለጥ፣ መበለጥ ያለ ነው። አንድ ግጥሚያ በፍትሕ በርትእ ይዳኝም አይዳኝም አጠቃላይ ጨዋታው ይቀጥላል። ያለፈውን ግጥሚያ ወደኋላ ተመልሶ መቀየር አይቻልም። ስላለፈው ግጥሚያ ስሕተቶች ያልካቸውን ለማስረዳት ሞክረሃል። ከዚያ በላይ ማድረግ አትችልም። ጨዋታው ካንተ የግል ውጤትና ስሜት ይበልጣልና መቀጠሉ አይቀርም። ወደ ጨዋታው ተመለስ፤ ወይም ጨዋታ ቀይር፤ ወይም ጨዋታ ተው።

ይሆናል 6፤ ስፖርተኛ ሆነህ ከተጎዳህ ቢያንስ ሕመምህ እስኪድን ጉዳት ካደረሰብህ ጨዋታ ማረፍ አለብህ። አንተ ከፖለቲካ በቂ እረፍት ሳትወስድ እየተመላለስክ ሕመምህ እንዳይሽር አድርገኸው ይሆናል። ካስቻለህ በቂ እረፍት አድርግ። ካላስቻለህ፣ ለቅሶህን አቁመህ፣ ወደምትወደውና ወደምትችለው የፓርቲ ፖለቲካ በቀጥታ ግባ። አለዚያም ከፓርቲ ፖለቲካ ውጭ ባለ መድረክ ለምሳሌ ትንተና ወደ መስጠት፥ ወደ ማጥናት ወዘተ ዙር። በአንድ ነጠላ ጉዳይ ላይ ጊዜህን፣ ስሜትህን እና አቅምህን አታባክን።

ነገሩ እንዲህ ነው።

(ይህን አስተያየቴን የሆነ ባንተ ላይ የተሸረበ ሴራ አካል አድርገህ እንደማታየው ተስፋ አደርጋለሁ። ያው ተስፋ ነው።)

መስፍን ነጋሽ፤ 10 Oct 2018 የተፃፈ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: lidetu ayalew, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule