የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ወደ ቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ እንደገባና አቀባበል እንደተደረገለት ቡለን ወረዳ አሳውቋል። የቡለን ወረዳ በይፋዊ ማህበራዊ ትስስር ገፁ ፥ "ለዘላቂ ሰላም የሚንቀሳቀሰው የአማራ ክልል ልዩ ሀይል በቡለን ከተማ አቀባበል ተደርጎለታል" ሲል ፅፏል። ወረዳው በአቀባበሉ ላይ የቡለን ወረዳ ወጣቶች፣ ነዋሪው፣ ማህበረስቡና የሴክተር መስርያ ቤት ሰራተኞችና አመራሩን ጨምሮ ከከተማው 1 ኪ/ሜትር ወጣ ብሎ በመሄድ አቀባበል አድርገዋል ሲል ገልጿል። የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ወደቡለን ወረዳ መግባቱ በወረዳው ያለውን የፅጥታ ችግር ለመፍታት፣ ማህበረሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ለማድረግ አስተዋጽዖ ያደርጋል ተብሏል። ቡለን ወረዳ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ውስጥ የፀጥታ ስጋት ካለባቸው ወረዳዎች አንዱ ሲሆን በተደጋጋሚ ጊዜ … [Read more...] about የአማራ ክልል ልዩ ኃይል መተከል ዞን ገባ
metekel
የመተከል ዞን ሕዝብ ሊደራጅና ሊታጠቅ ይገባዋል – አቶ ደመቀ መኮንን
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በዛሬው (ሰኞ) ዕለት የተፈፀመውን አሳዛኝ ድርጊት መነሻ በማድረግ በመተከል ዞን ከሚመራው ኮማንድ ፖስት አመራር አካላት ጋር በዞኑ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ መክረዋል። ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች ቤተሰቦች እና ወዳጆች መፅናናትን ተመኝተዋል። በዞን የተለየዩ አካባቢዎች ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት ኮማንድ ፖስት ተደራጅቶ የራሱን ዕቅድ አዘጋጅቶ ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም፤ አሁንም የዜጎች ህይወት በአሳዛኝ ሁኔታ መጥፋት መቀጠሉ ሪፖርት ቀርቧል። በዚህ አካባቢም ሆነ በሌሎች ሠላምና ፀጥታን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመፍጠር የሴረኞችን ገመድ መበጣጠስ፣ ጠንካራ የህግ የበላይነት ማስከበር ህብረተሰቡ ራሱን የመከላከል አቅም እንዲኖረው ማድረግ ወሳኝ ተግባር መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ … [Read more...] about የመተከል ዞን ሕዝብ ሊደራጅና ሊታጠቅ ይገባዋል – አቶ ደመቀ መኮንን