• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ

January 10, 2023 03:36 pm by Editor Leave a Comment

የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ቴድሮስ በቀለ እና ባለቤታቸው ሩት አድማሱን ጨምሮ በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ።

ተከሳሶቹ:—

1ኛ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ቴድሮስ በቀለ፣

2ኛ ተከሳሽ የአቶ ቴድሮስ ባለቤት ሩት አድማሱ፣

3ኛ የወ/ሮ ሩት እህት ቤተልሔም አድማሱ እና በግል ሥራ ይተዳደራሉ የተባሉት መርሐዊ መርሃዊ ምክረ ወልደፃዲቅ ፣ ራሄል ብርሃኑ፣ ፀሐይ ደሜ እና ጌታቸው ደምሴ ናቸው።

የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሁለት ክሶችን የመሰረተ ሲሆን፥ አንደኛው በቴድሮስ በቀለ ላይ ብቻ የቀረበ ክስ ነው፡፡

በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በተመሰረተው 2ኛ ክስ ከ1ኛ እስከ 7ኛ ተራ ቁጥር በተጠቀሱ ተከሳሶች ላይ በዝርዝር ቀርቧል።

በ1ኛው ክስ አቶ ቴድሮስ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲሠሩ የተቋሙን አሠራር ባልተከተለ መልኩ አስፈላጊው የደኅንነት ይለፍ ያልተደረገለትን የትምህርት ዝግጅቱ ብቁ ያልሆነና በሌላ የሙስና ወንጀል መዝገብ የተከሰሰ አቤል ጌታቸው የተባለ ግለሰብን ከታኅሣሥ 1ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በተቋሙ የተደራጁና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀሎች ፍተሻና ትንተና ከፍተኛ ኤክስፐርት ሆኖ እንዲሠራ ወደ ተቋሙ እንዲቀላቀል አድርገዋል ሲል ዐቃቤ ሕግ ዘርዝሯል።

በዚህም የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9(1) (ሀ) እና (3) ላይ የተመለከተውን ተላልፈዋል በሚል ነው ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተው፡፡

እንዲሁም ከሰኔ 1ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ አቤል ጌታቸው የተባለን ግለሰብ የፋይናንስ መረጃ ክትትል እና ቅበላ ቡድን መሪ አድርገው ባልተገባ መንገድ መመደባቸው በክሱ ተመልክቷል፡፡

የተቋሙን የቀደመ የመረጃ ምስጢራዊነት የጠበቀ እና ተጠያቂነትን ያማከለ የመረጃ ቅበላ እና ትንተና አሠራርን በመለወጥ፣ በተቋሙ ውስጥ ስልጣንን ተገን በማድረግ፣ የባለሀብቶችንና የድርጅቶችን የባንክ ሂሳብ አስቀድሞ በማጥናትና መረጃ በመውሰድ፣ በተለያየ ጊዜ ለባለሀብቶች ስልክ በመደወል በአካል በማግኘት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንዲከፍሉ በመጠየቅ፣ የማይከፍሉ ከሆነ ደግሞ የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውን በተመለከተ ምርመራ አድርጎ ለፖሊስ በማስተላለፍ የወንጀል ምርመራ እንዲጀመርባቸው እንዲደረግ ይገልፅ እንደነበረ በክሱ ተጠቅሷል።

ተከሳሹ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ውስጥ የነበረውን ኃላፊነት በመጠቀም፣ የፋይናንስ ትንተና በመሥራት ውጤቱን ለፍትሕ አካላት የሚተላለፍ ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም፣ ገንዘብ ያላቸው ባለሀብቶችን አስቀድሞ በማጥናት በመምረጥ በ2013 እና በ2014 ዓ.ም በተለያየ ጊዜ ባለሀብቶች የባንክ ሒሳባቸው እንደሚታገድ እና በፖሊስ እንደሚመረመሩ እንደሚደረጉ በመግለጽ በማስፈራራት ከሦስት ግለሰቦች 3 ሚሊየን 470 ሺህ ብር ገንዘብ በፋፋ ዳባ በተባለ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ እንዲደረግ በማድረግ በዋና ወንጀል አድራጊነት ስልጣንን አላአግባብ መገልገል ከባድ ሙስና ወንጀል ተከሰዋል።

በሁሉም ተከሳሾች በቀረበው ሁለተኛ ክስ ደግሞ፥ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32/1/ሀ እና በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ወይም ንብረትን ሕጋዊ አድርጎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29 (1) (ሀ) (ለ) እና (ሐ) ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ ተከሰዋል፡፡

ተከሳሾቹ በወንጀል የተገኘ 3 ሚሊየን 470 ሺህ ብር የወንጀል ፍሬ መሆኑን እያወቁ የገንዘቡን ምንጭ ለመደበቅ በማሰብ ግብረአበር ነው የተባለ ፋፋ ዳባ እየተባለ የሚጠራ ግለሰብ ስም በባንክ በተከፈተ ሒሳብ ገቢ እንዲደረግ በማድረግና ከገንዘቡ በተለያየ መጠን በመጠቀም ሕገ ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ማቆረብ ወንጀል ተከሰዋል።

ተከሳሾቹ ከጠበቆቻቸው ጋር ቀርበው ክሱ እንዲደርሳቸው ከተደረገ በኋላ በችሎት ክሱ በንባብ ተሰምቷል።

ቀደም ሲል ለአንድ ወር ከቴድሮስ በቀለ ጋር በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ ሲደረግባቸው የቆዩት የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የመረጃ ኦፕሬሽን ዲቪዢን ኃላፊ ባሕሩ ደምሴን በሚመለከት÷ ዐቃቤ ሕግ ምርመራቸው አለመጠናቀቁን ተከትሎ በዚህ ክስ ላይ አለማካተቱን ረፋድ ላይ የምርመራ መዝገባቸውን ሲመለከት ለነበረው ለጊዜ ቀጠሮ ችሎት አስታውቋል። (ታሪክ አዱኛ Fana)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: anti-corruption campaign, corruption, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule